• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዲያስጶራዎቻችን

November 30, 2016 06:55 am by Editor 1 Comment

ዲያስፖራ (ዲያስጶራ) የሚለው ቃል ትርጉም ‹‹ብትን /የተበተነ›› ወይም በአጪር አነጋገር ከትውልድ አገሩ ውጭ ተበታትኖ ያለ ሕዝብ ማለት ነው፡፡ በዚህ ትርጓሜ ከኢትዮጵያ መቶ ሜትርም ይሁን አንድ ሺሕ ማይል ይራቅ ከድንበር ማዶ ያለ ሁሉ ዲያስፖራ ነው፡፡ የምንገኝበት አገር፣ የትምህርት ደረጃችን፣ የወጣንበት መንገድ፣ ሃይማኖታችን ወይም ብሔራችን ዲያስፖራ ከመሆን (ከመበትን) አያድነንም፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው በአውሮፕላንም ይሁን በመርከብ፣ ጥገኝነት ጠይቆም ይሁን አግብቶ፣ ፊደል የቆጠረም ይሁን ፕሮፌሰር የሆነ፣ እስላምም ይሁን ክርስቲያን፣ ዐማራም ይሁን ኦሮሞ ወይም ጉራጌ ወይም ሌላ ከድንበር ወጥተን ወደ ሌላ ሉዓላዊ አገር ከገባን ተበትነናል ማለት ነው፡፡ የምንገኝበት አገርም መመዘኛ አይደለም፡፡ አፍሪካ፣ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ኤዥያ ወይም ኦሽኒያ መሆናችን ምንም ልዩነት አያመጣም፡፡ አንድ ሰው አሥመራ፣ ናይሮቢ፣ ካይሮ፣ ዱባይ፣ ፓሪስ፣ ዲሲ፣ ሲድኒ ወይም አንድ የዓለማችን ከተማ ላይ ቢሆን ከኢትዮጵያ ተነቅሏል፤ ተበትኗል፤ ልዩነት የለውም፡፡ አፍሪካ የሚኖር ጀግና ወይም አሜሪካ የሚኖር ደፋር የሚያስብል መስፈርትም የለም፡፡ በእኛ አገር ዲያስፖራ መሆንን እንደ ምርቃት (ጥሩ እድል) የመቁጠር እሳቤ አለ፡፡ ከአገር ወጥቶ መበተን እርግመት ወይም ምርቃት ነው የሚለውን ለጊዜው እንተወውና ስለብትኑ ማኅበረሰባችን ፖለቲካ ትንሽ እንበል፡፡

ብትን ወገን (ዲያስፖራ) በፖለቲካው ረገድ እስካሁን የተዋጣለት ሥራ የሠሩት የኢዝራኤል ዲያስፖራዎች ናቸው፡፡ ኢዝራኤል የምትባለዋ አገር የተመሠረተችው በዲያስፖራዎች ነው፡፡ ለነገሩ አይሁዶች ከአገራቸው ሲርቁ የበለጠ ስለአገራቸው የሚያስጨንቅ ነገር አላቸው፡፡ ቀድም ባሉ በብሉይ ዘመናት ዮሴፍ በወድሞቹ ተሸጦ ወደ ግብጽ አገር በተሰደደ ጊዜ ለወገኖቹ የሚሆን ጥሪት ያጠራቅም እንደነበር ማስታወስ ይቻላል፤ ሙሴም ቢሆን ጊዜው ከመርዘሙ ውጭ የተበተኑ ወገኖቹን ወደ አገሩ መልሷል፡፡ 

የእኛ አገር የዲያስፖራ ማኅበረሰብ ከቁጥሩ አንጻር ካየነው ከዚህ ግባ የሚባል ለአገር ፋይዳ ያለው ውጤት እስካሁን ማምጣት አልቻለም፡፡ ያ ማለት ግን አይችልም ማለት አይደለም፡፡ በዲያስፖራው ማኅበረሰብ ያሉ የአንዳንድ ችግሮች ከተስተካከሉ ለውጥ ማምጣት የማይቻልበት ምንም ዓይነት ምክንያት አይኖርም፡፡ የዲያስፖራው ማኅበረሰብ በሰለጠነ አገር እየኖረ የሰለጠነ የውይይት ባሕል ማዳበር ከፍተኛ ችግር ይታይበታል፡፡ በዚህ ምስኪን ብትን ማኅበሰረብ ውስጥ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ቢኖሩም ወደ ዲሞክራሲ የሚደረገውን የአገር ቤት ትግል ውጭ ባለው ጥገኛ እንዲሆን የተደከመው ድካም እና ዐማራውን ሕዝብ ‹‹በአንድነት ኃይልነት›› መድቦ ማሞኘት ሕዝባችን ከባድ ዋጋ እያስከፈለው ነው፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ድርጅቶችና ማኅበራት (ከአፍሪካ እስከ አውሮፓና አሜሪካ) ከጥቂት ግለሰቦች የመኖሪያ መንገድ (Livelihood) ብሎም ግለሰባዊ ዝና (ፌም) ማግኛነት ወደ ትክክለኛ ዓላማቸው መመለስ ካልቻሉ ወደ ነጻነት የምናደርገው ጉዞ መራዘሙ አይቀርም፡፡ ጥይት በጮኸበት ቦታ ሁሉ ከእግዚአብሔር መላዕክ ቀድሞ መድረሱም ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ይመስለኛል፡፡

(ይህ አስተያየት የተሰጠው ጠቅለል ተደርጎ ለብዙዎች ድርጅቶች መሆኑ ልብ ይባል፤ የሰለጠነ ውይይት ለማድረግ የማትፈልጉ ሰዎች ከእኔ ጋ ጓደኝነታችሁ ያቆማል፤ ዝርዝር ጉዳዮችን ወደፊት ይዤ ለመምጣት እሞክራለሁ፤ እንደ ግለሰብ እንጅ እንደ ድርጅት አቋም የለኝም)

ምንጭ: Muluken Tesfaw Facebook


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    December 11, 2016 09:27 pm at 9:27 pm

    ሙሉቀን ተስፋው! አንተም “ዲያስፖራ” ከምትለው ኢትዮጵያዊ ከመቀላቀለህ በቀር በ25 ዓመቱ ኢህዴግን ለመቀየር ከሚደረገው ትገል አንፅር 25 ዓመት ብቅ ጥለም ካሉት ግለሶቦች የተለየህ አይደለህም። ዛሬ አንተም ጸጉረ ልዉጥ ከመሆንህ ዉጭ የምትገፋው ሃሳብ ፍራሽ አዳሽ ከመሆን አላለፈም። ብዙዎቹ አንተን መሰሎች ብቅ ከማለታቸው ደፍረታቸው “አስተማሪ” ሆነው መታበያቸው ነው። ከእነዚህ ዉሰጥ አንዱ በ 2005 /1997 መርጫ በኋላ ውደ “Dኢያስፕራነት” የተቀላቀለው “ወጣቱ” ጃዋር መሀመድ አንዱ ነው። ጃዋር ሙሃመድ ደግሞ በወጣት ምላሱ ማንነቱን ወዲያዉኑ ለብልቦ ያቃጠለ የ ዘማናችን “ፖለቲካ ተንታኝ” ነው። ፍየል ከመደረሱ ቅጠል መበጠሷ እንዲሉ ሙሉቀን ተሰፋዉና ጃዋአር መሃመድ በመሰምማማተም ይሁን ባለመሰማማት በሚዲያዊና ብበፌስ ቡኩ ኢንተርቪው ተደራጊ ጓዴኛሞች መሆናቸው በኮንኒስፓሪስ ቲዎሪ እይታ መሬት ላይ የሚታይ ሃቅ ነው። ተመሳሳይ ላባ ያላቸው ወፎች አብረው ይበራ! በርቱ እነ ሙሉቀን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule