• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው”- ዶ/ር ዲማ ነገዎ

September 6, 2021 07:08 pm by Editor 1 Comment

ዛሬ (ሰኞ) በሸራተን አዲስ እየተከበረ በሚገኘው የኢትዮጵያዊነት ቀን የመወያያ ጽሑፍ ያቀረቡት ዶ/ር ዲማ ነገዎ የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የህዝቦች የተለያዩ የማንነት መገለጫዎች መኖራቸውን የገለጹት ዶ/ር ዲማ እነዚህን ሁሉ አጠቃሎ አንድ ዓይነት አገራዊ ማንነት የሚሰጠን ኢትዮጵያዊነታችን ማንነት ነው ብለዋል፡፡

አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ ማንነት አንድነትን በብዝሀነት አጣምሮ ሁሉንም ህዝብ በእኩልነት የሚያስተናግድ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

አገሪቷ አሁን ያለችበትን ውስብስብ ፈተና እንድትሻር ለማስቻል በህግ ማስከበር እና በሌሎች በሚወሰዱ እርምጃዎች የአገርን አንድነት እና ኢትዮጵያዊነትን እንዳይሸረሽር ጥንቃቄ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ (ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ማስታወሻ፤ የኦሮሞ መብት አቀንቃኝ ነን ለሚሉትና በነፍስ ግድያ ተጠርጥረው በእስር ለሚገኙት ጃዋር መሐመድና በቀለ ገርባ እንዲሁም ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም ካለም ተጭኖብኝ ነው በማለት የግል ብስጭቱን በፖለቲካ ሽፋን የሚያወራው ጸጋዬ አራርሳ የዶ/ር ዲማ ንግግር ኦነጋዊ አስተሳሰብ በኢትዮጵያ ምንም ቦታ የሌለው መሆኑን የሚያመላክት ሆኗል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: dima negeo, Ethiopia, ethiopian identity

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 8, 2021 08:23 am at 8:23 am

    እንደዛሬው ሳይሆን ድሮ ድሮ ሰው በበሬ ሳይሆን በድሮ አረሰ ሲባል ህዝባችን በፍቅር በአንድነት አንድ የአንድን ባህል አክብሮ እንደኖረ ይታወቃል። አሁን ሰለጠን ብለን ሰይጣን ከሆን ወዲህ የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ ለጀሮ የሚቀፉ፤ ለዓይን የሚዘገንኑ መሆናቸውን በሃገርና በዓለም ዙሪያ የሚናፈሱ ወሬዎች ይናገራሉ። የሰው ልጅ ሰልጥኖ ጨረቃን መርገጡ የክፋት ቋት ከመሆን አላዳነውም። እንዲያውም ሰለጠንኩ ባለ ቁጥር ሰንጣቂ ሃሳቦችን እያመነጨ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መላቱምን አበዛ እንጂ። በቅርቡ በስራ ቦታ ፎርም እየተሞላ ጾታ በሚለው ሥፍራ ላይ (Genderless) ከሴትም ከወንድም ያልሆነ ማለት ይመስለኛል የሚል ስመለከት ግራ ገባኝና ቀና ብዬ የማመልከቻውን ባለቤት ስመለከት ሴት መሆኗ ከራስ እስከ እግሮቿ ይናገሯሉ። እግዚኦ እንዲህም አለ እንዴ? አታድርስ በማለት ነገሩ አልፌ የቀን ሥራዬን ቀጠልኩ።
    ታዲያ ዶ/ር ዲማ ነገዎ ከተናገሩት ጋር ይህ ጉዳይ ምን አገናኘው ለምትሉ ረጋ ብላችሁ ሃሳቤን ተከተሉ። የኦሮሞ ህዝብ አቃፊ፤ ሰላምን የሚወድ፤ ያለውን የሚያካፍል፤ ለሌላው የሚያዝን እንደሆነ በመካከሉ በመኖር የማውቀው ስለሆነ አሁን ከደርዘን በላይ ለኦሮሞ ህዝብ ይገደናል እያሉ በውጭም በሃገር ቤትም የሞት ጥሩንባ ከሚነፉት ወገን የሚባለውን አልሰማም። በዚህ አንጻር ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በተለይም በ60 ዎቹ አካባቢ ጀምሮ እልፍ የኦሮሞ ልጆች ለዚህም ለዚያም በአመኑበት ተፋልመዋል። ታስረዋል፤ ተሰደዋል፤ ተገድለዋል፤ ተፈናቅለዋል። አሁን እንሆ ቀደምት የኦሮሞ ህዝብ ነጻነት ታጋዮች ወደ ልቦናቸው ተመልሰው ህዝብን የሚያረጋጋ፤ ወደ አንድነትና መከባበር የሚያመጣ፤ አንድ ለሌላው ተደራሽና ተደጋጋፊ ሃሳቦችን ሲያጋሩ ማየት ልብን ያሞቃል። በአንጻሩ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ ተቀምጠው የሞትና የእልቂት ከበሮ እየመቱ ህዝባችን የሚያተራምስ ነገር ሲሰሩ ማየት ደግሞ በእጅጉ ያሳዝናል። እነዚህ አጥፊ ሃይሎች የኦሮሞ ተወላጆች ብቻ ሳይሆኑ በዘርና በቋንቋ ተሰላፊዎችን ሁሉ ያጠቃልላል። ዘረኝነት የበታችነት ስሜት መግለጫ ነው። ዘረኛ ሰው ሁልጊዜም የደቦ ፓለቲካ ፈላጊ ነው። ያ በመሆኑ ነው 27 ዓመት በደምና በዝርፊያ አጨማልቆ የገዛትን ሃገር እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በማለት ወያኔ ዛሬ የትግራይን ህጻናት በጦርነት እየማገደና በአማራና በአፋር ከአውሬ ባህሪ በማይለይ ሁኔታ አርሶ አደሩን፤ የጋማና የቀንድ ከብቱን በጥይት የሚረፈርፈው። የፓለቲካ እብደት ይሏቹሃል ይህ ነው። ወያኔ እሳት መቆስቆስ ብቻ ሳይሆን እሳት ማቀበልና ማቀጣጠልም ተክኖበታል። ትላንት ተራራን ያንቀጠቀጠ ትውልድ እያለ ይለፍ የነበረው ወያኔ ዛሬ ከተራራ አናት ላይ መሽጎ ከተሞችን ይዘርፋል፤ ያቃጥላል፤ ሊጥና በርበሬ ሳይቀር ወደ መቀሌ ያጋግዛል። ትላንትም ሌቦች ዛሬም የባንክ ዘራፊዎች። የማይድኑ የመከራ ጆኒያዎች።
    በሃሳብና በገንዘብ ድለላ የዛገ ሃሳብ የሚከተሉ የኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች ከወያኔ ጎን ተሰልፈው ሌላውን ወገናቸውን ሲወጉ በ 27 ዓመቱ የወያኔ አገዛዝ በኦሮሞ ህዝብ ላይ የደረሰውን በደል ዘንግተውት አይደለም። እያወቁ አብደው እንጂ። በፈጠራ ታሪክ የሰከሩት እነዚህ የዘር ድውያን ዓለምና አህጉራዊ እይታቸው ከመንደራቸው አይርቅም። ተማሩ አልተማሩ ታጥበው አይጠሩም። ልብ ላለው ሰው ግን ዛሬም ሳንጃ በአፈሙዝ ትላትንም አባረህ በለው፤ ያዘው ጥለፈው የምንለው ለምን ይሆን በማለት ይጠይቅ ነበር። ከነጭና ከዓረብ ጋር ተጎዳኝቶ ህዝብን መጉዳት አረመኔነት ነው። ዛሬ በወለጋ የምንሰማውና የምናየው የዘር ጭፍጨፋ የኦሮሞ ህዝብን የሚወክል ሳይሆን የጥቂት እብዶች የተላላኪነት ተግባር ነው። ይህ ተግባራቸው በጎንደር ዙሪያ በተለይም በጭልጋ የቅማንት አጥፊ ሃይሎች በህበረተሰቡ ላይ ከሚያደርሱት ገመና ጋር ይገናኛል። በተል እኮም በሃሳብም አንድ ነው። ዝርፊያና ግድያ። ሰውን ማሸበር። የሃገሪቱን ሰላም መናጥ። አይ ነጻ አውጪ መሆን ድንቄም ነጻ ታውጣኝ።
    ባጭሩ እውነተኛ የኦሮሞ ልጆች ያኔም ነበሩ ዛሬም አሉ። በነጮቹ ቋንቋ (the silent majority) አንድ ቀን ሆ ብሎ ስለሚነሳ ዛሬ በዘር ፓለቲካ የሚነግድ እብድ የጌሾ ነጋዴዎች ቆም ብለው ቢያስቡ መልካም ነው። ነገርን መዝነው ልክ እንደ ዶ/ር ነገዎ ሃሳብን በሃሳብ ፈትገው ስንዴና ገለባውን በመለየት ለህዝባችን ሰላምና መረጋጋት መትጋቱ ለአሁኑም ሆነ ለወዲያኛው ዓለም ይጠቅማል። ለጥቁር ህዝቦች አንድነት መስራት ከመንደር እይታና የከዘር ፓለቲካ ነጻ ያወጣል። የሰፋ እይታ ተሻጋሪ ሃሳብ ያፈልቃል። ከተንኮልና ከሸር ርቀን ዛሬም የሚያነባውንና ተርቦ የሚያድረውን ወገናችን እንታደግ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule