• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ካፍቴሪያ ሰራተኞች ድምጽ አልባው እሮሮ!

January 21, 2015 10:14 am by Editor Leave a Comment

ንብረትነቱ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር እንደሆነ በሚነገርለት ካፍቴሪያ ውስጥ የሚፈጸመው ግፍ አይሏል ። ከዛሬ 10 ዓመት በፊት እዚህ ኮሚኒቲ ካፍቴሪያ ውስጥ በተለያየ የሙያ ዘርፍ ሰማርተው እያገለገሉ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን አብዛኛዎቹ በወጣትነት እድሚያቸው የተቀጠሩ ናቸው።

ታዲያ ለወጣትነት እድሜ ጉልበታቸው ሳይሰቱ ነገን በተስፋ በመናፈቅ ተመጣጣኝ ባልሆነ ክፍያ በቀን ከ 8 ሰዓት በላይ አውዳአመታትን ሳይቀር ያለ እረፍት በስራ በማሳለፍ ኮሚኒቲውን አገልግለዋል። ሰራተኞቹ በተሰማሩበት የስራ መስክ በሚከፈላቸው ደሞዝ እንደማንኛውም ማህበረሰብ ቤትሰብ አፍርተዋል ። እነዚህ ወገኖች እንደመነሻ በተቀጠሩበት አነስተኛ ደሞዝ ከግዜ ወደ ግዜ እየከበደ የመጣውን የስደት ዓለም ህይወት መቋቋም ተስኗቸው ገሚሱ በብስጨት በደረሰበት የጤና መታወክ ለህለፍት ሀይወት ሲዳረግ በስኳር በሽታ አይኑ ታውሮ የአልጋ ቁራኛ ሆኖ ቤተሰቡን የበተነም እንዳለ ይነገራል። የተቀሩት እንደ ስራ ባልደረቦቻቸው አስከፊው ዕጣ ደርሷቸው ከስራ ገበታ ስኪፈናቀሉ በደም ግፊት እና ተጓዳኝ በሆኑ በሽታዎች የተጎስቆለ አካላቸውን በቁም እያስታመሙ አቤት ቢባል አድማጭ በሌለበት ሰማይ ስር የመጣውን ሁሉ ችለው ከእጅ ወደ አፍ የሆነቸውን ኑሮ ለማሸነፍ በውዴታ ግዴታ ኮፍቴሪያውን ማገልገላቸውን ቀጥለዋል።

ሁሌም ሃዘን እንጂ ደስታ ውስጣቸውን የማይሰማው እነዚህ ወገኖች የወጣትነት ፊት ገጽታቸው ተቀይሮ ያለ እድሜያቸው የተሸብሽው ቆዳቸው ከሰውነት ጓዳና በመውጣት ውስጣቸው ፍጹም፡ ሰላም እንድሌለ ያሳብቃል። ኮሚኒቲውን ለቀው እንዳይሄዱ ጉልበታቸው ዝሎ አቅም አልባ ሆነዋል ! የእድሜውም ጉዳይ በሌላ በኩል በዕንቀርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖባቸዋል። ብቻ በአጠቃላይ በ 4 አመት አንድ ግዜ እየጠበቁ ከኮሚኒቲው መተዳደሪያ ደንብ እና ስረዓት ውጭ በኤንባሲው አስተባባሪነት በብሄር እይተቦደኑ ያለችሎታቸው የአመራሩን ቦታ በሚጨብጡ የኮሚቲኒው አስተዳዳሪዎች በሚደርሰባቸው ዛቻ እና ማስፈራሪያ ከደሞዝ ጭማሪ ይልቅ ከስራ ገበታቸው እንዳይፈናቅሉ በስጋት ተሸብበው ፈጣሪ መህረቱን እንዲያወርድላቸው ይማጸናሉ። ለነዚህ የኮሚቲው አንጋፋ ሰራተኞች ክብር ብሎ ነገር አይታሰብም ምግብ በላህ ሻይ ጠጣህ የለስላሳ ማቀዝቀዣ ለመክፈት አሰብክ ተብሎ የጎሪጥ ክትትል እየተደረገባቸው ከሚሰነዘርባቸው አሳፍሪና አስዛኝ ክስ ባሻገር ህይወታቸውን ሙሉ በማገልገላቸው ብቻ ለሞራል የሰርተፍኬት ሽልማት እንኳን አጊተው አያውቁም። አንዳንዴም በተጠቀሱት አመራር አባላት እንደ ሰራተኛ ሳይሆን እንደ ሌባ በአይነ ቁራኛ ይጠበቃሉ። አፋቸውን በሁለት እጆቻቸው ግጥም አድርገው ካልያዙ የመናገር ሰበአዊ መብታቸው ተገፎ አመራር ዘለፉችሃል በሚል ክስ በዝቅተኛ ደሞዛቸው ላይ ከፍተኛ ቅጣት ይጣላል አሊያም ከስራ ገበታቸው ይታገዳሉ፡፡ አልፎ አልፎም አይጥ በበላ ዳዋ እንዲሉ በሁለት አመት አንዴ ከአንድ ገጽ በማይበልጥ ብጣሽ ወረቀት ለማህበሩ አባላት ለይስሙላ በሚቀርብ ሪፖርት በኮሚኒቲው ካፍቴሪያ ካዝና ላይ ለተፈፀመው ነውረኛ ተግባር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተጠያቂ ሆነው ጣት ይቀሰርባቸዋል።

ሳውዲ አረቢያ ምድር ላይ ይህ ሁሉ ግፍ እና በደል በነዚህ ኢትዮጵያውያን ላይ እይተፈፀመ ያለው በባእዳኑ ሳውዲያን ሳይሆን ሰንደቃላማችን ከፍ ብሎ የሚውለበለብበት ግቢ ውስጥ በሚገኙ  ወገናውዊነት በማይሰማቸው ጨካኝ ኢትዮጵያውያን መሆኑ ነገሩን አነጋጋሪ እና ውስብስብ ያደርገዋል። ወትሮስ ለማን አቤት ሊባል ! ዛሬ እነዚህ ግፉሃን ልጆቻቸውን ማስተማር ተስኗቸው ተጨማሪ ግቢ ፍለጋ ከካፍቴሪያው የስራ ሰአት ውጭ በመከራተት አስቀያሚ የስደት ዓለም ህይወታቸውን መግፋት ግድ ቢሆንባቸውም ሁሉም ነገር ግን ጨልሞል።በተላይ የሳውዲ አረቢያ ሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር መ/ቤት የአሰሪ እና ሰራተኛ ደንብ አስመልክቶ ባወጣው ህግ ማናኛውም የውጭ ሃገር ዜጋ አሰሪው ከሚያሰማራው የስራ መስክ ውጭ የትም ሄዶ መስራት እንደማይችል ከተነገረ ወዲህ ለነዚህ ወገኖች የስውዲን አረቢያን ህይወት ያለተጨማሪ ግቢ መግፋት የማይታሰብ በመሆኑ ለከፋ ስቃይ እና መከራ ተዳርገዋል።

Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

ማሳሰቢያ ከመረጃው ጋር ተያያዥ የሆነ ምስል ትክክለኛ የኮሚኒቲው ካፍቴሪያ መሆኑን መግለጽ እንወዳለን

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule