• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመሪዎች እምባ

May 17, 2015 04:15 am by Editor Leave a Comment

ከስም ልጀምር፣ የዛሬ ወጣቶች በተለይ ዘፋኞች ስማቸው በመጠኑ ተቆርጦ ወይም አንሶ ሲጠሩ እየሰማን ነው፤ ቴዎድሮስ – ቴዲ ብዙ ባያስከፋም ተያይዘው የቀጠሉት ዘፋኞች ግን እስከ አባታቸው ስለሚያሳንሱት ኢትጵያዊ ስም መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ የሆነብኝ ጊዜ አለ። እስቲ አሁን ጃህ ሉድ አጥሮ ነው ወይስ ተቆርጦ ቻቺ፣ ጃኪ፣ ጂጂ፣ አቢ፣ ኢሚ፣ ዮሲ፣ ጃኪ-ጎሲ፣ ሚሊ፣ ሚኪ፣ ዮኒ፣ … ልተዋቸው።

እንደውነቱ ከሆነ ይህ በፊትም እንዳለ የሚጠቁሙ ማስረጃዎች አሉ አጼ ቴዎድሮስ (መይሳው) መዩ ይባሉ ነበር። ገብርዬም ስማቸው አጥሮ ነው ገብርዬ የሆኑት፣ ኃይለሥላሴም ኃይሌ፣ መንግሥቱም መንጌ ተብለዋል። መለስን መሌ ሲባሉ ባልሰማም ሊባልላቸው ይችል ነበር። በረከት ቤኪ፣ ተፈራ ተፌ … መባላቸውን ግን ሰምቻለሁ። የኃይለማርያም ደሳለኝ ስም ረዥም ነው መቆረጥ ይገባዋል፤ ኃይሌ ሊባል ይቻል ነበር፤ ግን ኃይሌ ለሳቸው እንደ ረዥም ኮት አያምርባቸውም። ቢያምርስ ምን ኃይል አላቸውና ኃይሌ ይባሉ?

የለቅሶ ነገር ሲነሳ ደግሞ “ዋይ ዋይ ሲሉ” በማለት አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ ያፈሰሰው እንባ የማንንም አንጀት የሚያላውስ ነበር። ነጋሶም የፍርድ መዛባትን፣ የሕዝብ ውርደትን፣ የህልውና መደፈርን አይተው ደጋግመው በአደባባይ አልቅሰዋል። የነጋሶም እንባ በቀልድ አልፈሰሰችም፤ ሆድ ማገላበጥዋ አልቀረም። ነጋሶ መሪ ነበሩ፤ ከኢትዮጵያ መሪዎች ያለቀሱ እሳቸው ብቻ አይደሉም አጼ ቴዎድሮስም አልቅሰዋል፤ ፈርተው ተሰድበው ተገምግመው አልነበረም ያለቀሱት፤ አንድ ሊያደርጓት የጣሩላት አገርን መጨረሻ ሳያዩ በነጭ ወታደሮች ተከበው የመጨረሻ ሰዓታቸው መቃረቡን ሲያውቁት፤ የዚች አገር ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን? ብለው ነበር ያለቀሱት። የዛሬ ውድቀታችን፣ የዛሬ ለቅሶአችን፣ የዛሬ ስደታችን፣ የዛሬ መታረዳችን ያን ጊዜ ታይቷቸው ነበር ያለቀሱት። ሰላሙን ሊያስከብሩለት፣ መብቱን ሊያስጠብቁለት፣ አንድ ሊያደርጉት የተነሱለትን ሕዝብ በትነውት መሞታቸው ነበር ያስለቀሳቸው።

ጃንሆይም አልቅሰዋል፤ ያስለቀሳችው ግን ሃምሳ ዓመት ከኖሩበት ቤተ መንግሥት በመውጣታቸው፣ ከተከበረው ዙፋናቸው በመውረዳቸው አልነበረም፤ እንደውም «… ለአገር በጎ አስባችሁ ከተነሳችሁ፣ የአገርን ጥቅም ከራስ ጥቅም ማስቀደም አይቻልም፤ እኛ እስካሁን አገራችንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል፤ አሁን ተራው የኛ ነው ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ …» በማለት ነበር ቤተ መንግሥቱን የለቀቁት፤ በኋላ ግን በእስር በቆዩበት ጊዚያት አገራቸው በምን አይነት ሰዎች እጅ እንደወደቀች ሲገነዘቡ ያ ሁሉ ከውጪ ጠላት ያደረጉት ትንቅንቅ፣ ለነጻነት ያደረጉት ተጋድሎ፣ ለሥልጣኔ ያደረጉት ጥረት፣ … እንዲህ ከንቱ ሲቀር አገሪቱ አስከፊ አደጋ ውስጥ እንደምትወድቅ ገብቷቸው ነበር ያለቀሱት። ለሕዝቡ ነበር ያነቡት።

አብዮታዊው መሪ መንግሥቱ ኃ/ማርያምም አስራ ሰባት ዓመታት ሳይተኙ፣ ሳይስቁ፣ አብዮታዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት፣ ዳር ድንበርዋን ለመጠበቅ፣ አገራቸው ተቆርሳ እንዳትወሰድ ከውስጥና ከውጪ ጠላት ለመከላከል ያደራጁት ያነቁት የሚተማመኑበት ጦር ፈርሶ እንደጎርፍ መንገዱን ሞልቱ ሲሄድ በአንቦ አቅጣጫ በሚገኝ አንድ ተራራ አናት ላይ ወጥተው ድንጋይ ላይ ቁጭ ብለው ጦሩን ቁልቁል እያዩ ነበር ያለቀሱት፤ የሀገራቸው መጪ ዕድል አስከፊ ውድቀት እየታያቸው ነበር ያነቡት።

የሁሉም እንባ አላግባብ የፈሰሰ አልነበረም፤ ከመቆርቆር ከመቆጨት ምንም ማድረግ ካለመቻል የመነጨ ነበር። ይህ ደግሞ ምስክር የሚያስፈልገው፣ ማስረጃ የሚጎተትለት አይደለም፤ ጠቀመም ጎዳ የሁሉንም ታሪክ ሥራቸው በይፋ ያስረዳል። ለዚህ ጽሁፍ ያነሳሳኝ ኃይለማርያም ዓይን ስር ቁርዝዝ ብላ የወረደችው እንባ ናት። እንደውነቱ ጉንጫቸውን ሰንጥቃ ባትወርድም ያው እንባ ናትና እንደመሪ እንባ ልቆጥራት አስቤ ነበር፤ ግን እሷንስ ቢሆን ለምን አለቀሷት ብዬ ሳስብ የባሰ ንድድ አለኝ። እንደዚች አይነት የምታቅለሸልሽ አስቀያሚ እንባ ዕድሜዬን ሙሉ አይቼ አላውቅም። ለነገሩ እንኳን እንባቸው ሳቃቸውንም ያምራል ብሎ የሚከራከር ያለ አይመስለኝም።

ዋናው ነገር ግን ይሄ አይደለም ለምን አለቀሱ ነው? ጥያቄው እንዴ! እንዴት አያለቅሱም በደቡብ አፍሪካ የተቃጠሉት ወገኖቻቸው አይደሉም እንዴ! ምን ማለትህ ነው። ባህር እየሰመጠ የሚሞተው ወጣት አያሳዝናቸውም እንዴ! ሰሞኑንስ እንደመስዋዕት በግ የታረዱት ወገኖቻቸው አይደሉም እንዴ! ሌላም ሌላም ልትሉ ትችሉ ይሆናል። የኃይለማርያም ለቅሶ ግን በዚህ አይደለም፤ ግምገማ በሚባል ፈሊጥ እየታዘዙ ከሚመሩባት ወንበር ተሽቀንጥረው እንደሚወረወሩ የሚያመላክት ዘለፋና ስድብ ስለደረሰባቸው ነው። ሌሎችን በዚችው ጥበብ እሳቸውም አባረው ያውቃሉ፤ ያቺ ቀን ለሳቸውም በጣም ቅርብ መሆንዋ ስለተሰማቸው ነበር ያነቡት (ማንባት እንኳን አትባልም)። ብዙዎች ለምን ደም አያለቅሱም ይበላቸው ከማለት ውጪ ከንፈር ይመጡላቸዋል ብዬ አላስብም፤ እራሳቸውም ቢሆኑ ጥርስ ከማፋጨትና ጸጉር ከመንጨት በቀር የሚሉት ይኖራል ተብሎ አይገመትም።

የእንባን ነገር ካነሳሁ አይቀር ጠ/ሚንስትሩን ምክር መክሬ ልሰናበት። ጠ/ሚንስትር ሆይ! ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በይቅርታም ሆነ ነገርን አለዝበው የመውረጃዎን ጊዜን አበላሽተዋል። ካሁን በኋላም ተሰድጄ እኖራለሁም ብለው አያስቡ። ያንንም አጥተዋል። የጠቅላይ ሚንስትርነቱንም ሥልጣን ይዘው መቀመጥ ካሁን በኋላ የህልም እንጀራ ነው። የሥራ ጊዜዎን ወይም መጠቀሚያነትዎን በአግባቡ ጨርሰዋል። ማድረግ የሚገባዎ ቢኖር ረዥም የማልቀሻ ጊዜ ስለሚጠብቅዎ እንባ ቁጠባ በማድረግ ዓይንዎትን መጠበቅ ብቻ ነው። ኖሮም አላማረበት «ከሞጨሞጨ ዓይን የጠፋ ይሻላል» ካሉም የራስዎ ጉዳይ ግምገማውን ያቅልልዎ።

ወለላዬ 

welelaye2@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule