
በህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማና ድጋፍ ለዓለም የጤና ጥበቃ ድርጅት ዳይሬክተርነት የሚወዳደረው ቴድሮስ አድሃኖም የመመረጡ ጉዳይ አደጋ ገጥሞታል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረበት ወቅት ሦስት የኮሌራ ወረርሽኞች በምሥጢር እንዲያዙ ማድረጉ ለዳይሬክተርነት እንዳይበቃ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ እንደ አሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ጉዳይ የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ሜይ 13፤2017 ዓም “የዓለም ጤና ጥበቃ ድርጅትን ለመምራት የሚወዳደረው እጩ ወረርሽኝ በመደበቅ ተከሰሰ” በሚል ርዕስ ባስነበበው ዜና የቴድሮስን የመመረጥ ተስፋ ስለሚያጨልመው የኮሌራ ወረርሽኝ ምሥጢር በዝርዝር አትቷል፡፡
በያዝነው የግንቦት ወር (ከሜይ 22፣ 2017) ጀምሮ በጄኔቫ በሚካሄደው የአንድ ሳምንት ስብሰባ ድርጅቱን ለመምራት ከሚወዳደሩት ሦስት እጩዎች (ቴድሮስን ጨምሮ እንግሊዛዊው ዶ/ር ዴቪድ ናባሮና ፓኪስታናዊቷ ዶ/ር ሳኒያ ኒሽታር) መካከል አንዱ የዳይሬክተርነቱን ቦታ ይወስዳል፡፡ ስብሰባው ሊጀመር አንድ ሳምንት አካባቢ ሲቀረው በቴድሮስ ላይ የቀረበው ይህ ክስ ራሱንም ያስደነገጠው ይመስላል፤ “አልገረመኝም ግን ቅሬታን አሳድሮብኛል፤ ይህ ባለቀ ሰዓት የሚካሄድ የስም ማጥፋት ዘመቻ ነው” ብሎታል፡፡
ምሥጢሩን ይፋ ያደረጉት የቴድሮስ ተፎካካሪ የሆኑት የዶ/ር ናባሮ ኢ-መደበኛ አማካሪና በጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ የኦኒል የብሔራዊና ዓለምአቀፍ የጤና ሕግ ተቋም ዳይሬክተር የሆኑት ሎውረንስ ጎስቲን ናቸው፡፡ ጎስቲን እንደሚሉት ቴድሮስ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረበት ዓመታት (2005 – 2012) እኤአ በ2006፣ 2009 እና 2011 በኢትዮጵያ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ይፋ እንዳይሆን በምሥጢር እንዲያዝ አድርጓል፤ ይህም ዓለምአቀፉን የጤና ጥበቃ ድርጅት እንዳይመራ ከበቂ በላይ ምክንያት መሆን ይችላል የሚል መከራከሪያ ነው፡፡

ዶ/ር ናባሮ ስለጉዳዩ ሲጠየቁ “እኔ በጭራሽ ይህንን አላውቅም፤ ዶ/ር ቴድሮስ ብቃት ያለው የጤና ባለሙያ ነው፤ ጎስቲን ይህንን የተናገረው እኔን ሳያማክር ነው፤ ሆኖም ግን ቴድሮስ እውነቱን መናገር፤ ለረጅም ጊዜ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ሪፖርት ማድረግ፤ እውነትን መናገር ይገባዋል” በማለት ከቻይና በስልክ ለኒው ዮርክ ታይምስ ተናግረዋል፡፡ ጎስቲን ከኢመደበኛ አማካሪነት በተጨማሪ ከናባሮ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው መሆኑ ቢታወቅም ጎስቲን ይህንን ያጋለጡት ለዓለምአቀፉ ድርጅት ከመቆርቆር የተነሳ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ቴድሮስ አድሃኖም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረባቸው ዓመታት ጎስቲን በሚመሩት ተቋም ጥሪ እየተደረገለት በጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ “የተከበሩ” ተብሎ ንግግሮችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ዓይነቱን የምዕራባውያን “ወዳጅነት” ነበር ቴድሮስ እንደ ብቃት መለኪያ አድርጎ ሲያቀርብ የነበረው፡፡
የዛሬ አሥር ዓመት አካባቢ በኢትዮጵያ የኮሌራ በሽታ ተነስቶ እኤአ በ2007ዓም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ 700 ያህል ሕዝብ ሲልቅና ከ60ሺህ በላይ በበሽታው ሲጠቃ የህወሃት ሹሞች “ውሃ ተቅማጥ” ነው ከማለት ባላለፈ የሽታውን መከሰት ሲክዱ ነበር፡፡ ዜናው በዓለምአቀፍ ሚዲያ ላይ ቢዘገብም “የድርብ አኻዝ” ዕድገት ስሌቱን የሚያዛባና ቱሪዝምን የሚደናቅፍ ሆኖ በመገኘቱ የሰዎች መሞት ለህወሃት ብዙም አላስጨነቀውም፡፡ ቴድሮስም በወቅቱ ከአውሮጳና አሜሪካ የሚሰጠውን ትዕዛዝ በመፈጸም ተግባር ተይዞ “ዛሬን” አላሰበም ነበር፡፡ ይኸው በሽታ አሁን ደግሞ “አተት” (አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት) የሚል የቁልምጫ ስም ተሰጥቶታል፡፡
የኮሌራ ወረርሽኝ በተደጋጋሚ በሚከሰትበት ወቅት ከህወሃት/ኢህአዴግ የበላይ ሹሞች ሚዲያውም ሆነ የጤና ሠራተኞች “ኮሌራ” የሚለውን ቃል እንዳይጠቀሙ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ ሆኖም በድብቅ እንዲወጣ በተደረገ የሰገራ ናሙና ምርመራ በርግጥ የኮሌራ ወረርሽን ለመከሰቱ ዓለምአቀፍ የጤና ባለሙያዎች ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ ዘገባው በዝርዝር እንደሚያስረዳው ከዚህ በፊት የበሽታው ወረርሽን ታይቶባቸው በማይታወቀው በጉጂ፣ በባሌ እና በምስራቅ ሸዋ ዞኖች እኤአ ከሴፕቴምበር 15 እስከ ኦክቶበር 9፣ 2006ዓም (መስከረም5 እስከ 29፤1999ዓም) ቦታዎቹን የቃኙና ምርምር ያደረጉ ባለሙያዎች ኮሌራ በአካባቢዎቹና አጎራባች ክልሎችና ዞኖች መከሰቱን አረጋግጠዋል፡፡ (ኒው ዮርክ ታይምስ የጠቀሰውን የባለሙያዎቹን ዘገባ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል)፡፡
በኢትዮጵያ ማንኛውንም ተቃውሞ በማፈን ለህዝብን ስቃይ “ጥሪ አይቀበልም” ሲል የኖረው ህወሃት/ኢህአዴግ አሁን በራሱ ገመድ ለመታነቅ ጊዜው የደረሰበት ይመስላል፡፡ በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ ለምርጫ ውድድር ያቀረበው ዕጩ ተወዳዳሪ በዚህ ሁኔታ መከሰሱ ባለቀ ሰዓት ተስፋ አስቆራጭ ሆኖበታል፤ ቴድሮስም ይህንኑ ያመነ ይመስላል፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት በዕጩነት ሲቀርብ የተጠየቀውን ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ አቅቶት ሲጨነቅ የነበረው ቴድሮስ አድሃኖም፤ ይህንን በመጨረሻ ሰዓት ላይ የተከፈተበትን የተቀነባበረ ዘመቻ ለመቋቋም አይችልም የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው፡፡ የኮ/ሎ ጎሹ ወልዴን አስደናቂ ብቃት ባስናፈቀ መልኩ ቴድሮስ ያቀረበው የምረጡኝ ቃለ ምልልስ ጎልጉል በዘገበበት ወቅት የሕዝብንም ኃፍረት አብሮ ዘግቦ ነበር፡፡
በአሜሪካ የፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሲካሄድ በህዳር ወር መጀመሪያ ምርጫው ከመደረጉ በፊት በጥቅምት ወር አንዱ ዕጩ ስለ ሌላኛው ጊዜ ጠብቆ የሚያወጣው ምሥጢር አለ፡፡ ይህ በተለምዶ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” (the October Surprise) በሚባለው የመመረጥ ዕድላቸው በቀላሉ እንዲሳካ የተደረገላቸው የመኖሩን ያህል በአስከፊ ሁኔታ ሽንፈትን እንዲከናነቡ የተደረጉም ጥቂቶች አይደሉም፡፡ የተደበቀው የኮሌራ ምሥጢር የቴድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” ይሆን?
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
If the Western politicians approve the appointment of Adhanom for heading theWHO, they are boldly telling the world that they are wedging disguised war against humanity.
Adhanom is one of the evil gangs put in power to destroy Ethiopia/Ethiopians and beyond.
Also: https://www.nytimes.com/2017/05/13/health/candidate-who-director-general-ethiopia-cholera-outbreaks.html?_r=1
Tedros should go to The Hague, by no means to the WHO!
ግዜኣችሁ በከንቱ እያበከናችሁ ነው። ኣሁን ኣሁን’ማ ቀይ መስመሩን እያለፋችሁ ነው። 7 ሚልዮን የትግራይ ህዝብን በጣም በሚግርም መልኩ መልኩ ኢትዮጵያውነት ነጥቃችሁ፡ መድረሻችሁ የት እንደሆነ ማወቅ የተሳናችሁ ናችሁ።
ዶ/ር ቴድሮስ፡ የትግራይ ተወላጅ በመሆኑ ብቻ ይህን ያክል የጥላቻ ዘመቻ፡ ከባድ ዕዳ እተሸከማሁ መሆናችሁን ማወቅ ተስኖችሃል።
Thank you Reeyot!
Most of all, I like your synthesis “After all, as Dr. Martin Luther King Jr. said: “Injustice anywhere is a threat to justice everywhere.” We cannot overlook not only the injustices across the world but also the perpetrators and their enablers that cause so much pains and suffering.”
[http://www.ethiomedia.com/1000bits/reeyot-alemu-letter-to-WHO-general-assembly.html]
Post Cold war Western politicians are pursuing disguised war against the powerless humanity using a very simple tact: enabling ill-willed individuals and dictators in the East. If you critically analyse the post cold war world order, Western politicians are pursuing in concert two parallel seemingly disguised tact against the weak societies (the East):
1. demolishing by enabling traitors
2. demolishing by wedging direct war based on fictitious claims
I think they will appoint Adhanom for two reasons:
1. because they have to award him for his tremendous services to them in demolishing Ethiopia and killing/crippling lives of numerous Ethiopians.
2. to demolish more African nations and abolish more African lives in the near future
We should realize that TPLF is an ideal partner of the post cold war disguised inhuman world order (WO) lead by US and UK.
Many other TPLF like junta’s who effectively served the post cold war WO will be elevated and awarded for their extraordinary records against their own people and nations. Enabling traitors and dictators will continue until another global revolution or the 3rd world war. I hope at least the second will take place soon.