• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዲያስጶራዎቻችን

November 30, 2016 06:55 am by Editor 1 Comment

ዲያስፖራ (ዲያስጶራ) የሚለው ቃል ትርጉም ‹‹ብትን /የተበተነ›› ወይም በአጪር አነጋገር ከትውልድ አገሩ ውጭ ተበታትኖ ያለ ሕዝብ ማለት ነው፡፡ በዚህ ትርጓሜ ከኢትዮጵያ መቶ ሜትርም ይሁን አንድ ሺሕ ማይል ይራቅ ከድንበር ማዶ ያለ ሁሉ ዲያስፖራ ነው፡፡ የምንገኝበት አገር፣ የትምህርት ደረጃችን፣ የወጣንበት መንገድ፣ ሃይማኖታችን ወይም ብሔራችን ዲያስፖራ ከመሆን (ከመበትን) አያድነንም፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው በአውሮፕላንም ይሁን በመርከብ፣ ጥገኝነት ጠይቆም ይሁን አግብቶ፣ ፊደል የቆጠረም ይሁን ፕሮፌሰር የሆነ፣ እስላምም ይሁን ክርስቲያን፣ ዐማራም ይሁን ኦሮሞ ወይም ጉራጌ ወይም ሌላ ከድንበር ወጥተን ወደ ሌላ ሉዓላዊ አገር ከገባን ተበትነናል ማለት ነው፡፡ የምንገኝበት አገርም መመዘኛ አይደለም፡፡ አፍሪካ፣ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ኤዥያ ወይም ኦሽኒያ መሆናችን ምንም ልዩነት አያመጣም፡፡ አንድ ሰው አሥመራ፣ ናይሮቢ፣ ካይሮ፣ ዱባይ፣ ፓሪስ፣ ዲሲ፣ ሲድኒ ወይም አንድ የዓለማችን ከተማ ላይ ቢሆን ከኢትዮጵያ ተነቅሏል፤ ተበትኗል፤ ልዩነት የለውም፡፡ አፍሪካ የሚኖር ጀግና ወይም አሜሪካ የሚኖር ደፋር የሚያስብል መስፈርትም የለም፡፡ በእኛ አገር ዲያስፖራ መሆንን እንደ ምርቃት (ጥሩ እድል) የመቁጠር እሳቤ አለ፡፡ ከአገር ወጥቶ መበተን እርግመት ወይም ምርቃት ነው የሚለውን ለጊዜው እንተወውና ስለብትኑ ማኅበረሰባችን ፖለቲካ ትንሽ እንበል፡፡

ብትን ወገን (ዲያስፖራ) በፖለቲካው ረገድ እስካሁን የተዋጣለት ሥራ የሠሩት የኢዝራኤል ዲያስፖራዎች ናቸው፡፡ ኢዝራኤል የምትባለዋ አገር የተመሠረተችው በዲያስፖራዎች ነው፡፡ ለነገሩ አይሁዶች ከአገራቸው ሲርቁ የበለጠ ስለአገራቸው የሚያስጨንቅ ነገር አላቸው፡፡ ቀድም ባሉ በብሉይ ዘመናት ዮሴፍ በወድሞቹ ተሸጦ ወደ ግብጽ አገር በተሰደደ ጊዜ ለወገኖቹ የሚሆን ጥሪት ያጠራቅም እንደነበር ማስታወስ ይቻላል፤ ሙሴም ቢሆን ጊዜው ከመርዘሙ ውጭ የተበተኑ ወገኖቹን ወደ አገሩ መልሷል፡፡ 

የእኛ አገር የዲያስፖራ ማኅበረሰብ ከቁጥሩ አንጻር ካየነው ከዚህ ግባ የሚባል ለአገር ፋይዳ ያለው ውጤት እስካሁን ማምጣት አልቻለም፡፡ ያ ማለት ግን አይችልም ማለት አይደለም፡፡ በዲያስፖራው ማኅበረሰብ ያሉ የአንዳንድ ችግሮች ከተስተካከሉ ለውጥ ማምጣት የማይቻልበት ምንም ዓይነት ምክንያት አይኖርም፡፡ የዲያስፖራው ማኅበረሰብ በሰለጠነ አገር እየኖረ የሰለጠነ የውይይት ባሕል ማዳበር ከፍተኛ ችግር ይታይበታል፡፡ በዚህ ምስኪን ብትን ማኅበሰረብ ውስጥ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ቢኖሩም ወደ ዲሞክራሲ የሚደረገውን የአገር ቤት ትግል ውጭ ባለው ጥገኛ እንዲሆን የተደከመው ድካም እና ዐማራውን ሕዝብ ‹‹በአንድነት ኃይልነት›› መድቦ ማሞኘት ሕዝባችን ከባድ ዋጋ እያስከፈለው ነው፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ድርጅቶችና ማኅበራት (ከአፍሪካ እስከ አውሮፓና አሜሪካ) ከጥቂት ግለሰቦች የመኖሪያ መንገድ (Livelihood) ብሎም ግለሰባዊ ዝና (ፌም) ማግኛነት ወደ ትክክለኛ ዓላማቸው መመለስ ካልቻሉ ወደ ነጻነት የምናደርገው ጉዞ መራዘሙ አይቀርም፡፡ ጥይት በጮኸበት ቦታ ሁሉ ከእግዚአብሔር መላዕክ ቀድሞ መድረሱም ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ይመስለኛል፡፡

(ይህ አስተያየት የተሰጠው ጠቅለል ተደርጎ ለብዙዎች ድርጅቶች መሆኑ ልብ ይባል፤ የሰለጠነ ውይይት ለማድረግ የማትፈልጉ ሰዎች ከእኔ ጋ ጓደኝነታችሁ ያቆማል፤ ዝርዝር ጉዳዮችን ወደፊት ይዤ ለመምጣት እሞክራለሁ፤ እንደ ግለሰብ እንጅ እንደ ድርጅት አቋም የለኝም)

ምንጭ: Muluken Tesfaw Facebook


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    December 11, 2016 09:27 pm at 9:27 pm

    ሙሉቀን ተስፋው! አንተም “ዲያስፖራ” ከምትለው ኢትዮጵያዊ ከመቀላቀለህ በቀር በ25 ዓመቱ ኢህዴግን ለመቀየር ከሚደረገው ትገል አንፅር 25 ዓመት ብቅ ጥለም ካሉት ግለሶቦች የተለየህ አይደለህም። ዛሬ አንተም ጸጉረ ልዉጥ ከመሆንህ ዉጭ የምትገፋው ሃሳብ ፍራሽ አዳሽ ከመሆን አላለፈም። ብዙዎቹ አንተን መሰሎች ብቅ ከማለታቸው ደፍረታቸው “አስተማሪ” ሆነው መታበያቸው ነው። ከእነዚህ ዉሰጥ አንዱ በ 2005 /1997 መርጫ በኋላ ውደ “Dኢያስፕራነት” የተቀላቀለው “ወጣቱ” ጃዋር መሀመድ አንዱ ነው። ጃዋር ሙሃመድ ደግሞ በወጣት ምላሱ ማንነቱን ወዲያዉኑ ለብልቦ ያቃጠለ የ ዘማናችን “ፖለቲካ ተንታኝ” ነው። ፍየል ከመደረሱ ቅጠል መበጠሷ እንዲሉ ሙሉቀን ተሰፋዉና ጃዋአር መሃመድ በመሰምማማተም ይሁን ባለመሰማማት በሚዲያዊና ብበፌስ ቡኩ ኢንተርቪው ተደራጊ ጓዴኛሞች መሆናቸው በኮንኒስፓሪስ ቲዎሪ እይታ መሬት ላይ የሚታይ ሃቅ ነው። ተመሳሳይ ላባ ያላቸው ወፎች አብረው ይበራ! በርቱ እነ ሙሉቀን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule