• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመሪዎች እምባ

May 17, 2015 04:15 am by Editor Leave a Comment

ከስም ልጀምር፣ የዛሬ ወጣቶች በተለይ ዘፋኞች ስማቸው በመጠኑ ተቆርጦ ወይም አንሶ ሲጠሩ እየሰማን ነው፤ ቴዎድሮስ – ቴዲ ብዙ ባያስከፋም ተያይዘው የቀጠሉት ዘፋኞች ግን እስከ አባታቸው ስለሚያሳንሱት ኢትጵያዊ ስም መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ የሆነብኝ ጊዜ አለ። እስቲ አሁን ጃህ ሉድ አጥሮ ነው ወይስ ተቆርጦ ቻቺ፣ ጃኪ፣ ጂጂ፣ አቢ፣ ኢሚ፣ ዮሲ፣ ጃኪ-ጎሲ፣ ሚሊ፣ ሚኪ፣ ዮኒ፣ … ልተዋቸው።

እንደውነቱ ከሆነ ይህ በፊትም እንዳለ የሚጠቁሙ ማስረጃዎች አሉ አጼ ቴዎድሮስ (መይሳው) መዩ ይባሉ ነበር። ገብርዬም ስማቸው አጥሮ ነው ገብርዬ የሆኑት፣ ኃይለሥላሴም ኃይሌ፣ መንግሥቱም መንጌ ተብለዋል። መለስን መሌ ሲባሉ ባልሰማም ሊባልላቸው ይችል ነበር። በረከት ቤኪ፣ ተፈራ ተፌ … መባላቸውን ግን ሰምቻለሁ። የኃይለማርያም ደሳለኝ ስም ረዥም ነው መቆረጥ ይገባዋል፤ ኃይሌ ሊባል ይቻል ነበር፤ ግን ኃይሌ ለሳቸው እንደ ረዥም ኮት አያምርባቸውም። ቢያምርስ ምን ኃይል አላቸውና ኃይሌ ይባሉ?

የለቅሶ ነገር ሲነሳ ደግሞ “ዋይ ዋይ ሲሉ” በማለት አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ ያፈሰሰው እንባ የማንንም አንጀት የሚያላውስ ነበር። ነጋሶም የፍርድ መዛባትን፣ የሕዝብ ውርደትን፣ የህልውና መደፈርን አይተው ደጋግመው በአደባባይ አልቅሰዋል። የነጋሶም እንባ በቀልድ አልፈሰሰችም፤ ሆድ ማገላበጥዋ አልቀረም። ነጋሶ መሪ ነበሩ፤ ከኢትዮጵያ መሪዎች ያለቀሱ እሳቸው ብቻ አይደሉም አጼ ቴዎድሮስም አልቅሰዋል፤ ፈርተው ተሰድበው ተገምግመው አልነበረም ያለቀሱት፤ አንድ ሊያደርጓት የጣሩላት አገርን መጨረሻ ሳያዩ በነጭ ወታደሮች ተከበው የመጨረሻ ሰዓታቸው መቃረቡን ሲያውቁት፤ የዚች አገር ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን? ብለው ነበር ያለቀሱት። የዛሬ ውድቀታችን፣ የዛሬ ለቅሶአችን፣ የዛሬ ስደታችን፣ የዛሬ መታረዳችን ያን ጊዜ ታይቷቸው ነበር ያለቀሱት። ሰላሙን ሊያስከብሩለት፣ መብቱን ሊያስጠብቁለት፣ አንድ ሊያደርጉት የተነሱለትን ሕዝብ በትነውት መሞታቸው ነበር ያስለቀሳቸው።

ጃንሆይም አልቅሰዋል፤ ያስለቀሳችው ግን ሃምሳ ዓመት ከኖሩበት ቤተ መንግሥት በመውጣታቸው፣ ከተከበረው ዙፋናቸው በመውረዳቸው አልነበረም፤ እንደውም «… ለአገር በጎ አስባችሁ ከተነሳችሁ፣ የአገርን ጥቅም ከራስ ጥቅም ማስቀደም አይቻልም፤ እኛ እስካሁን አገራችንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል፤ አሁን ተራው የኛ ነው ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ …» በማለት ነበር ቤተ መንግሥቱን የለቀቁት፤ በኋላ ግን በእስር በቆዩበት ጊዚያት አገራቸው በምን አይነት ሰዎች እጅ እንደወደቀች ሲገነዘቡ ያ ሁሉ ከውጪ ጠላት ያደረጉት ትንቅንቅ፣ ለነጻነት ያደረጉት ተጋድሎ፣ ለሥልጣኔ ያደረጉት ጥረት፣ … እንዲህ ከንቱ ሲቀር አገሪቱ አስከፊ አደጋ ውስጥ እንደምትወድቅ ገብቷቸው ነበር ያለቀሱት። ለሕዝቡ ነበር ያነቡት።

አብዮታዊው መሪ መንግሥቱ ኃ/ማርያምም አስራ ሰባት ዓመታት ሳይተኙ፣ ሳይስቁ፣ አብዮታዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት፣ ዳር ድንበርዋን ለመጠበቅ፣ አገራቸው ተቆርሳ እንዳትወሰድ ከውስጥና ከውጪ ጠላት ለመከላከል ያደራጁት ያነቁት የሚተማመኑበት ጦር ፈርሶ እንደጎርፍ መንገዱን ሞልቱ ሲሄድ በአንቦ አቅጣጫ በሚገኝ አንድ ተራራ አናት ላይ ወጥተው ድንጋይ ላይ ቁጭ ብለው ጦሩን ቁልቁል እያዩ ነበር ያለቀሱት፤ የሀገራቸው መጪ ዕድል አስከፊ ውድቀት እየታያቸው ነበር ያነቡት።

የሁሉም እንባ አላግባብ የፈሰሰ አልነበረም፤ ከመቆርቆር ከመቆጨት ምንም ማድረግ ካለመቻል የመነጨ ነበር። ይህ ደግሞ ምስክር የሚያስፈልገው፣ ማስረጃ የሚጎተትለት አይደለም፤ ጠቀመም ጎዳ የሁሉንም ታሪክ ሥራቸው በይፋ ያስረዳል። ለዚህ ጽሁፍ ያነሳሳኝ ኃይለማርያም ዓይን ስር ቁርዝዝ ብላ የወረደችው እንባ ናት። እንደውነቱ ጉንጫቸውን ሰንጥቃ ባትወርድም ያው እንባ ናትና እንደመሪ እንባ ልቆጥራት አስቤ ነበር፤ ግን እሷንስ ቢሆን ለምን አለቀሷት ብዬ ሳስብ የባሰ ንድድ አለኝ። እንደዚች አይነት የምታቅለሸልሽ አስቀያሚ እንባ ዕድሜዬን ሙሉ አይቼ አላውቅም። ለነገሩ እንኳን እንባቸው ሳቃቸውንም ያምራል ብሎ የሚከራከር ያለ አይመስለኝም።

ዋናው ነገር ግን ይሄ አይደለም ለምን አለቀሱ ነው? ጥያቄው እንዴ! እንዴት አያለቅሱም በደቡብ አፍሪካ የተቃጠሉት ወገኖቻቸው አይደሉም እንዴ! ምን ማለትህ ነው። ባህር እየሰመጠ የሚሞተው ወጣት አያሳዝናቸውም እንዴ! ሰሞኑንስ እንደመስዋዕት በግ የታረዱት ወገኖቻቸው አይደሉም እንዴ! ሌላም ሌላም ልትሉ ትችሉ ይሆናል። የኃይለማርያም ለቅሶ ግን በዚህ አይደለም፤ ግምገማ በሚባል ፈሊጥ እየታዘዙ ከሚመሩባት ወንበር ተሽቀንጥረው እንደሚወረወሩ የሚያመላክት ዘለፋና ስድብ ስለደረሰባቸው ነው። ሌሎችን በዚችው ጥበብ እሳቸውም አባረው ያውቃሉ፤ ያቺ ቀን ለሳቸውም በጣም ቅርብ መሆንዋ ስለተሰማቸው ነበር ያነቡት (ማንባት እንኳን አትባልም)። ብዙዎች ለምን ደም አያለቅሱም ይበላቸው ከማለት ውጪ ከንፈር ይመጡላቸዋል ብዬ አላስብም፤ እራሳቸውም ቢሆኑ ጥርስ ከማፋጨትና ጸጉር ከመንጨት በቀር የሚሉት ይኖራል ተብሎ አይገመትም።

የእንባን ነገር ካነሳሁ አይቀር ጠ/ሚንስትሩን ምክር መክሬ ልሰናበት። ጠ/ሚንስትር ሆይ! ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በይቅርታም ሆነ ነገርን አለዝበው የመውረጃዎን ጊዜን አበላሽተዋል። ካሁን በኋላም ተሰድጄ እኖራለሁም ብለው አያስቡ። ያንንም አጥተዋል። የጠቅላይ ሚንስትርነቱንም ሥልጣን ይዘው መቀመጥ ካሁን በኋላ የህልም እንጀራ ነው። የሥራ ጊዜዎን ወይም መጠቀሚያነትዎን በአግባቡ ጨርሰዋል። ማድረግ የሚገባዎ ቢኖር ረዥም የማልቀሻ ጊዜ ስለሚጠብቅዎ እንባ ቁጠባ በማድረግ ዓይንዎትን መጠበቅ ብቻ ነው። ኖሮም አላማረበት «ከሞጨሞጨ ዓይን የጠፋ ይሻላል» ካሉም የራስዎ ጉዳይ ግምገማውን ያቅልልዎ።

ወለላዬ 

welelaye2@yahoo.com

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule