• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ እና እንድምታው

August 2, 2016 01:18 am by Editor Leave a Comment

በሰሞነኛው የአዲስ አቤ ቀልድ ልጀምር። ወጣቱ፣ ሱሪ ለመግዛት ወጥቶ አንድ የልብስ ሱቅ ወስጥ ገባ። ባለ ሱቁ ጠየቀው። “የቻይና ይሁንልህ ወይንስ የአውሮፓ ሱሪ?”  ወጣቱም መለሰ። “የለም የለም… የጎንደሩን ሱሪ ነው የምፈልገው።”

እስረኞችን የማስፈታቱ ሰላማዊ ጥያቄ የእብሪት መልስ ሲያገኝ፤  ጨዋታውም ተቀየረ።   “እንዲያውም አናውቅህም። ከህዝብ ጫንቃ ላይ ወረድ” ሲል ነበር የጎንደር ሕዝብ ብረትን ሰብሮ ዙፋኑን የነቀነቀው። “ወንዱን በምርቃና ሴቱን በቃና አደንዝዘን ይዘነዋል!” ያሉት ሕዝብ ከቶውንም እንዳልተዘናጋ አሳየን….  የመናገር እና ሃሳብን ያለፍርሃት የመግለጽ መብትን ህወሃት ሲፈልግ የሚሰጥ ሲያሻው ደግሞ የሚነፍገው የግል ሃብቱ አድርጎ ለ25 አመታት ሰንብቶ ነበር። ይህ መብት በኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አሸብርቆ ጎንደር ላይ ተከበረ። በባህርዳር፣ በደሴ፣ በኦሮምያ፣ በመቀሌ…. ላይም ይቀጥላል..

ከአርባ አመት በፊት የቬትናም ህዝብ ባዕዳን ያነገሱትን አሻንጉሊት መንግስት በሃይል ሲነቀንቀው፤ አሻንጉሊቱ ስርዓት ለሕዝብ እጅ ከመስጠት ውጭ አማራጭ አልነበረውም። የህዝብ ያልነበረው ይህ መንግስት ወደ አመሻሹ ላይ ካመሸገበት የአይጥ ጉድጓድ ሆኖ መግለጫ ሰጠ። እንዲህ ሲል፣

“ስልጣኑን ለህዝብ ለማስረከብ ከንጋት ጀምሮ እየጠበቅኩ ነው።…“

የሰሜኑ ህዝብም ምላሽ የተጠበቀው ነበር፣  “ይህን ለማድረግ ትንሽ ዘገየህ።… የሌለህን ስልጣን እንዴትስ ልታስረክብ ትችላለህ?…“

ይህ ተላላኪ መንግስት ወድቆ የነበረው ከህዝባዊው አመጽ እና እንቢተኝነት በፊት መሆኑን አላስተዋለውም። ስርዓቱ የወደቀ ራሱ ያወጣውን ህግ ራሱ ሲሽረው ነበር። ሕዝብ “መንግስት የለም!” ማለት የጀመረው ለአፋኝ አዋጆች አልንበረከክም ብሎ አደባባይ በወጣ ግዜ ነበር።  ይህ መንግስት የተወገደውም ለዜጋው የመብት ጥያቄ የጥይት ምላሽ በሰጠ ግዜ ነው።

“የዘመናችን ትልቁ ክስተት!”  ብሎታል የኩባው ፊደል ካስትሮ።

ባለፈው እሁድ በጎንደር የታየው የሕዝብ እንቢተኝነትም የዘመናችን ትልቁ ክስተት ነበር። ሕዝብ የተፈጥሮ መብቱን ተነጥቆ በጫንቃው ላይ ተጭኖ የነበረውን ቀንበር ያስወገደበት ክስተት!  ስልጣን የህዝብ እንጂ የጥቂቶች መፈንጫ አለመሆኑ የታየበት ክስተት። በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ወርቃማ አሻራ ጥሎ ያለፈ፤ ለሀገር የፍቅር፣ ለዜጎች የፍትህ እና የህብረት ሃውልትን የተከለ ክስተት። የማይቻል የሚመስለውን ተራራ ደርምሶ የናደ ሃይል ስለነበር ታሪክ ይህንን ሰልፍ ይዘክረዋል።

ግዙፉ የጎንደር ሕዝብ ሰላማዊ ሰልፍ እንደተተናቀቀ፣ የህወሃት መገናኛ ብዙሃን የሆነው ፋና ራዲዮ ሲዘግብ፤

“የጎንደሩ የተቃውሞ ሰልፍ በሰላም ተጠናቀቀ።…” ነበር ያለው። “ጋዜጠኛው” ከምጥ እንደተገላገለች ሴት በረጅም ተነፈሰ።

በስፍራው ያልነበረው መገናኛ ብዙሃን በስፍራው የነበረውን ክስተት ሲደሰኩር፣ ለሰላማዊ ሰልፍ ፍቃድ የተከለከለ ህዝብ በራሱ ፈቃድ መውጣቱን፤ በሰልፉም ላይ እነሱ የከለከሉትን ባንዲራ ብቻ መያዙን ጨምሮ አበሰረ።

ይህንን የዜና እወጃ ያዳመጠው የጎንደር ሕዝብ “ይህን ለማድረግ ትንሽ ዘገየህ። …” ሳይለው አልቀረም። ልክ እንደ አሻንጉሊቱ የቬትናም መንግስት፣ የህወሃት የአፈና ግዜ ማብቃቱን እያረጋገጡት ይመስላል። አንድ ስርዓት መንግስትነቱ የሚያከትመው ራሱ ያወጣውን ህግ ራሱ ሲረግጠው እና ሕዝብም ለሱ አዋጅ ተገዥ አለመሆኑን ሲያሳየው ነው። አላስተዋልነው ይሆናል እንጂ ህወሃት እድሜውን ጨርሶ በባከነ ሰዓት እንደሚንገዳገድ “የልማቱ” ተጠቃሚዎች ሳይቀሩ ነግረውን ነበር። እነ ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እና አበበ ተ/ኃይማኖት (ጆቤ) ከማጀታቸው ወጣ ወጣ ብለው አገሪቱ እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ፣ መንግስት በሚባለው እና በፓርቲ መሃል እንኳን ልዩነት እንደጠፋባቸው ነግረውናል። ይህ ጉዳይ ጻድቃንን ግራ ካጋባው ሌላው ምን ይበል? ጆቤ የህወሃት ሙስና እና የፍትህ እጦት ካስፈራው ተራው ህዝብ ምን ይሰማው? የሚገርመው ነገር፣ እያየነው ያለው ቀውስ  የነ ፃድቃን እና የነ ጆቤ “ሌጋሲ”ም ጭምር መሆኑ ነው።

የጎንደሩ አመጽ ሁለት አበይት ነገሮችን ጥሎልን አልፏል። አንደኛው መተባበር እና መደጋገፍን ማስተማሩ ነው። አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል እንዲሉ፤ በተለይ የኦሮሞ ወገናችን ደም የሁላችንም ደም ነው ማለታቸው የህወሃትን ከፈፍሎ መግዛት እቅድ የሚያፈርስ መፈክር ነበር። የአኙዋክ መገደል ከአማራው መገደል ተለይቶ አለመታየቱን፣ የሲዳማው ሰቆቃ … የሁሉም ወገን ስእቆቃ እንደሆነ … የሚያሳይ ትእይንት ነበር። በማን አለብኝነት የሚጫኑ አዋጆችን መስበር መቻሉ ደግሞ ስልጣን ዛሬ በህዝብ እንጂ በአንባገነኖች እጅ አለመሆኑን አሳይቶናል። ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ ለመብቱ ፈቃድ እንደማያስፈልገው ብቻ ሳይሆን ይልቁንም ጥንት አባቶቹ  በአደራ ያስረከቡትን ባንዲራ ይዞ በመውጣቱም የስርዓቱን ማክተም አሳይቶናል።

የማይነካ የመሰለው ጉልበቱ ሲፈታ፣ የማይሰበር የመሰለው ሃይል ሲሰበር ይህ የመጀመርያው አይደለም። በዘረፉት ሃብት እና በሰራዊታቸው ጉልበት ብቻ እየተማመኑ የገዛ ወገናቸውን ሲበድሉ የኖሩ አንባገነኖች ከቶውንም መቶ አመት ሲቆዩ አላየንም። በአለማችን የተነሱ ብርቱ የሚባሉ አንባገነኖች በህዝብ ሃይል እየተዋረዱ መውደቃቸውን የታሪክ መዛግብት ይመሰክራሉ።

የማያልቅ መንገድ እና የማይነጋ ጨለማ የለም። በአንጻሩ የማይመሽ ቀን የለም። የብዙዎ አንባገነኖች ችግርበ ጉልበታቸው ብቻ በመተማመን ዙፋናቸውን ዘላለማዊ ለማድረግ ማሰባቸው ነው።  በዚህች ተለዋዋጭ አለም ውስጥ ለውጥ  የሰው ልጅ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ግደታም ነው። ዘገምታኛም ይሁን ቅጽበታዊ፣ እኛም በተራችን ለውጥን የምናይበት ወቅት ላይ ደርሰናል።

ይህ ሊሆን ግድ ነው። ጽዋ እስኪሞላ የሚጨመርለትን ሁሉ ይሸከም እና ከሞላ በኋላ መፍሰሱ ሳይንሳዊም፤ ተፈጥሯዊም ህግ ነውና ከአቅሙ በላይ ሲሞላ ሁሉም ነገር ይፈስሳል። ከየአቅጣጫው ሕዝቡን ገፍተው እዚህ አደረሱት። እነሆም የሕዝብን የቁጣ ወላፈን ትላንት በኦሮሞ ወንድሞቻችን፣ ዛሬ ደግሞ በጎንደር አዩት። ነገ በደቡብ፣ ከዚያም በምስራቅ እና በምእራብ ይቀጥላል። ይህ ቁጣ የመጀመርያው እንጂ የመጨረሻው አይደለም።

“የዚህን መንግስት ያህል በህዝብ ክፉኛ የተጠላ ስርዓት በህይወት ዘመኔ አይቼም ሆነ ሰምቼ አላየሁም።” ሲሉ አንድ ከፍተኛ የኢህአኤግ ባለስልጣን ሲናገሩ አድምጫለሁ። ከውስጣዊ ሰዎች  እንደምንሰማው ከሆነ 90 በመቶ የሚሆኑት የኦህዴድ እና የብአዴን አመራር አባላት ከህወሃት ጋር ሆድና ጀርባ ከሆኑ ሰንበትበት ብለዋል፤ የህዝቡ በደል አንገሽግሿቸው ህዝባዊውን አመጽ ለመቀላቀል በመጠባበቅ ላይም ናቸው። በራሱ በአገዛዙ ውስጥ ያሉ ሁለተኛ ረድፈኞች ሳይቀሩ እንደሚመሰክሩት፤ የህወሃት ወንጀል ደርግ ከሰራው ወንጀል እንኳን ሊወዳደር አይችልም። የበደሉን ብዛት እና የዝርፊያውን ግዙፍነት የሚመሰክሩት ሁሉ ይህ ስርዓት በቅርጽ እንጂ በይዘት እንደሌለ ነው እየመሰከሩ ያሉት። “በአሁን ሰዓት በመንግስት ስም የሚነግድ የማፍያ ቡድን እንጂ መንግስት የለም!” ነው ያለው አንድ ከፍተኛ የብአዴን ሰው።

ሕዝቡ ይህንን ሰርዓት ለምን አይጥላው? ሁሉም ስለታፈነ ሕዝብ ነው የሚናገሩት።  አንድ ለአምስት ተጠረንፎ የተያዘ ሕዝብ፣ እስከውስጥ ገመናው በኢህአዲግኛ መስፈርት እየተገመገመ የሚሰቃይ ሕዝብ፣ ሌት ተቀን በሙስና እንደመዥገር እየተበዘበዘ ያለ ሕዝብ። ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል እንኳን ለመጥራት እየተጸየፉ፣ ሀገርን እና ታሪካዊ ባንድራዋን እየጠሉ፣ … እንዴት ሊቆዩ ይችላሉ?

ለችግሮች ሁሉ መፍትሄያቸው ጠመንጃ ነው። የጎንደሩንም ችግር በጠመንጃ ለመፍታት እየመከሩ ይገኛሉ። በመጀመርያ ከህዝቡ መሳርያ መንጠቅ። ከዚያም እንደ በኦሮሞ ወጣቶች እንዳደረግነው በአልሞ ተኳሾች አማጺውን መልቀም ይኖርብናል ሲሉ ዶ/ር ደብረጽዮን መናገራቸው እየተሰማ ነው። ከ500 ያላነሱ የኦሮሞ ወገኖቻችንን ጨርሰው ሲያበቁ፤ እርምጃው ተመጣጣኝ እና ፍትሃዊ ነው ሲሉ ቀለዱብን። ለመሆኑ ከአንድ ሰብዓዊ ፍጡር እንደዚህ አይነት ፍጹም አረመኔያዊ ነገር ይሰማል? የጭካኔ ጣርያው የት ድረስ ነው?…

መገናኛ ብዙሃን ላይ እየወጡ በህዝብ ላይ የሚያላግጡት ነገር ደግሞ እጅግ ያሳምማል።  ለጥያቄዎች ሁሉ አንድ መልስ ነው ያላቸው። መልሱም “ሻዕቢያ” የሚባል ግዑዝ ነገር። የኦሮሞ ሕዝብ ሰቆቃ ይቁም ብለው የተነሱት ወጣቶች በሙሉ “የታጠቁ እና የተደራጁ የሻዕቢያ ቡድኖች ናቸው” ተባልን። የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ያነሱት ወገኖች ሁሉ ያሻዕቢያ ተላላኪዎች እንደሆኑ ነገሩን። የታገልነው ለነጻነታችን እንጂ ትግሬ ለመሆን አይደለም ያሉት ከራሳቸው ውስጥ ያሉ ታጋዮችም የሻዕቢያ መልዕክተኞች ናቸው። የችግሮቻቸው ሁሉ መንስኤው ሻእቢያ ነው። ይህ ሊሆን ይችላል። 10 ሰው የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ይችላል። 100 ሰውም የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ይችላል። 1000 ሰው የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ይችላል። አንድ ሚልየን ህዝብ የሻዕቢያ ተላላኪ ከሆነ ግን ከነጻነት ትግሉ ጀርባ ሻዕቢያ እንዳለ ነው እየነገሩን ያሉት። ፖለቲካን እንደ ማስንቆ እየቃኘ የሚጫወትበትን ህዝብ፣ እነሱ የሚናገሩትን ሁሉ እንደ ስንዴ እየፈለፈለ እንደሚያበጥረው እንኳን አይገነዘቡም።

የምስራቁ ፈላስፋ ኮንፋሽየስ “ትልቁ እውቀት የራስን የድንቁርና መጠን ጠንቅቆ ማወቅ ነው“ ይለናል። ይህንን ሁሉ ህዝብ የሻዕቢያ ተላላኪ ሲሉ በድፍረት መናገራቸው የድንቁርናቸው መጠን ምን ያህል የወረደ መሆኑን ያመላክተናል። “በወልቃይት ጠገዴ ስቃይ እና እስር ይብቃ!“ የሚለው መፈክር የሻዕቢያ ከሆነ ሻዕቢያ ለወልቃይት ህዝብ መብት በመነሳቱ ሊወገዝ ሳይሆን ይልቁንም ሊወደስ ይገባዋል። እንደ ጣዕረ-ሞት እየተከተለ እንቅልፍ የሚነሳቸው ሻዕቢያ “ለሱዳን የተሸጠው ድንበራችን ባስቸኳይ ይመለስ!“ የሚል መልዕክት ይዞ ህዝብን ማሰለፍ ከቻለ ወዳጅ እንጂ ጠላት አይሆንም።

ሁሌም ህዝብን ማታለል የሚችሉ ይመስላቸዋል። ትላንት የተጫወቱበትን ካርታ ሳይቀይሩ ዛሬም ለመጫወት ይሞክራሉ። በኮብልስቶን፣ በአነስተኛና ጥቃቅን … ወዘተ የተያዘ ወጣት ሁሉ፣ በደል ያላመረረው፣ ንቀት ያላስቆጣው መሆኑን አሁን ማረጋገጥ ይችላሉ።

ካሁን በኋላ እነሱ ሊያደርጉ የሚችሉት አንድ አስፈሪ ነገር ቢኖር፤  የትግራይን ህዝብ ከወንድሙ የአማራና ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ደም ማቃባት ብቻ ነው። እዚህ ላይ ነው ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ የሚገባው። የትግራይ ህዝብ የዚህ አናሳ ቡድን እዳ ከፋይ መሆን የለበትም። የትግራይ ሕዝብም በቡድን-በቡድን ተከፋፍሎ የሚሰቃይ መሆኑን መረዳት ይኖርብናል። የተገመገመ፣ የሚገመገም እና ለት ተቀን የሚገመግም ቡድን!  ይህ ሕዝብም ነጻ መውጣት አለበት።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule