• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ካፍቴሪያ ሰራተኞች ድምጽ አልባው እሮሮ!

January 21, 2015 10:14 am by Editor Leave a Comment

ንብረትነቱ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር እንደሆነ በሚነገርለት ካፍቴሪያ ውስጥ የሚፈጸመው ግፍ አይሏል ። ከዛሬ 10 ዓመት በፊት እዚህ ኮሚኒቲ ካፍቴሪያ ውስጥ በተለያየ የሙያ ዘርፍ ሰማርተው እያገለገሉ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን አብዛኛዎቹ በወጣትነት እድሚያቸው የተቀጠሩ ናቸው።

ታዲያ ለወጣትነት እድሜ ጉልበታቸው ሳይሰቱ ነገን በተስፋ በመናፈቅ ተመጣጣኝ ባልሆነ ክፍያ በቀን ከ 8 ሰዓት በላይ አውዳአመታትን ሳይቀር ያለ እረፍት በስራ በማሳለፍ ኮሚኒቲውን አገልግለዋል። ሰራተኞቹ በተሰማሩበት የስራ መስክ በሚከፈላቸው ደሞዝ እንደማንኛውም ማህበረሰብ ቤትሰብ አፍርተዋል ። እነዚህ ወገኖች እንደመነሻ በተቀጠሩበት አነስተኛ ደሞዝ ከግዜ ወደ ግዜ እየከበደ የመጣውን የስደት ዓለም ህይወት መቋቋም ተስኗቸው ገሚሱ በብስጨት በደረሰበት የጤና መታወክ ለህለፍት ሀይወት ሲዳረግ በስኳር በሽታ አይኑ ታውሮ የአልጋ ቁራኛ ሆኖ ቤተሰቡን የበተነም እንዳለ ይነገራል። የተቀሩት እንደ ስራ ባልደረቦቻቸው አስከፊው ዕጣ ደርሷቸው ከስራ ገበታ ስኪፈናቀሉ በደም ግፊት እና ተጓዳኝ በሆኑ በሽታዎች የተጎስቆለ አካላቸውን በቁም እያስታመሙ አቤት ቢባል አድማጭ በሌለበት ሰማይ ስር የመጣውን ሁሉ ችለው ከእጅ ወደ አፍ የሆነቸውን ኑሮ ለማሸነፍ በውዴታ ግዴታ ኮፍቴሪያውን ማገልገላቸውን ቀጥለዋል።

ሁሌም ሃዘን እንጂ ደስታ ውስጣቸውን የማይሰማው እነዚህ ወገኖች የወጣትነት ፊት ገጽታቸው ተቀይሮ ያለ እድሜያቸው የተሸብሽው ቆዳቸው ከሰውነት ጓዳና በመውጣት ውስጣቸው ፍጹም፡ ሰላም እንድሌለ ያሳብቃል። ኮሚኒቲውን ለቀው እንዳይሄዱ ጉልበታቸው ዝሎ አቅም አልባ ሆነዋል ! የእድሜውም ጉዳይ በሌላ በኩል በዕንቀርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖባቸዋል። ብቻ በአጠቃላይ በ 4 አመት አንድ ግዜ እየጠበቁ ከኮሚኒቲው መተዳደሪያ ደንብ እና ስረዓት ውጭ በኤንባሲው አስተባባሪነት በብሄር እይተቦደኑ ያለችሎታቸው የአመራሩን ቦታ በሚጨብጡ የኮሚቲኒው አስተዳዳሪዎች በሚደርሰባቸው ዛቻ እና ማስፈራሪያ ከደሞዝ ጭማሪ ይልቅ ከስራ ገበታቸው እንዳይፈናቅሉ በስጋት ተሸብበው ፈጣሪ መህረቱን እንዲያወርድላቸው ይማጸናሉ። ለነዚህ የኮሚቲው አንጋፋ ሰራተኞች ክብር ብሎ ነገር አይታሰብም ምግብ በላህ ሻይ ጠጣህ የለስላሳ ማቀዝቀዣ ለመክፈት አሰብክ ተብሎ የጎሪጥ ክትትል እየተደረገባቸው ከሚሰነዘርባቸው አሳፍሪና አስዛኝ ክስ ባሻገር ህይወታቸውን ሙሉ በማገልገላቸው ብቻ ለሞራል የሰርተፍኬት ሽልማት እንኳን አጊተው አያውቁም። አንዳንዴም በተጠቀሱት አመራር አባላት እንደ ሰራተኛ ሳይሆን እንደ ሌባ በአይነ ቁራኛ ይጠበቃሉ። አፋቸውን በሁለት እጆቻቸው ግጥም አድርገው ካልያዙ የመናገር ሰበአዊ መብታቸው ተገፎ አመራር ዘለፉችሃል በሚል ክስ በዝቅተኛ ደሞዛቸው ላይ ከፍተኛ ቅጣት ይጣላል አሊያም ከስራ ገበታቸው ይታገዳሉ፡፡ አልፎ አልፎም አይጥ በበላ ዳዋ እንዲሉ በሁለት አመት አንዴ ከአንድ ገጽ በማይበልጥ ብጣሽ ወረቀት ለማህበሩ አባላት ለይስሙላ በሚቀርብ ሪፖርት በኮሚኒቲው ካፍቴሪያ ካዝና ላይ ለተፈፀመው ነውረኛ ተግባር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተጠያቂ ሆነው ጣት ይቀሰርባቸዋል።

ሳውዲ አረቢያ ምድር ላይ ይህ ሁሉ ግፍ እና በደል በነዚህ ኢትዮጵያውያን ላይ እይተፈፀመ ያለው በባእዳኑ ሳውዲያን ሳይሆን ሰንደቃላማችን ከፍ ብሎ የሚውለበለብበት ግቢ ውስጥ በሚገኙ  ወገናውዊነት በማይሰማቸው ጨካኝ ኢትዮጵያውያን መሆኑ ነገሩን አነጋጋሪ እና ውስብስብ ያደርገዋል። ወትሮስ ለማን አቤት ሊባል ! ዛሬ እነዚህ ግፉሃን ልጆቻቸውን ማስተማር ተስኗቸው ተጨማሪ ግቢ ፍለጋ ከካፍቴሪያው የስራ ሰአት ውጭ በመከራተት አስቀያሚ የስደት ዓለም ህይወታቸውን መግፋት ግድ ቢሆንባቸውም ሁሉም ነገር ግን ጨልሞል።በተላይ የሳውዲ አረቢያ ሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር መ/ቤት የአሰሪ እና ሰራተኛ ደንብ አስመልክቶ ባወጣው ህግ ማናኛውም የውጭ ሃገር ዜጋ አሰሪው ከሚያሰማራው የስራ መስክ ውጭ የትም ሄዶ መስራት እንደማይችል ከተነገረ ወዲህ ለነዚህ ወገኖች የስውዲን አረቢያን ህይወት ያለተጨማሪ ግቢ መግፋት የማይታሰብ በመሆኑ ለከፋ ስቃይ እና መከራ ተዳርገዋል።

Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

ማሳሰቢያ ከመረጃው ጋር ተያያዥ የሆነ ምስል ትክክለኛ የኮሚኒቲው ካፍቴሪያ መሆኑን መግለጽ እንወዳለን

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule