• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢህአዴግ ዉሸት – እስካሁን ደህና ነኝ ማለት

July 12, 2015 07:18 am by Editor Leave a Comment

እሙሩ ብሪታንያዊ የምርመራ ጋዜጠኛ ኒኮላስ (ኒክ) ዴቪስ የብዕሩ ሞገስ ይደርጅለትና ዕውነት እንዳንናገር፣ ሀቅ እንዳንዘረዝር የሚያደርጉን ሠለስቱ ቀታሊያን ሥህተቶች፣ ሦስቱ ገዳይ ድክመቶች:-

“1) የምንመርጣቸው ርዕሰ ጉዳዮች ዕውነታውን በመሠረታዊ መንገድ የሚያፋልሱት እንዲሆኑ በማድረግ ዋናውን ጭብጥ ማሳት፣

“2) በተደጋጋሚ የምንጠቀምባቸውን ኢተአማኒ፣ አንዳንዴም ፈጽሞ ውሸት፣ የሆኑ ጭብጦች ደጋግመን በመጠቀም ዕውነተኛ ማስረጃዎች እንዲመስሉ ማድረግ፣

“3) ከአካባቢው ህብረተሰብ መካከል ኃይለኛ ጉልበት ያላቸውን ወገኖች የሚያደምቁ ዕሴቶችን የማያቋርጥ አሻራ እንዲኖራቸው ፖለቲካዊና ሞራላዊ ውትወታን ማብዛት፣ ናቸው” ሲል የጣፈው ቀልብ የሚማርክና ለአብነት የሚጠቀስ መንደርደሪያ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ማለፊያ አስተዉሎት ነው መቼም።

ታድያ ይህን የኒኮላስ ዴቪስን ሓቲት ባስታወስኩ ቁጥር በሃሳቤ ወዲያው ደርሶ የሚደቀነው ፀሐዩ መንግሥታችን (ኢህአዴግ) ነው። ዉሸት የኢህአዴግ መለዮ ማንነቱ ሆኗል። ተሳስቶ እዉነት መናገር አልፈጠረበትም፣ ሲያልፍም አይነካካው። እንዲያው ተገዶ ለመናገር ቢገፋፋም ሺህ ዉሸቶች አካቦ፣ ሁልቆ መሳፍርት የሌላቸው የፈጠራ እብለቶች ቀንብቦ ነው። ስለ ምጣኔ ሀብት እድገት፣ ስለህዝብ ኑሮ መሻሻል፣ ስለድንበር ጉዳይ፣ ስለ ሃይማኖት ተቋማት፣ ስለ መለስ ሞት፣ ስለአንዳርጋቸው አፈና፣ ስለ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ስለጋዜጠኞችና ፀሐፍት፣ ለሰላም ማስከበር ሥራ ወደተለያዩ ሀገሮች ስለሚሄዱ የሠራዊት አባላት፣ ስለምርጫ፣ ስለባድመና የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት፣ ስለመተካካት፣ የቱን አንስተን የቱን እንተው? ዉሸት ያልቀላቀለበትን፣ ሐሰት ያልዶለበትን ጉዳይ አስሶ ፈልጎ ማግኘት ዘበት ነው ያሉ ዋሹ አይሰኙም። ይዋሻል። ሎሌዎቹንም ዓይናቸዉን በጨው አጥበው ይዋሹለት ዘንድ ያሰልጥናል፣ ይገራል፣ ያዛል። ማጅራታቸዉን አንቆ ይዞ፣ በፍርፋሪ ሹመትና ጉርሻ አንብዞ፣በሙስና (በስኳር) አፍዝዞ ያስዋሻቸዋል። በሁሉም ትካር (ጉዳይ) ላይ ቅጥፈትን ዋልታ አድርጎ ነው ሃሳብና ድርጊትን የሚቀልሰው። አንዳንዴ ሳስበው፣ የዚህ ሥርዓት ግፈኝነት ምንጩ ከጥላቻ ቀጥሎ በዉሸትና ክህደት ላይ መመስረቱ ነው ብዬ ለማመን እገደዳለሁ። ተቆጠቡም ተናገሩት፣ ገለፁትም ደበቁት ኢትዮጵያዉያን ይህን አመሉን አንጥረው አብጠርጥረው ያውቁታል። “ማወቁንማ እናውቃለን፣ ብንናገር እናልቃለን” ሆነ እንጂ ችግሩ!

የሥነ ልቡና ጠበብት እንደሚያስተምሩን፣ ዉሸት የደካሞች ባህርይ ሲሆን መጨረሻዉም ዉድቀት መሆኑ አያጠራጥርም። ሌላው ሌላው ይቅርና ትላንት ከአለም 46ኛ ከአፍሪካ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፣ አቻ የሌለው የዘመኑን ቴክኒዎሎጂ ታጥቋል፣ ሰው አልባ አውሮፕላን ሰርቷል፣ አለምን ያርበደብዳል ተብሎ ወታደራዊ ትዕይንት ያሳየው የመከላከያን ቀን በድምቀት ያከበረው ሠራዊት፣ መሳሪያዎቹ ሁሉ ጊዜ ያለፈባቸዉና ያረጁ፣ ምንም ጥቃት ለመቋቋም አቅም የሌለው መሆኑን በምሥጢር በተካሄደው የአመራሩ ስብሰባ ላይ ጄኔራል ሳሞራ ያቀረበው ሪፖርት የመንግስታችንን እኩይ ገፅታ በአሳፋሪ ሁኔታ አጋልጦታል። መከላከያ ኦዲት የማይደረግ፣ የህዝብ ሀብት በከፍተኛ ሁኔታ እየተመዘበረ ጎጠኞች ያበጡ የናጠጡ ቱጃሮች የሆኑበት የገለማ የነቀዞች እልፍኝ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው። እድሜ ለአርበኞችና ግንቦት ሰባት ገና አንድ ጥይት ከመተኮሳቸው የመንግሥታችን ጭንብል ተገለጠ።

መንግስታችን አሁንም የልማዱን ይዋሻል። የወጋችን ኤርትራ አይደለችም። የኢህአዴግ የአፈና ሥርዓት ሆድ ያስባሰው ወገን ኢህአዴግን አስወግዶ፣ ዴሞክራሲና ፍትህን ለማስፈን የሚያደረገው ሁለገብ ትግል አካል መሆኑን ነገሮናል። ኤርትራ የወጋችን በማስመሰል የህዝብን ሆድ ለመብላትና እነሱ ፎቅ በፎቅ ላይ ሲገነቡ መኖሪያ ቤት አሳጥተው ሜዳ የወረወሩትን፣ እነሱ የሰሊጥ እርሻ ለማስፋፋትና ሚሊየነር ለመሆን ከአያት ቅድመአያት ቀዬው ያፈናቀሉትን ምስኪን ዛሬም በደሙ ሥልጣናቸዉን እንዲያቆይላቸው አፈሳና አፈናቸዉን አጡፈዉታል። እንደ ባድመው ጊዜ ሆ ብሎ ተነስቶ ላያፀድቅ አንገቱን የሚሰየፍላቸው ሞኝ ማግኘታቸው ግን ሲበዛ ነው የሚያጠራጥረው። አሁንም ሳሞራ የኑስ ሃያ ሁለት ቢሊዮን ብር በጀት ባስቸኳይ ፀድቆ የጦር መሳሪያ ካልተገዛ ባለን አቅም የትም አንደርስም ሲል በቃሪያ ጥፊ እንዳጮሉት ብላቴና ሲለፈልፍ ተሰምቷል። ስለመከላከያ ሠራዊቱ የተደሰኮረው፣ የተዘፈነው ሁሉ እብድ የያዘው በሶ ሆኖ በነፋስ በኖ ቀረ ማለት ነው?? ዉሸታም ሥርዓት!

“ሲበዛ ማርም ይመራል።” ኢህአህዴግ በዉሸቱ ሊቀጥል አይችልም። “ጥቂት ሰዎችን ሁልጊዜ ማታለል ይቻላል፤ ሁሉንም ሰው ለጥቂት ጊዜ ማታለል ያቻላል፤ ነገር ግን ሁሉንም ሰው ሁልጊዜ ማታለል አይቻልም፤” እንዳለው አብርሃም ሊንከን፣ ኢህአዴግ ሁልጊዜም አታልላችሁዋለሁ ብሎ ካሰበ ራሱ ተታሏል፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ አያውቅም ማለት ነው። ወይም እንደትላንት ለኢሕአዴግ ድጋፍ ወጥቶ በፍቅር አስክሮአቸው፣ በነጋታው በእጥፉ አደባባዩን አጥለቅልቆት ከቅንጅት ጎን ተሰልፎ ያሳበደዉን ሕዝብ አመል ዘንግቶታል ማለት ነው። ከዚያም ተምሮ አለመለወጡ በራሱ በሽተኛነቱን አምኖ፣ እዉነቱን ተናግሮ መድሃኒት ለመፈለግ አለመወሰኑን ይመሰክርበታል። ለዉጥ የህይወት ሕግ ሲሆን በጊዜ፣ ሁኔታና ቦታ ያልተለወጠ ደግሞ ከገፀ ምድር መጥፋቱ አሌ አይባልም።

የኢህአዴግ ዉሸት ከዉድቀት እንጦርጦስ ሊፈጠፍጠው ዥው አድርጎ እየወሰደው ነው። ከ20ኛ ፎቅ ላይ እየወደቀ ሳለ 8ኛ ፎቅ ያሉ ሰዎች “እንዴት ነህ?” ቢሉት፤ “እስካሁን ደህና ነኝ” አለ እንደተባለው ሩሲያዊ እየመሰለኝ መጥቷል። ዉሎ አድሮ የሚሆነው አይታወቅም፣ ሁሌም እንዳማሩ መኖር አይቻልም ።

ቸር እንሰንብት።

ka139693@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule