• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው”- ዶ/ር ዲማ ነገዎ

September 6, 2021 07:08 pm by Editor 1 Comment

ዛሬ (ሰኞ) በሸራተን አዲስ እየተከበረ በሚገኘው የኢትዮጵያዊነት ቀን የመወያያ ጽሑፍ ያቀረቡት ዶ/ር ዲማ ነገዎ የማንነታችን መገለጫዎች ማሰሪያው ኢትዮጵያዊነት ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የህዝቦች የተለያዩ የማንነት መገለጫዎች መኖራቸውን የገለጹት ዶ/ር ዲማ እነዚህን ሁሉ አጠቃሎ አንድ ዓይነት አገራዊ ማንነት የሚሰጠን ኢትዮጵያዊነታችን ማንነት ነው ብለዋል፡፡

አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ ማንነት አንድነትን በብዝሀነት አጣምሮ ሁሉንም ህዝብ በእኩልነት የሚያስተናግድ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

አገሪቷ አሁን ያለችበትን ውስብስብ ፈተና እንድትሻር ለማስቻል በህግ ማስከበር እና በሌሎች በሚወሰዱ እርምጃዎች የአገርን አንድነት እና ኢትዮጵያዊነትን እንዳይሸረሽር ጥንቃቄ መደረግ አለበት ብለዋል፡፡ (ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ማስታወሻ፤ የኦሮሞ መብት አቀንቃኝ ነን ለሚሉትና በነፍስ ግድያ ተጠርጥረው በእስር ለሚገኙት ጃዋር መሐመድና በቀለ ገርባ እንዲሁም ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም ካለም ተጭኖብኝ ነው በማለት የግል ብስጭቱን በፖለቲካ ሽፋን የሚያወራው ጸጋዬ አራርሳ የዶ/ር ዲማ ንግግር ኦነጋዊ አስተሳሰብ በኢትዮጵያ ምንም ቦታ የሌለው መሆኑን የሚያመላክት ሆኗል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Slider Tagged With: dima negeo, Ethiopia, ethiopian identity

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 8, 2021 08:23 am at 8:23 am

    እንደዛሬው ሳይሆን ድሮ ድሮ ሰው በበሬ ሳይሆን በድሮ አረሰ ሲባል ህዝባችን በፍቅር በአንድነት አንድ የአንድን ባህል አክብሮ እንደኖረ ይታወቃል። አሁን ሰለጠን ብለን ሰይጣን ከሆን ወዲህ የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ ለጀሮ የሚቀፉ፤ ለዓይን የሚዘገንኑ መሆናቸውን በሃገርና በዓለም ዙሪያ የሚናፈሱ ወሬዎች ይናገራሉ። የሰው ልጅ ሰልጥኖ ጨረቃን መርገጡ የክፋት ቋት ከመሆን አላዳነውም። እንዲያውም ሰለጠንኩ ባለ ቁጥር ሰንጣቂ ሃሳቦችን እያመነጨ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መላቱምን አበዛ እንጂ። በቅርቡ በስራ ቦታ ፎርም እየተሞላ ጾታ በሚለው ሥፍራ ላይ (Genderless) ከሴትም ከወንድም ያልሆነ ማለት ይመስለኛል የሚል ስመለከት ግራ ገባኝና ቀና ብዬ የማመልከቻውን ባለቤት ስመለከት ሴት መሆኗ ከራስ እስከ እግሮቿ ይናገሯሉ። እግዚኦ እንዲህም አለ እንዴ? አታድርስ በማለት ነገሩ አልፌ የቀን ሥራዬን ቀጠልኩ።
    ታዲያ ዶ/ር ዲማ ነገዎ ከተናገሩት ጋር ይህ ጉዳይ ምን አገናኘው ለምትሉ ረጋ ብላችሁ ሃሳቤን ተከተሉ። የኦሮሞ ህዝብ አቃፊ፤ ሰላምን የሚወድ፤ ያለውን የሚያካፍል፤ ለሌላው የሚያዝን እንደሆነ በመካከሉ በመኖር የማውቀው ስለሆነ አሁን ከደርዘን በላይ ለኦሮሞ ህዝብ ይገደናል እያሉ በውጭም በሃገር ቤትም የሞት ጥሩንባ ከሚነፉት ወገን የሚባለውን አልሰማም። በዚህ አንጻር ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በተለይም በ60 ዎቹ አካባቢ ጀምሮ እልፍ የኦሮሞ ልጆች ለዚህም ለዚያም በአመኑበት ተፋልመዋል። ታስረዋል፤ ተሰደዋል፤ ተገድለዋል፤ ተፈናቅለዋል። አሁን እንሆ ቀደምት የኦሮሞ ህዝብ ነጻነት ታጋዮች ወደ ልቦናቸው ተመልሰው ህዝብን የሚያረጋጋ፤ ወደ አንድነትና መከባበር የሚያመጣ፤ አንድ ለሌላው ተደራሽና ተደጋጋፊ ሃሳቦችን ሲያጋሩ ማየት ልብን ያሞቃል። በአንጻሩ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ ተቀምጠው የሞትና የእልቂት ከበሮ እየመቱ ህዝባችን የሚያተራምስ ነገር ሲሰሩ ማየት ደግሞ በእጅጉ ያሳዝናል። እነዚህ አጥፊ ሃይሎች የኦሮሞ ተወላጆች ብቻ ሳይሆኑ በዘርና በቋንቋ ተሰላፊዎችን ሁሉ ያጠቃልላል። ዘረኝነት የበታችነት ስሜት መግለጫ ነው። ዘረኛ ሰው ሁልጊዜም የደቦ ፓለቲካ ፈላጊ ነው። ያ በመሆኑ ነው 27 ዓመት በደምና በዝርፊያ አጨማልቆ የገዛትን ሃገር እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በማለት ወያኔ ዛሬ የትግራይን ህጻናት በጦርነት እየማገደና በአማራና በአፋር ከአውሬ ባህሪ በማይለይ ሁኔታ አርሶ አደሩን፤ የጋማና የቀንድ ከብቱን በጥይት የሚረፈርፈው። የፓለቲካ እብደት ይሏቹሃል ይህ ነው። ወያኔ እሳት መቆስቆስ ብቻ ሳይሆን እሳት ማቀበልና ማቀጣጠልም ተክኖበታል። ትላንት ተራራን ያንቀጠቀጠ ትውልድ እያለ ይለፍ የነበረው ወያኔ ዛሬ ከተራራ አናት ላይ መሽጎ ከተሞችን ይዘርፋል፤ ያቃጥላል፤ ሊጥና በርበሬ ሳይቀር ወደ መቀሌ ያጋግዛል። ትላንትም ሌቦች ዛሬም የባንክ ዘራፊዎች። የማይድኑ የመከራ ጆኒያዎች።
    በሃሳብና በገንዘብ ድለላ የዛገ ሃሳብ የሚከተሉ የኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች ከወያኔ ጎን ተሰልፈው ሌላውን ወገናቸውን ሲወጉ በ 27 ዓመቱ የወያኔ አገዛዝ በኦሮሞ ህዝብ ላይ የደረሰውን በደል ዘንግተውት አይደለም። እያወቁ አብደው እንጂ። በፈጠራ ታሪክ የሰከሩት እነዚህ የዘር ድውያን ዓለምና አህጉራዊ እይታቸው ከመንደራቸው አይርቅም። ተማሩ አልተማሩ ታጥበው አይጠሩም። ልብ ላለው ሰው ግን ዛሬም ሳንጃ በአፈሙዝ ትላትንም አባረህ በለው፤ ያዘው ጥለፈው የምንለው ለምን ይሆን በማለት ይጠይቅ ነበር። ከነጭና ከዓረብ ጋር ተጎዳኝቶ ህዝብን መጉዳት አረመኔነት ነው። ዛሬ በወለጋ የምንሰማውና የምናየው የዘር ጭፍጨፋ የኦሮሞ ህዝብን የሚወክል ሳይሆን የጥቂት እብዶች የተላላኪነት ተግባር ነው። ይህ ተግባራቸው በጎንደር ዙሪያ በተለይም በጭልጋ የቅማንት አጥፊ ሃይሎች በህበረተሰቡ ላይ ከሚያደርሱት ገመና ጋር ይገናኛል። በተል እኮም በሃሳብም አንድ ነው። ዝርፊያና ግድያ። ሰውን ማሸበር። የሃገሪቱን ሰላም መናጥ። አይ ነጻ አውጪ መሆን ድንቄም ነጻ ታውጣኝ።
    ባጭሩ እውነተኛ የኦሮሞ ልጆች ያኔም ነበሩ ዛሬም አሉ። በነጮቹ ቋንቋ (the silent majority) አንድ ቀን ሆ ብሎ ስለሚነሳ ዛሬ በዘር ፓለቲካ የሚነግድ እብድ የጌሾ ነጋዴዎች ቆም ብለው ቢያስቡ መልካም ነው። ነገርን መዝነው ልክ እንደ ዶ/ር ነገዎ ሃሳብን በሃሳብ ፈትገው ስንዴና ገለባውን በመለየት ለህዝባችን ሰላምና መረጋጋት መትጋቱ ለአሁኑም ሆነ ለወዲያኛው ዓለም ይጠቅማል። ለጥቁር ህዝቦች አንድነት መስራት ከመንደር እይታና የከዘር ፓለቲካ ነጻ ያወጣል። የሰፋ እይታ ተሻጋሪ ሃሳብ ያፈልቃል። ከተንኮልና ከሸር ርቀን ዛሬም የሚያነባውንና ተርቦ የሚያድረውን ወገናችን እንታደግ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule