• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመተማው “የዘር-ፍጅት” ትርክት በደህንነት ተቋሙ የተቀናበረ ነበር

September 22, 2016 07:58 pm by Editor 2 Comments

በቅርቡ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ መተማ-ዮሀንስ አካባቢ በትግርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ ተፈፀመ የተባለው ዘርን ያማከለ ጥቃት ሆነ ተብሎ በፀጥታ ሰራተኞች የተቀነባበረ እንደነበረ ጉዳዩን በቅርብ የመረመሩ የዲፕሎማቲክ ምንጮች መሰከሩ።

አጋጣሚውን የትግራይ ክልል መንግስት አልያም የሀገሪቱ የደህንነት ባለስልጣናት “የዘር-ፍጅት አደጋ” እንደተከሰተ አድርገው በማቅረብ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ሀዘኔታና ድጋፍ ለማግኘት ሙከራ ማድረጋቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች ተገኝተዋል።

የዋዜማ ሁነኛ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ባደረሱን መረጃ – ድርጊቱ በተፈፀመበት ወቅት በስፍራው የነበሩ የረድኤት ስራተኞች፣ ከድርጊቱ በኋላ ወደ ስፍራው ያመሩ ሁለት አጣሪ ቡድኖችና የአማራ ክልል መንግስት ባልስልጣናት የደረሱበት መደምደሚያ፣ የመንግስት የደህንነት ሰራተኞች በበላይ አለቆቻቸው ትዕዛዝ መሰረት የትግራይ ተወላጆች ሸሽተው ወደ ሱዳን እንዲገቡ አድርገዋል።

ሽሽቱ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ውጥረት እንደነበረ ግን ደግሞ የትግራይ ተወላጆች ላይ በተለይ ያነጣጠረ እንዳልነበረ ኋላ ግን በርካታ ትግርኛ ተናጋሪዎች ሽሽት መጀመራቸው ድንጋጤን ፈጥሮ እንደነበር ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ የሆነ ዲፕሎማት በፃፉት የውስጥ ስነድ ላይ ገልፀዋል።

ይህን ጉዳይ ማጣራት ያስፈለገው የተባለው እውነት ከሆነ ችግሩን ለመቀልበስ በማለም እንደነበር ሰነዱ በመግቢያው ያትታል።

የትግርኛ ተወላጆቹ ሽሽት ከመጀመራቸው በፊት ፀጉረ – ልውጥ የፀጥታ ሰራተኞች ወደስፍራው መድረሳቸውንና የአካባቢው (የአማራ ክልል ባለስልጣናት) ስዎች በመኪና ተጭነው እስኪወጡ የሚያውቁት ነገር እንዳልነበር ምስክርነት ሰጥተዋል። የትግርኛ ተናጋሪዎቹ ከአካባቢው ሲወጡና ጉዞ ሲጀምሩ በደህንነት ሰራተኞቹ ፊልም መቀረፃቸውን መመልከታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ቢያንስ ሶስት መኖሪያ ቤቶች ላይ ነዋሪዎቹ ከወጡ በኋላ ባልታወቁ ሰዎች ጥቃት መፈፀሙን የሚያሳይ መረጃ አለ።

በወቅቱ በስፍራው የነበሩ ሶስት የረድዔት ሰራተኞች በአጋጣሚ ሰዎች የተሰባሰቡበት አካባቢ በመገኘታቸው ለአራት ሰዓታት በአነስተኛ ምግብ ቤት ውስጥ ታግተው እንደነበርና ስልኮቻቸውና ካሜራቸው ላይ የነበሩ ምስሎች መበርበራቸውን ተናግረዋል።

ይህን ጉዳይ ለማጣራት ወደ ስፍራው የተላኩ ሁለት የተለያዩ መረጃ አሰባሳቢዎች ያገኙት መረጃ የትግርኛ ተናጋሪዎቹ ሽሽት በተደራጀ መልክ መካሄዱን የሚያሳዩ መረጃዎች መኖራቸውን ሪፖርት አድርገዋል።

“አካባቢው ለድንበር ቅርብ በመሆኑ ከፍተኛ ወታደራዊና የደህንነት ሰራተኞች የሚንቀሳቀሱበት ሆኖ ሳለ ለምን ሌሎች የደህንነት ሰራተኞች ከመቀሌ ወይም ከአዲስ አበባ ወደ ስፍራው እንደተላኩ ግልፅ አይደለም” ይላሉ መረጃ አሰባሳቢዎቹ።

“በትግርኛ ተናጋሪዎች ላይ ስጋትና ፍራቻ መኖሩን መካድ አይቻልም ይሁንና ኢትዮጵያውያን በአመዛኙ ለማህበራዊ ትስስር በሚሰጡት ልዩ ዋጋ ይህ አብሮነት እንዲናጋ የሚፈቅዱ አይደሉም፣ በመተማ የነበረው ሁኔታም በዚህ መነፅር መታየት ይኖርበታል” ይላሉ ዲፕሎማቱ በሰነዱ ላይ ባሰፈሩት አስተያየት።

“እስካሁን ባለን መረጃ ጥቃት የተፈፀመባቸው የትግርኛ ተናጋሪዎች በቁጥር እጅግ ኢምንት ናቸው። በአብዛኛው ገና ለገና ጥቃት ይፈፀምብኛ በሚል ስጋት ከባህር ዳር ጎንደርና የኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች መኖሪያቸውን ለቀው ወደ አዲስ አበባና ወደ ትግራይ ያመሩ መኖራቸውን እናውቃለን” ይላል ሪፖርቱ ።

“ይህን ስጋት የደህንነት ተቋሙ እንደ ጥሩ አጋጣሚ ሊጠቀምበት መሞከሩን በቂ ፍንጮች አሉ” ይላል ሰነዱ። “ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታና የትግራይ ተወላጆችን ከጎኑ ለማሰለፍ ፍላጎት እንዳለው ማሳያ ነው”

“ለሌሎች ኢትዮጵያውያንም ሀገሪቱ በዘር ፍጅት አደጋ አፋፍ ላይ እንዳለች አስመስሎ በማሳየት በሀገሪቱ ያለው ተቃውሞ ‘አደጋ ያመጣል’ የሚል ስጋት የማጫር ዕቅድም ሊኖረው ይችላል። ይህን ዋናው የደህንነት መስሪያ ቤት ወይም የትግራይ ክልል በተናጠል/ በጋራ ያደረገው መሆኑን መረጋገጥ አልቻልንም”

የትግራይ ክልል አልያም የማዕከላዊ መንግስት የዘር ፍጅት አደጋ ማንዣበቡን በመተማው አጋጣሚ በማሳየት ራሱን አረጋጊና የሰላም ዋስትና የማድረግ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ያለ ኢህአዴግ አመራር ሀገሪቱ ወደ እልቂት እንደምትገባ ለማመላከት ዓላማ ሊያውለው መሞከሩን ዲፕሎማቱ በሰጡት አስተያየት አስፍረዋል።

በጎንደር ተቃውሞ ተባብሶ በነበረበት ሀምሌ 2008 የኢትዮጵያ መንግስት በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን (ኢሳትና) በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ የአማርኛው ክፍል (VOA ላይ የዘር ፍጅት ቅስቀሳ አድርገውብኛል ሲል ለአሜሪካ መንግስት ክስ አቅርቦ ነበር። ክሱ ተቀባይነት አላገኘም።

የኢትዮጵያ ደህንነት መስሪያ ቤት ራሱ ፈንጂ በማፈንዳት ተቃዋሚ የፖለቲካ ሀይሎችንና ኤርትራን ይወነጅል እንደነበረ ከዚህ ቀደም ይፋ የሆነ የአሜሪካምስጢራዊ የዲፕሎማቲክ ሰነድ መግለፁ ይታወሳል። (ምንጭ: ዋዜማ ራዲዮ)

(ፎቶ: የትግራይ ተወላጆች በዘር ፍጅት አደጋ ሊደርስባቸው በመሆኑ መፈናቀላቸው የሚያሳይ – Tigrai Online)

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Alemayehu seifu says

    September 23, 2016 08:29 pm at 8:29 pm

    Weyane yewdem ke siltan yewred

    Reply
  2. Angile says

    September 24, 2016 04:28 pm at 4:28 pm

    የህዝብ ጥያቄ ስልጣን በአንድ አንስተኛ ጠባብ እጅ ስለወደቀ እኩል ተካፍለን አገራችን በጋራ እናስተዳድር ነው። የ 100 ሚሊዮን ህዝብ አገር በጥቂቶች መተዳደር ይብቃ። የአደራ መንግስት ሁሉንም ያካተተ ይቋቋም ነው ያለው ህዝቡ። ጥገና ሳይሆን ለውጥ። ሰው መቀያየር ሳይሆን የስርዐት ለውጥ። አባ ድላን አንስቶ ተሾመ ቶጋን መተካት ሳይሆን ምሁራንን የአገር ሽማግሌዎችን ተቃዋሚዎችን ያካተተ የአደራ መንግስት በአስቸኳይ ይቋቋም ነው ጥያቄው መልሱም እሱ ብቻ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule