• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው”- ዶ/ር ዲማ ነገዎ

September 6, 2021 07:08 pm by Editor 1 Comment

ዛሬ (ሰኞ) በሸራተን አዲስ እየተከበረ በሚገኘው የኢትዮጵያዊነት ቀን የመወያያ ጽሑፍ ያቀረቡት ዶ/ር ዲማ ነገዎ የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የህዝቦች የተለያዩ የማንነት መገለጫዎች መኖራቸውን የገለጹት ዶ/ር ዲማ እነዚህን ሁሉ አጠቃሎ አንድ ዓይነት አገራዊ ማንነት የሚሰጠን ኢትዮጵያዊነታችን ማንነት ነው ብለዋል፡፡

አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ ማንነት አንድነትን በብዝሀነት አጣምሮ ሁሉንም ህዝብ በእኩልነት የሚያስተናግድ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

አገሪቷ አሁን ያለችበትን ውስብስብ ፈተና እንድትሻር ለማስቻል በህግ ማስከበር እና በሌሎች በሚወሰዱ እርምጃዎች የአገርን አንድነት እና ኢትዮጵያዊነትን እንዳይሸረሽር ጥንቃቄ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ (ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ማስታወሻ፤ የኦሮሞ መብት አቀንቃኝ ነን ለሚሉትና በነፍስ ግድያ ተጠርጥረው በእስር ለሚገኙት ጃዋር መሐመድና በቀለ ገርባ እንዲሁም ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም ካለም ተጭኖብኝ ነው በማለት የግል ብስጭቱን በፖለቲካ ሽፋን የሚያወራው ጸጋዬ አራርሳ የዶ/ር ዲማ ንግግር ኦነጋዊ አስተሳሰብ በኢትዮጵያ ምንም ቦታ የሌለው መሆኑን የሚያመላክት ሆኗል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: dima negeo, Ethiopia, ethiopian identity

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 8, 2021 08:23 am at 8:23 am

    እንደዛሬው ሳይሆን ድሮ ድሮ ሰው በበሬ ሳይሆን በድሮ አረሰ ሲባል ህዝባችን በፍቅር በአንድነት አንድ የአንድን ባህል አክብሮ እንደኖረ ይታወቃል። አሁን ሰለጠን ብለን ሰይጣን ከሆን ወዲህ የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ ለጀሮ የሚቀፉ፤ ለዓይን የሚዘገንኑ መሆናቸውን በሃገርና በዓለም ዙሪያ የሚናፈሱ ወሬዎች ይናገራሉ። የሰው ልጅ ሰልጥኖ ጨረቃን መርገጡ የክፋት ቋት ከመሆን አላዳነውም። እንዲያውም ሰለጠንኩ ባለ ቁጥር ሰንጣቂ ሃሳቦችን እያመነጨ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መላቱምን አበዛ እንጂ። በቅርቡ በስራ ቦታ ፎርም እየተሞላ ጾታ በሚለው ሥፍራ ላይ (Genderless) ከሴትም ከወንድም ያልሆነ ማለት ይመስለኛል የሚል ስመለከት ግራ ገባኝና ቀና ብዬ የማመልከቻውን ባለቤት ስመለከት ሴት መሆኗ ከራስ እስከ እግሮቿ ይናገሯሉ። እግዚኦ እንዲህም አለ እንዴ? አታድርስ በማለት ነገሩ አልፌ የቀን ሥራዬን ቀጠልኩ።
    ታዲያ ዶ/ር ዲማ ነገዎ ከተናገሩት ጋር ይህ ጉዳይ ምን አገናኘው ለምትሉ ረጋ ብላችሁ ሃሳቤን ተከተሉ። የኦሮሞ ህዝብ አቃፊ፤ ሰላምን የሚወድ፤ ያለውን የሚያካፍል፤ ለሌላው የሚያዝን እንደሆነ በመካከሉ በመኖር የማውቀው ስለሆነ አሁን ከደርዘን በላይ ለኦሮሞ ህዝብ ይገደናል እያሉ በውጭም በሃገር ቤትም የሞት ጥሩንባ ከሚነፉት ወገን የሚባለውን አልሰማም። በዚህ አንጻር ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በተለይም በ60 ዎቹ አካባቢ ጀምሮ እልፍ የኦሮሞ ልጆች ለዚህም ለዚያም በአመኑበት ተፋልመዋል። ታስረዋል፤ ተሰደዋል፤ ተገድለዋል፤ ተፈናቅለዋል። አሁን እንሆ ቀደምት የኦሮሞ ህዝብ ነጻነት ታጋዮች ወደ ልቦናቸው ተመልሰው ህዝብን የሚያረጋጋ፤ ወደ አንድነትና መከባበር የሚያመጣ፤ አንድ ለሌላው ተደራሽና ተደጋጋፊ ሃሳቦችን ሲያጋሩ ማየት ልብን ያሞቃል። በአንጻሩ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ ተቀምጠው የሞትና የእልቂት ከበሮ እየመቱ ህዝባችን የሚያተራምስ ነገር ሲሰሩ ማየት ደግሞ በእጅጉ ያሳዝናል። እነዚህ አጥፊ ሃይሎች የኦሮሞ ተወላጆች ብቻ ሳይሆኑ በዘርና በቋንቋ ተሰላፊዎችን ሁሉ ያጠቃልላል። ዘረኝነት የበታችነት ስሜት መግለጫ ነው። ዘረኛ ሰው ሁልጊዜም የደቦ ፓለቲካ ፈላጊ ነው። ያ በመሆኑ ነው 27 ዓመት በደምና በዝርፊያ አጨማልቆ የገዛትን ሃገር እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በማለት ወያኔ ዛሬ የትግራይን ህጻናት በጦርነት እየማገደና በአማራና በአፋር ከአውሬ ባህሪ በማይለይ ሁኔታ አርሶ አደሩን፤ የጋማና የቀንድ ከብቱን በጥይት የሚረፈርፈው። የፓለቲካ እብደት ይሏቹሃል ይህ ነው። ወያኔ እሳት መቆስቆስ ብቻ ሳይሆን እሳት ማቀበልና ማቀጣጠልም ተክኖበታል። ትላንት ተራራን ያንቀጠቀጠ ትውልድ እያለ ይለፍ የነበረው ወያኔ ዛሬ ከተራራ አናት ላይ መሽጎ ከተሞችን ይዘርፋል፤ ያቃጥላል፤ ሊጥና በርበሬ ሳይቀር ወደ መቀሌ ያጋግዛል። ትላንትም ሌቦች ዛሬም የባንክ ዘራፊዎች። የማይድኑ የመከራ ጆኒያዎች።
    በሃሳብና በገንዘብ ድለላ የዛገ ሃሳብ የሚከተሉ የኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች ከወያኔ ጎን ተሰልፈው ሌላውን ወገናቸውን ሲወጉ በ 27 ዓመቱ የወያኔ አገዛዝ በኦሮሞ ህዝብ ላይ የደረሰውን በደል ዘንግተውት አይደለም። እያወቁ አብደው እንጂ። በፈጠራ ታሪክ የሰከሩት እነዚህ የዘር ድውያን ዓለምና አህጉራዊ እይታቸው ከመንደራቸው አይርቅም። ተማሩ አልተማሩ ታጥበው አይጠሩም። ልብ ላለው ሰው ግን ዛሬም ሳንጃ በአፈሙዝ ትላትንም አባረህ በለው፤ ያዘው ጥለፈው የምንለው ለምን ይሆን በማለት ይጠይቅ ነበር። ከነጭና ከዓረብ ጋር ተጎዳኝቶ ህዝብን መጉዳት አረመኔነት ነው። ዛሬ በወለጋ የምንሰማውና የምናየው የዘር ጭፍጨፋ የኦሮሞ ህዝብን የሚወክል ሳይሆን የጥቂት እብዶች የተላላኪነት ተግባር ነው። ይህ ተግባራቸው በጎንደር ዙሪያ በተለይም በጭልጋ የቅማንት አጥፊ ሃይሎች በህበረተሰቡ ላይ ከሚያደርሱት ገመና ጋር ይገናኛል። በተል እኮም በሃሳብም አንድ ነው። ዝርፊያና ግድያ። ሰውን ማሸበር። የሃገሪቱን ሰላም መናጥ። አይ ነጻ አውጪ መሆን ድንቄም ነጻ ታውጣኝ።
    ባጭሩ እውነተኛ የኦሮሞ ልጆች ያኔም ነበሩ ዛሬም አሉ። በነጮቹ ቋንቋ (the silent majority) አንድ ቀን ሆ ብሎ ስለሚነሳ ዛሬ በዘር ፓለቲካ የሚነግድ እብድ የጌሾ ነጋዴዎች ቆም ብለው ቢያስቡ መልካም ነው። ነገርን መዝነው ልክ እንደ ዶ/ር ነገዎ ሃሳብን በሃሳብ ፈትገው ስንዴና ገለባውን በመለየት ለህዝባችን ሰላምና መረጋጋት መትጋቱ ለአሁኑም ሆነ ለወዲያኛው ዓለም ይጠቅማል። ለጥቁር ህዝቦች አንድነት መስራት ከመንደር እይታና የከዘር ፓለቲካ ነጻ ያወጣል። የሰፋ እይታ ተሻጋሪ ሃሳብ ያፈልቃል። ከተንኮልና ከሸር ርቀን ዛሬም የሚያነባውንና ተርቦ የሚያድረውን ወገናችን እንታደግ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule