• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች የሚጠቀሙበት የፖለቲካ ፎርሙላ

May 2, 2014 12:50 am by Editor Leave a Comment

ፎርሙላ (ቀመር)

አንድ የጎሳ ፖለቲካ ማለት በመጀመርያ ቤተሰብህን የተለዩ ፍጥረት እንደሆኑ መስበክ መጀመር ማለት ነው። እነርሱ የተለዩ መሆናቸውን በደንብ ማሰብ ሲጀምሩልህ ደግሞ በመቀጠል የሰፈርህን እና የወንዝህን ሰዎች ልዩ መሆናቸውን በሚገባ መስበክ ነው። የሰፈርህን ሰዎች ልዩ እና የተለዩ መሆናቸውን ስትነግር ግን የአንተ ቤተሰብ ጋር እንደማይደርሱ ግን ደግሞ ከቤተሰብህ ዝቅ ባለ መልክ የተለዩ መሆናቸውን ወትውታቸው። በመጨረሻ አንተ የቤተሰብህም ሆነ የሰፈርህ ብቸኛ አለቃ መሆንህን ትነግራቸውና ከሰፈርህ ማዶ ያሉ ሰዎች ደግሞ እርኩስ፣ የተለዩ፣ ጥንትም አባቶችን ሲበድሉ እንደነበሩ የሆነ ያልሆነ ተረታ ተረት እየነገርክ ተራራ የሚያህል ጥላቻ እንዲያድርባቸው አድርግ።

ፎርሙላ (ቀመር) ሁለት 

ከእዚህ በኃላ በሰፈርህ ሰዎች እና ማዶ ባሉ ሰፈር ሰዎች መካከል በአንተ የጦር አበጋዝነት ጦርነት እንዲከፈት አድርግ። ጦርነቱን ልትከፍት ስትል ትልቅ ችግር ሊገጥምህ ይችላል። ለምሳሌ ለዘመናት በክፉም  ሆነ በደግ አብረው የኖሩ ሰዎች ናቸው እና ከአንተ ሰፈርም ሆነ ከማዶ ሰፈር ያሉ የበሰሉ ሽማግሌዎች ወይንም አስታራቂዎች ነገሩን እንዳያበርዱብህ ተጠንቀቅ። ”የፍቅር ዘመቻ” ብሎ በሰፈርህ መካከል ዘፈን ልዝፈን፣ ፍቅርን ልዝራ፣ ብሎ የሚነሳ ሀገር የወደደው ዘፋኝ ካለ ቀድመህ በቻልከው ነገር በማማሰያም ሆነ በብረት ምጣድ ደብድበህ አባረው። የስም ማጥፋት ናዳ ልቀቅበት። ዘፋኝ እና የሃይማኖት ሰዎች አንድ ናቸው። ሁለቱም ዓለም አንድ ነው፣ ምናምን እያሉ አላማህን ያደናቅፉብሃል። ‘ቀንድ ቀንዳቸውን’ በላቸው። ከሃይማኖት በፍቅር የተሰበሰቡ ማሕበራት ካሉም እግር ከእግር እየተከታተልክ አድክማቸው። ከቻልክ ዝጋቸው።

የሃይማኖት እና የኪነት ሰዎች ብቻ አይደሉም የዓላማህ ጠላቶች ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮች ሁሉ ቀድመው የሰፈርህን ሰዎች ከማዶ ሰፈር ሰዎች ጋር አብረው እንዲኖሩ ሊሰብኩ ይችላሉ እና ፈጥነህ ከእየቤታቸው ፖሊስ ልከህ ልቀማቸው! ያዛቸው! ማዕከላዊ ወስደህ አጉራቸው! ነግሬሃለሁ ጉድህን ይዘከዝኩታል። በሰፈርህ እና በማዶ ሰፈር መካከል ልታጋጭ ያሰብከውን ጉድ ሁሉ ለሀገር ይነዙልሃል። ይህ ብቻ አይደለም ቤተሰብህ ከሰፈርህ ሰው የተለየ አለመሆኑን፣ አንተም በቤተሰብህ እና በሰፈርህ ሰዎች ላይ መንገስ እንደማይገባህ፣ ሌላ ‘በሰፈርህ እና በማዶ ሰፈር ሰዎች መካከል ልዩነት የለም በፍቅር እንኑር’ የሚል ሰው መንገስ አለበት ብለው ለሕዝቡ ይነግሩብሃል። እናም ፍጠን! እሰራቸው!ልክህን አሳያቸው!።

ፎርሙላ (ቀመር) ሶስት 

ይህንን ሁሉ ከጨረስክ በኃላ አንተ እና ቤተሰብህ ጥንቱንም የተለያችሁ ፍጥረቶች መሆናችሁን በተለይ አዲስ ለሚወለዱት ልጆች እየሰበክ በሰፈርህ ሰዎች እና በማዶ ሰፈር ሰዎች መካከል  እረጋ ብለህ ቡናህን  እየጠጣህ ጦርነት እንዲከፈት ማዘዝ ትችላለህ። ተቀናቃኝህን ሁሉ እንደሆነ እስር ቤት ሰደሃቸዋል። የዘፋኙንም ስም ከማዶ ሰፈር ካሉ መሰሎችህ ጋር ሆነህ ስሙን አስጠፍተሃል። ከእዚህ በኃላ ማዶ ያሉ መሰሎችም ሆኑ አንተ አንድ አይነት ጫወታ ላይ ገባችሁ ማለት ነው። መንደር ከመንደር እየቆጠረ ህዝቡ ሲባላ እነርሱ በውስኪ አንተም በኮኛክህ መዝናናት ፈታ! ማለት ነው።

ፎርሙላ (ቀመር) አራት 

ጦርነቱ  ሲደረግ አንተ በሰፈርህ ሰዎች ላይ ንጉስ  ሆነህ ”ካለእርስዎ አመራር የት እንደርሳለን?” ስትባል ጀነን፣ ጎምለል ማለት ነው። አሁን ጥሩ ጊዜ መጣልህ የሀብት መጠንህ ይጨምራል። ምክንያቱም የሰፈርህንም ሆነ የማዶ ሰፈር ሰዎችን ገንዘብ ወደ ኪስህ እየከተትክ አለምህን መቅጨት ትችላለሃ!። በመካከል ታድያ ሥራ አትፍታ እዛኛው ማዶ የራሱ የሰፈሩን ሰዎች የመሰሉ ሰዎች ሰው እየላክ ”የእዝህኛው ሰፈር ሰዎች እናንተን ይጠላሉ ተጠንቀቁ!” ማለት ለእራስህም ሰፈር ሰዎች እንዲሁ ተመሳሳይ ነገር ጣል ማድረግ።ግጭቱ በደንብ አልጋጋልም  ካለህ ቀድሞ ከመቶ ዓመት በፊት የነበሩ የአንተ ሰፈር ሰዎች ”የሰሩት ኃጢያት አለ” የሚል የሐሰት ታሪክ ማዶ ሰፈር ካለው መሰልህ ጋር በሚስጥር ተነጋግረህ  ”ማስታወሻ” በሚል ስም የቂም ሐውልቶችን በየሰፈሩ መደርደር በተለይ ሴቶች ስሜታቸው የሚነካ የሰውነት ክፍል ለምሳሌ ጡት እና ጣት የመሳሰሉ የሰውነት ክፍሎች ተቆርጠው ነበር ብለህ ሃውልት መስራት። ያኔ ወጪ ወራጁ ”ህም! ድሮ እንዲህ አድርገዋል አሉ” እያለ ከንፈር እንዲነክስ ማገዝ። አዎ ማገዝ።

ፎርሙላ (ቀመር) አምስት 

የሰፈርህ እና የማዶ ሰፈር ሰዎች አንድ መሆናቸውን ሊሰብኩ የሚነሱ ከመከከልህ ከተነሱ ወይንም ደግሞ የእዚህ አይነት አስተሳሰብ አላቸው የምትላቸውን ገልሰቦችም ሆነ የሃይማኖት ሰዎች ማኅበራት በሙሉ ተለጣፊ ስም መስጠት “አጎብዳጆች፣ አሸባሪዎች፣ የሰፈሬን ሰዎች ሰላም የሚያናጉ፣ ዥንጉርጉር አብዮት ሊያስነሱ ያቀዱ” እያልክ ማሰር እና መግደል።

መደምደምያ 

በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት እና በባህር ማዶ እና በሀገር ቤት በጎሳቸው ላይ እራሳቸውን ያነገሱ እና ኢትዮጵያዊነትን የሚያጥላሉ ሁሉ ሲጠቀሙበት የሰነበቱት የጎሳ ፖለቲካ ፎርሙላ  ይሄው ነው። ኢትዮጵያ በእናንተ ዘመን አልተፈጠረችም እንዴት እንደምትኖር ታውቅበታለች። ግዴላችሁም ይህች ሀገር አምላክ አላት። በኢትዮጵያዊነት ላይ ጥላቻ ያደረበት ለጥላቻውም አስር ምክንያት ቢደረድር በመንግሥትነትም ሆነ በተቃዋሚነት ቢሰየም፣ የቂም ሐውልቶችን እንደ አሸን ቢያፈላም ሆነ በነፃነት ስም ከመቶ ዓመት በፊት ይህ ትውልድ ላልኖረበት ዘመን እየጠቀሰ ለስልጣን መወጣጫ ሊጠቀም ቢሞክርም  ከህዝብ ፍርድ አያመልጥም። አሁንም ግዴላችሁም ይህች ሀገር ጎሳ እና ብሔር የማያውቁ ለሰው ልጆች በሙሉ የሚፀልዩ ቅዱሳን እና የሚሰማቸው አምላክም አሏት። አሁንም ኢትዮጵያዊነት የጋራ መጠለያችን ነው። የጎሳ ፖለቲካ ፎርሙላ-ቀመራችሁ  ተነቅቶበታል።

ጉዳያችን

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule