• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ“ጃሃዳዊ ሐረካት” ዘጋቢ ፊልም መዘዝ!

February 11, 2013 03:14 am by Editor 4 Comments

“ጀሃዳዊ ሐረካት” ዘጋቢ ፊልም “በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ከሃሳብ ያለፈ እቅድ አላቸው” የተባሉት ተጠርጣሪ አሸባሪዎችን ገመና አንጠርጥሮ ሊያሳየን መሆኑን ሞቀ ደመቅ ደመቅመቅ ያለው የኢቲቪ ማስታወቂያ ልባችን አንጠልጥሎት ከርሟል ። ሳምንት በደመጽና በምስል በለፈፉትና በናኙት ማስታወቂያ የሙሰሊማን የመፍትሄ አፈላላጊ ኰሚቴ አባላት “አሸባሪ” አካሄድ በተጨባጭ መረጃ እንደሚያሳዩን የነገሩን የመንግሰት መገናኛ ብዙሃንን የተለመደ ስራ የማውቀው ሳይቀር ነፈሴ በአንገቴ እሰክትወጣ ጉጉት አሳድሮብኛል። ይህ መሰሉ ስሜት ለጊዜው ምንጩ ከየት እንደሆነ ባውቀውም ስሜቴን ተቆጣጥሬ በሰአቱ ደረስኩ፡፡ ተመሳሳይ ስሜት አድሮባቸው እንደሁ በሚል እዚህ ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውንን እየደወልኩ ስሜታቸውን መጠየቅ ያዝኩ! (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)::

ጸሐፊውን በዚህ አድራሻ ማግኘት ይቻላል:   nsirak@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Damtew Demeke says

    February 11, 2013 08:41 am at 8:41 am

    it is stupid of the so cold Ethiopian bully weyanes

    Reply
  2. ብስራት says

    February 11, 2013 04:22 pm at 4:22 pm

    በዚህ ጀሀዳዊ ሐረካት ላይ የታየው ከላይ ባለው ምስል ላይ ፊት ለፈት የቀረበው ሰው የኔ ቤተሰብ ነው ( እስማኤል አሰፋ ወይም በቤት ስሙ ወንድም አለም) ፍቅሩን እንጂ ክፋቱን በህይወቴ አላየሁም ፡፡ ምንም እንኳን እሱ ሙስሊም ቢሆንም እና ቤተሰባችን ክርስትያን ቢሆንም ማንም ግን ማንንም ገፍቶ አይደለም ክፉ እንኳን ተነጋግሮ አያውቅም፡፡ የክርስቲያን በዓል ሲሆን አብረን ያለንን ተካፍለን በልተን ተጫውተን ነው የምናሳልፈው፡፡ አሁንም ቢሆን ያቀረቡት ነገር እጅግ ውሸት እና እጅግ ከእውነት የራቀ መሆኑን ለማወቅ የማንንም ማረጋገጫ አልፈልግም፡፡ ወንድም አለም አሁንም እጅግ የምንወድህ ቤተሰቦችህ ነን፡፡ ከኛ ስለተለየህ አዝነናል እጅግም ተደናግጠናል፡፡ አይዞህ ወንድማችን አባታችን፡፡ ይሄ ውሸት እና የሌለብህን ነገር የለጠፉብህ ክፉዎች እስኪነቀሉ በትእግስት ጠብቅ አብረንህ ነን፡፡ እጅግ እንወድሀለን!!

    Reply
  3. ሕሊና ብርሃኑ says

    February 11, 2013 06:32 pm at 6:32 pm

    “ጂሃዳዊ ሃረካት” የተባለውን የመንግሥት የፕሮፓጋንዳ ፊልም፣ እኔም ረጋ ብዬ ተመልክቼዋለሁ። ሃገርና ዜጋን ሁሉ፣ ባጠቃላይ ኢትየጵያን በሙሉ የሚያዋርድ ሰነድ ነው።

    በጨለማው ቤት የሚወርድባቸው ስቃዩና መዓቱ አነሰ ብሎ፣ ምርመራውን ራሱን ባደባባይ ያወጣ መንግሥት በዓለም ላይ ያለም አይመስለኝም። ያደባባይ ፍርድ ቤት ክንውን ይሆን እንደሆን እንጂ! ይህ ሁለት ሶስት ጊዜ አንድን ሰው የመግደል የናላ በሽተኞች /psychopaths / ሱስ ነው።
    እንደዚህ ዓይነቶቹን፣ ሥልጣን ያሰከራቸውን ፍጡሮች ፣ ናላ የሌላቸው፣ የርህራሄ ስሜት ድንቁርና በሽተኞች /psychopaths/ናቸው ይላሉ፣ የስነ ልቦና ምርምሮች፣።
    Exploring the minds of psychopaths and dictators:-
    http://www.psychologytoday.com/blog/engineering-the-brain/201106/the-mind-dictator

    ስለሆነም ፣ የሃገር ወዳዶች፣ የፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው፣ ከሁሉም በፊት መሰረት የሚያደርገው ሰብዓዊነት እስከሆነ ድረስ፣ እውነትን ለማወቅ ሰብዓዊነትን መሰረት ያላደረገ „መረጃ“ ወዲያም ወዲህ ሳይገለባባጥ፣ ህሊናቸው ሊቀበል አይገባም።
    /”The End justifies the Means” /”ከየትም አምጪው ዱቄቱን ፍጪው” ፣ የሚባለው ነገር፣ ምን ጊዜም ቢሆን ሰብዓዊ ዘይቤ ሊሆን ስለማይችል፣ የአምባገነኖችን ፖሊስና የፍርድ ቤቶቹን ተረት ወደ ጎን መተው ብቻ ሳይሆን፣ ለህሊና ፍርድ የሚቀርብን ፋይልንም እንኳን ወድያውኑ ዘግተን ለስቃይ ከተዳረገው ሰው ጋር መቆም አለብን፣ ነው የምለው።
    -የጠላቴ ጠላት ወዳጄ- የሚባለው ተንኮል ለሰብዓዊነት ስለማይሰራ፣ ወይንም በሌላ አማርኛ፣ “ቀንድ ካወጣ ሰይጣን ጋር ተባብሮ ጠላቱን የሚታገል“ ራሱ ሰይጣን እንጂ ፣ ምንጊዜም ቢሆን መላክ ሊሆን ስለማይችል፣ በስቃይ ላይ የተገኘን „መረጃ“፣ እንደዚህ ሊሆን ይችላል፣ ላይሆን ይችላል፣ እያልን፣ ፍሬ ከርስኪ ውስጥ ባንገባ መልካም ይመስለኛል።

    ይልቅ፣ ስለ እዚህ ዓይነቱ ስቃይ ባለሙያዎች የሚሉትን እያገላበጥን፣ የሚፈጸመውን ወንጀል በህሊናችን እያሰብን፣ የሰብዓዊነት የረቀቀ የመንፈስ አንድነታችንን ብንገልጽላቸው እኛንም የበለጠ ሰብዓዊነት ተሰምቶን ወደፊት እንራምዳለን! እንዳው ለምሳሌ ያህል ምን ምን ዓይነት ገጽታና መዘዝ ይህ ስቅይ እንዳለው ይህን ሰነድ ብንመለከተው አንዳንድ ነገር መረዳት እንችላለን ፥http://samvak.tripod.com/torturepsychology.html

    ይህችን ዓለማችንን ዛሬ ከግጭት ወደ ግጭት እያሰጠማት ያመጣው ጣጣ አንዱም፣ የ -”ከየትም አምጪው ዱቄቱን ፍጪው” – ዓይነት አመለካከት ነው። በኔ አስተያየት፣ የሞተው ቢን ላደን ራሱ፣ ከመቃብሩ ወጥቶ፣ በኢህአዴግ ናላቢስ ገራፊዎች/psychopaths/ ተገዶ መንግስት ልገለብጥ መጣሁ፣ ቢል እንኳን፣ የርሱ አክራሪነት ክርክር ውስጥ ሳይሆን የምገባው፣ እንደ ክርስቲያንም ሆነ እንደሰላማዊ ሙዝሊም ወይንም እንደማንኛውም ሰብዓዊ ሰላማዊ ሰው፣ የናላቢሱ መንግስት ኢሰብዓዊነት ጉዳይ ውስጥ ነው ።

    ሌላው መቼም፤ ዛሬ ዓለም የገባችበት የሃይማኖት አክራሪነት፣ የሙዝሊምም ሆነ የክርስቲያን ወይንም ሌላ፣ እንደ ኢትዮጵያ ማህበረሰብ ውስጥ፣ ሁለቱም ሃይማኖቶች በስፋት በቆዩበት ሃገር፣ ተከታይ ለማግኘት የማይገለብጡት ድንጋይ እንደማይኖር፣ እንኳን ለፖለቲካ ተዋናይ ቀርቶ፣ ለማንም ግልጽ ነው። እናም ይህ ስለሆነ መንግሥትን በቁጥጥር ያስገባቸውን ዜጎቹን የማሰቃየት ነጻ ሰርተፊኬት ይሰጠዋል ማለት ነው !!!???? ለነገሩማ ለዚህ ነበር አያሌ የሰብዓዊ ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች በየጊዜው የተደነገጉት። ያው የስምምነቶቹ „ቄሱም ፓፓሱም ሼኩም“ ይረጋግጧቸዋል እንጂ! ጉዋንታናሞንንም አይተናል! የማን ሆነሽ ትባረኪያለሽ ነው!

    ለነገሩማ፣ እናንሳው ካልን ደግሞ፣ እነዚህን፣ በሁሉም በኩል ያሉትን አክራሪዎች በቀዳማዊነት በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ የሚመግቡት፣ እነማን ናቸው? ራሳቸው የሜሪካንና የሳውዲ ባለጸጎች መሆናቸው ያደባባይ ምስጢር ነው። ያልካዒዳ መዋቅር ውስጥ የሚረጨው ሃብትም፣ ከየት እንደሚመጣ ዊኪ ሊኪስ አንድ ሰሞን አዳባባይ አውጥቶታል፤ የሳውዲ ባለጸጎች! የኢትዮጵያን ገበሬና ደሃ ዜጋ በያለበት የሚያፈናቅሉት። ለማያውቋቸው ይታጠኑ እያልን፤ የኢትዮጵያውንም እግዜር ይወቀው፣ በደፈናው ማለት ይሻላል! የሳውዲ ባለጸጎች እራሱ ኢህአዲግ ጉያ ውስጥም አሉና።

    ስለሆነም ፥ ይልቅ የኢህዴግን ተረት ትተን፣ ዛሬ በጀግንነትና በዘርም ሆነ በጥቃቅን የሆድ ጥቅም፣ ሳይከፋፈሉ በአንድነት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ለመብታቸው፣ ለመብታችን በመቆም የሚታገሉት የሙዝሊም ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን፣ አርአያነት በማስተዋል፣
    “ድምጻችን ይሰማ !” መሪዎቻችን ይፈቱ፣
    የሚሉትን ያህል፣ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ይፈቱ!
    እውነት! እውነቱም ይሰማ ! እውነቱ ሃገራችንን ዛሬ የሚያስተዳድሩት የእጅ አዙር ቅኝ ገዥዎች ናቸው!
    አንድ ህዝብ ነን ! አንድ ህዝብ ነን ! ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ !!!
    ብለን እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ ሃገር ወዳድ የሆን ሁሉ ድምጻችንን ከፍ አድርገን ለሰብዓዊነት ና ለነፃ ኢትዮጵያ እንጩህ ! ከተኛንበት በአእምሮም በተግባርም ከዳር እስከዳር እንነሳ !!!
    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

    Reply
  4. nwba says

    February 14, 2013 10:46 am at 10:46 am

    Nonsense….. how can Muslims build an Islamic state where more than half of the people and all it needs for a power is belong to other religious group. Have you heard of a Muslim country even having 3/4th of the whole population and having Islamic or the other way and having christian state? NOT POSSIBLE. This is politics!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule