• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢህአዴግ ዉሸት – እስካሁን ደህና ነኝ ማለት

July 12, 2015 07:18 am by Editor Leave a Comment

እሙሩ ብሪታንያዊ የምርመራ ጋዜጠኛ ኒኮላስ (ኒክ) ዴቪስ የብዕሩ ሞገስ ይደርጅለትና ዕውነት እንዳንናገር፣ ሀቅ እንዳንዘረዝር የሚያደርጉን ሠለስቱ ቀታሊያን ሥህተቶች፣ ሦስቱ ገዳይ ድክመቶች:-

“1) የምንመርጣቸው ርዕሰ ጉዳዮች ዕውነታውን በመሠረታዊ መንገድ የሚያፋልሱት እንዲሆኑ በማድረግ ዋናውን ጭብጥ ማሳት፣

“2) በተደጋጋሚ የምንጠቀምባቸውን ኢተአማኒ፣ አንዳንዴም ፈጽሞ ውሸት፣ የሆኑ ጭብጦች ደጋግመን በመጠቀም ዕውነተኛ ማስረጃዎች እንዲመስሉ ማድረግ፣

“3) ከአካባቢው ህብረተሰብ መካከል ኃይለኛ ጉልበት ያላቸውን ወገኖች የሚያደምቁ ዕሴቶችን የማያቋርጥ አሻራ እንዲኖራቸው ፖለቲካዊና ሞራላዊ ውትወታን ማብዛት፣ ናቸው” ሲል የጣፈው ቀልብ የሚማርክና ለአብነት የሚጠቀስ መንደርደሪያ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ማለፊያ አስተዉሎት ነው መቼም።

ታድያ ይህን የኒኮላስ ዴቪስን ሓቲት ባስታወስኩ ቁጥር በሃሳቤ ወዲያው ደርሶ የሚደቀነው ፀሐዩ መንግሥታችን (ኢህአዴግ) ነው። ዉሸት የኢህአዴግ መለዮ ማንነቱ ሆኗል። ተሳስቶ እዉነት መናገር አልፈጠረበትም፣ ሲያልፍም አይነካካው። እንዲያው ተገዶ ለመናገር ቢገፋፋም ሺህ ዉሸቶች አካቦ፣ ሁልቆ መሳፍርት የሌላቸው የፈጠራ እብለቶች ቀንብቦ ነው። ስለ ምጣኔ ሀብት እድገት፣ ስለህዝብ ኑሮ መሻሻል፣ ስለድንበር ጉዳይ፣ ስለ ሃይማኖት ተቋማት፣ ስለ መለስ ሞት፣ ስለአንዳርጋቸው አፈና፣ ስለ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ስለጋዜጠኞችና ፀሐፍት፣ ለሰላም ማስከበር ሥራ ወደተለያዩ ሀገሮች ስለሚሄዱ የሠራዊት አባላት፣ ስለምርጫ፣ ስለባድመና የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት፣ ስለመተካካት፣ የቱን አንስተን የቱን እንተው? ዉሸት ያልቀላቀለበትን፣ ሐሰት ያልዶለበትን ጉዳይ አስሶ ፈልጎ ማግኘት ዘበት ነው ያሉ ዋሹ አይሰኙም። ይዋሻል። ሎሌዎቹንም ዓይናቸዉን በጨው አጥበው ይዋሹለት ዘንድ ያሰልጥናል፣ ይገራል፣ ያዛል። ማጅራታቸዉን አንቆ ይዞ፣ በፍርፋሪ ሹመትና ጉርሻ አንብዞ፣በሙስና (በስኳር) አፍዝዞ ያስዋሻቸዋል። በሁሉም ትካር (ጉዳይ) ላይ ቅጥፈትን ዋልታ አድርጎ ነው ሃሳብና ድርጊትን የሚቀልሰው። አንዳንዴ ሳስበው፣ የዚህ ሥርዓት ግፈኝነት ምንጩ ከጥላቻ ቀጥሎ በዉሸትና ክህደት ላይ መመስረቱ ነው ብዬ ለማመን እገደዳለሁ። ተቆጠቡም ተናገሩት፣ ገለፁትም ደበቁት ኢትዮጵያዉያን ይህን አመሉን አንጥረው አብጠርጥረው ያውቁታል። “ማወቁንማ እናውቃለን፣ ብንናገር እናልቃለን” ሆነ እንጂ ችግሩ!

የሥነ ልቡና ጠበብት እንደሚያስተምሩን፣ ዉሸት የደካሞች ባህርይ ሲሆን መጨረሻዉም ዉድቀት መሆኑ አያጠራጥርም። ሌላው ሌላው ይቅርና ትላንት ከአለም 46ኛ ከአፍሪካ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፣ አቻ የሌለው የዘመኑን ቴክኒዎሎጂ ታጥቋል፣ ሰው አልባ አውሮፕላን ሰርቷል፣ አለምን ያርበደብዳል ተብሎ ወታደራዊ ትዕይንት ያሳየው የመከላከያን ቀን በድምቀት ያከበረው ሠራዊት፣ መሳሪያዎቹ ሁሉ ጊዜ ያለፈባቸዉና ያረጁ፣ ምንም ጥቃት ለመቋቋም አቅም የሌለው መሆኑን በምሥጢር በተካሄደው የአመራሩ ስብሰባ ላይ ጄኔራል ሳሞራ ያቀረበው ሪፖርት የመንግስታችንን እኩይ ገፅታ በአሳፋሪ ሁኔታ አጋልጦታል። መከላከያ ኦዲት የማይደረግ፣ የህዝብ ሀብት በከፍተኛ ሁኔታ እየተመዘበረ ጎጠኞች ያበጡ የናጠጡ ቱጃሮች የሆኑበት የገለማ የነቀዞች እልፍኝ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው። እድሜ ለአርበኞችና ግንቦት ሰባት ገና አንድ ጥይት ከመተኮሳቸው የመንግሥታችን ጭንብል ተገለጠ።

መንግስታችን አሁንም የልማዱን ይዋሻል። የወጋችን ኤርትራ አይደለችም። የኢህአዴግ የአፈና ሥርዓት ሆድ ያስባሰው ወገን ኢህአዴግን አስወግዶ፣ ዴሞክራሲና ፍትህን ለማስፈን የሚያደረገው ሁለገብ ትግል አካል መሆኑን ነገሮናል። ኤርትራ የወጋችን በማስመሰል የህዝብን ሆድ ለመብላትና እነሱ ፎቅ በፎቅ ላይ ሲገነቡ መኖሪያ ቤት አሳጥተው ሜዳ የወረወሩትን፣ እነሱ የሰሊጥ እርሻ ለማስፋፋትና ሚሊየነር ለመሆን ከአያት ቅድመአያት ቀዬው ያፈናቀሉትን ምስኪን ዛሬም በደሙ ሥልጣናቸዉን እንዲያቆይላቸው አፈሳና አፈናቸዉን አጡፈዉታል። እንደ ባድመው ጊዜ ሆ ብሎ ተነስቶ ላያፀድቅ አንገቱን የሚሰየፍላቸው ሞኝ ማግኘታቸው ግን ሲበዛ ነው የሚያጠራጥረው። አሁንም ሳሞራ የኑስ ሃያ ሁለት ቢሊዮን ብር በጀት ባስቸኳይ ፀድቆ የጦር መሳሪያ ካልተገዛ ባለን አቅም የትም አንደርስም ሲል በቃሪያ ጥፊ እንዳጮሉት ብላቴና ሲለፈልፍ ተሰምቷል። ስለመከላከያ ሠራዊቱ የተደሰኮረው፣ የተዘፈነው ሁሉ እብድ የያዘው በሶ ሆኖ በነፋስ በኖ ቀረ ማለት ነው?? ዉሸታም ሥርዓት!

“ሲበዛ ማርም ይመራል።” ኢህአህዴግ በዉሸቱ ሊቀጥል አይችልም። “ጥቂት ሰዎችን ሁልጊዜ ማታለል ይቻላል፤ ሁሉንም ሰው ለጥቂት ጊዜ ማታለል ያቻላል፤ ነገር ግን ሁሉንም ሰው ሁልጊዜ ማታለል አይቻልም፤” እንዳለው አብርሃም ሊንከን፣ ኢህአዴግ ሁልጊዜም አታልላችሁዋለሁ ብሎ ካሰበ ራሱ ተታሏል፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ አያውቅም ማለት ነው። ወይም እንደትላንት ለኢሕአዴግ ድጋፍ ወጥቶ በፍቅር አስክሮአቸው፣ በነጋታው በእጥፉ አደባባዩን አጥለቅልቆት ከቅንጅት ጎን ተሰልፎ ያሳበደዉን ሕዝብ አመል ዘንግቶታል ማለት ነው። ከዚያም ተምሮ አለመለወጡ በራሱ በሽተኛነቱን አምኖ፣ እዉነቱን ተናግሮ መድሃኒት ለመፈለግ አለመወሰኑን ይመሰክርበታል። ለዉጥ የህይወት ሕግ ሲሆን በጊዜ፣ ሁኔታና ቦታ ያልተለወጠ ደግሞ ከገፀ ምድር መጥፋቱ አሌ አይባልም።

የኢህአዴግ ዉሸት ከዉድቀት እንጦርጦስ ሊፈጠፍጠው ዥው አድርጎ እየወሰደው ነው። ከ20ኛ ፎቅ ላይ እየወደቀ ሳለ 8ኛ ፎቅ ያሉ ሰዎች “እንዴት ነህ?” ቢሉት፤ “እስካሁን ደህና ነኝ” አለ እንደተባለው ሩሲያዊ እየመሰለኝ መጥቷል። ዉሎ አድሮ የሚሆነው አይታወቅም፣ ሁሌም እንዳማሩ መኖር አይቻልም ።

ቸር እንሰንብት።

ka139693@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule