• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመሪዎች እምባ

May 17, 2015 04:15 am by Editor Leave a Comment

ከስም ልጀምር፣ የዛሬ ወጣቶች በተለይ ዘፋኞች ስማቸው በመጠኑ ተቆርጦ ወይም አንሶ ሲጠሩ እየሰማን ነው፤ ቴዎድሮስ – ቴዲ ብዙ ባያስከፋም ተያይዘው የቀጠሉት ዘፋኞች ግን እስከ አባታቸው ስለሚያሳንሱት ኢትጵያዊ ስም መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ የሆነብኝ ጊዜ አለ። እስቲ አሁን ጃህ ሉድ አጥሮ ነው ወይስ ተቆርጦ ቻቺ፣ ጃኪ፣ ጂጂ፣ አቢ፣ ኢሚ፣ ዮሲ፣ ጃኪ-ጎሲ፣ ሚሊ፣ ሚኪ፣ ዮኒ፣ … ልተዋቸው።

እንደውነቱ ከሆነ ይህ በፊትም እንዳለ የሚጠቁሙ ማስረጃዎች አሉ አጼ ቴዎድሮስ (መይሳው) መዩ ይባሉ ነበር። ገብርዬም ስማቸው አጥሮ ነው ገብርዬ የሆኑት፣ ኃይለሥላሴም ኃይሌ፣ መንግሥቱም መንጌ ተብለዋል። መለስን መሌ ሲባሉ ባልሰማም ሊባልላቸው ይችል ነበር። በረከት ቤኪ፣ ተፈራ ተፌ … መባላቸውን ግን ሰምቻለሁ። የኃይለማርያም ደሳለኝ ስም ረዥም ነው መቆረጥ ይገባዋል፤ ኃይሌ ሊባል ይቻል ነበር፤ ግን ኃይሌ ለሳቸው እንደ ረዥም ኮት አያምርባቸውም። ቢያምርስ ምን ኃይል አላቸውና ኃይሌ ይባሉ?

የለቅሶ ነገር ሲነሳ ደግሞ “ዋይ ዋይ ሲሉ” በማለት አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ ያፈሰሰው እንባ የማንንም አንጀት የሚያላውስ ነበር። ነጋሶም የፍርድ መዛባትን፣ የሕዝብ ውርደትን፣ የህልውና መደፈርን አይተው ደጋግመው በአደባባይ አልቅሰዋል። የነጋሶም እንባ በቀልድ አልፈሰሰችም፤ ሆድ ማገላበጥዋ አልቀረም። ነጋሶ መሪ ነበሩ፤ ከኢትዮጵያ መሪዎች ያለቀሱ እሳቸው ብቻ አይደሉም አጼ ቴዎድሮስም አልቅሰዋል፤ ፈርተው ተሰድበው ተገምግመው አልነበረም ያለቀሱት፤ አንድ ሊያደርጓት የጣሩላት አገርን መጨረሻ ሳያዩ በነጭ ወታደሮች ተከበው የመጨረሻ ሰዓታቸው መቃረቡን ሲያውቁት፤ የዚች አገር ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን? ብለው ነበር ያለቀሱት። የዛሬ ውድቀታችን፣ የዛሬ ለቅሶአችን፣ የዛሬ ስደታችን፣ የዛሬ መታረዳችን ያን ጊዜ ታይቷቸው ነበር ያለቀሱት። ሰላሙን ሊያስከብሩለት፣ መብቱን ሊያስጠብቁለት፣ አንድ ሊያደርጉት የተነሱለትን ሕዝብ በትነውት መሞታቸው ነበር ያስለቀሳቸው።

ጃንሆይም አልቅሰዋል፤ ያስለቀሳችው ግን ሃምሳ ዓመት ከኖሩበት ቤተ መንግሥት በመውጣታቸው፣ ከተከበረው ዙፋናቸው በመውረዳቸው አልነበረም፤ እንደውም «… ለአገር በጎ አስባችሁ ከተነሳችሁ፣ የአገርን ጥቅም ከራስ ጥቅም ማስቀደም አይቻልም፤ እኛ እስካሁን አገራችንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል፤ አሁን ተራው የኛ ነው ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ …» በማለት ነበር ቤተ መንግሥቱን የለቀቁት፤ በኋላ ግን በእስር በቆዩበት ጊዚያት አገራቸው በምን አይነት ሰዎች እጅ እንደወደቀች ሲገነዘቡ ያ ሁሉ ከውጪ ጠላት ያደረጉት ትንቅንቅ፣ ለነጻነት ያደረጉት ተጋድሎ፣ ለሥልጣኔ ያደረጉት ጥረት፣ … እንዲህ ከንቱ ሲቀር አገሪቱ አስከፊ አደጋ ውስጥ እንደምትወድቅ ገብቷቸው ነበር ያለቀሱት። ለሕዝቡ ነበር ያነቡት።

አብዮታዊው መሪ መንግሥቱ ኃ/ማርያምም አስራ ሰባት ዓመታት ሳይተኙ፣ ሳይስቁ፣ አብዮታዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት፣ ዳር ድንበርዋን ለመጠበቅ፣ አገራቸው ተቆርሳ እንዳትወሰድ ከውስጥና ከውጪ ጠላት ለመከላከል ያደራጁት ያነቁት የሚተማመኑበት ጦር ፈርሶ እንደጎርፍ መንገዱን ሞልቱ ሲሄድ በአንቦ አቅጣጫ በሚገኝ አንድ ተራራ አናት ላይ ወጥተው ድንጋይ ላይ ቁጭ ብለው ጦሩን ቁልቁል እያዩ ነበር ያለቀሱት፤ የሀገራቸው መጪ ዕድል አስከፊ ውድቀት እየታያቸው ነበር ያነቡት።

የሁሉም እንባ አላግባብ የፈሰሰ አልነበረም፤ ከመቆርቆር ከመቆጨት ምንም ማድረግ ካለመቻል የመነጨ ነበር። ይህ ደግሞ ምስክር የሚያስፈልገው፣ ማስረጃ የሚጎተትለት አይደለም፤ ጠቀመም ጎዳ የሁሉንም ታሪክ ሥራቸው በይፋ ያስረዳል። ለዚህ ጽሁፍ ያነሳሳኝ ኃይለማርያም ዓይን ስር ቁርዝዝ ብላ የወረደችው እንባ ናት። እንደውነቱ ጉንጫቸውን ሰንጥቃ ባትወርድም ያው እንባ ናትና እንደመሪ እንባ ልቆጥራት አስቤ ነበር፤ ግን እሷንስ ቢሆን ለምን አለቀሷት ብዬ ሳስብ የባሰ ንድድ አለኝ። እንደዚች አይነት የምታቅለሸልሽ አስቀያሚ እንባ ዕድሜዬን ሙሉ አይቼ አላውቅም። ለነገሩ እንኳን እንባቸው ሳቃቸውንም ያምራል ብሎ የሚከራከር ያለ አይመስለኝም።

ዋናው ነገር ግን ይሄ አይደለም ለምን አለቀሱ ነው? ጥያቄው እንዴ! እንዴት አያለቅሱም በደቡብ አፍሪካ የተቃጠሉት ወገኖቻቸው አይደሉም እንዴ! ምን ማለትህ ነው። ባህር እየሰመጠ የሚሞተው ወጣት አያሳዝናቸውም እንዴ! ሰሞኑንስ እንደመስዋዕት በግ የታረዱት ወገኖቻቸው አይደሉም እንዴ! ሌላም ሌላም ልትሉ ትችሉ ይሆናል። የኃይለማርያም ለቅሶ ግን በዚህ አይደለም፤ ግምገማ በሚባል ፈሊጥ እየታዘዙ ከሚመሩባት ወንበር ተሽቀንጥረው እንደሚወረወሩ የሚያመላክት ዘለፋና ስድብ ስለደረሰባቸው ነው። ሌሎችን በዚችው ጥበብ እሳቸውም አባረው ያውቃሉ፤ ያቺ ቀን ለሳቸውም በጣም ቅርብ መሆንዋ ስለተሰማቸው ነበር ያነቡት (ማንባት እንኳን አትባልም)። ብዙዎች ለምን ደም አያለቅሱም ይበላቸው ከማለት ውጪ ከንፈር ይመጡላቸዋል ብዬ አላስብም፤ እራሳቸውም ቢሆኑ ጥርስ ከማፋጨትና ጸጉር ከመንጨት በቀር የሚሉት ይኖራል ተብሎ አይገመትም።

የእንባን ነገር ካነሳሁ አይቀር ጠ/ሚንስትሩን ምክር መክሬ ልሰናበት። ጠ/ሚንስትር ሆይ! ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በይቅርታም ሆነ ነገርን አለዝበው የመውረጃዎን ጊዜን አበላሽተዋል። ካሁን በኋላም ተሰድጄ እኖራለሁም ብለው አያስቡ። ያንንም አጥተዋል። የጠቅላይ ሚንስትርነቱንም ሥልጣን ይዘው መቀመጥ ካሁን በኋላ የህልም እንጀራ ነው። የሥራ ጊዜዎን ወይም መጠቀሚያነትዎን በአግባቡ ጨርሰዋል። ማድረግ የሚገባዎ ቢኖር ረዥም የማልቀሻ ጊዜ ስለሚጠብቅዎ እንባ ቁጠባ በማድረግ ዓይንዎትን መጠበቅ ብቻ ነው። ኖሮም አላማረበት «ከሞጨሞጨ ዓይን የጠፋ ይሻላል» ካሉም የራስዎ ጉዳይ ግምገማውን ያቅልልዎ።

ወለላዬ 

welelaye2@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule