• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኮሌራው ምሥጢር! የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ”?

May 14, 2017 01:42 am by Editor 4 Comments

በህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማና ድጋፍ ለዓለም የጤና ጥበቃ ድርጅት ዳይሬክተርነት የሚወዳደረው ቴድሮስ አድሃኖም የመመረጡ ጉዳይ አደጋ ገጥሞታል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረበት ወቅት ሦስት የኮሌራ ወረርሽኞች በምሥጢር እንዲያዙ ማድረጉ ለዳይሬክተርነት እንዳይበቃ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ እንደ አሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ጉዳይ የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡

ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ሜይ 13፤2017 ዓም “የዓለም ጤና ጥበቃ ድርጅትን ለመምራት የሚወዳደረው እጩ ወረርሽኝ በመደበቅ ተከሰሰ” በሚል ርዕስ ባስነበበው ዜና የቴድሮስን የመመረጥ ተስፋ ስለሚያጨልመው የኮሌራ ወረርሽኝ ምሥጢር በዝርዝር አትቷል፡፡

በያዝነው የግንቦት ወር (ከሜይ 22፣ 2017) ጀምሮ በጄኔቫ በሚካሄደው የአንድ ሳምንት ስብሰባ ድርጅቱን ለመምራት ከሚወዳደሩት ሦስት እጩዎች (ቴድሮስን ጨምሮ እንግሊዛዊው ዶ/ር ዴቪድ ናባሮና ፓኪስታናዊቷ ዶ/ር ሳኒያ ኒሽታር) መካከል አንዱ የዳይሬክተርነቱን ቦታ ይወስዳል፡፡ ስብሰባው ሊጀመር አንድ ሳምንት አካባቢ ሲቀረው በቴድሮስ ላይ የቀረበው ይህ ክስ ራሱንም ያስደነገጠው ይመስላል፤ “አልገረመኝም ግን ቅሬታን አሳድሮብኛል፤ ይህ ባለቀ ሰዓት የሚካሄድ የስም ማጥፋት ዘመቻ ነው” ብሎታል፡፡

ምሥጢሩን ይፋ ያደረጉት የቴድሮስ ተፎካካሪ የሆኑት የዶ/ር ናባሮ ኢ-መደበኛ አማካሪና በጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ የኦኒል የብሔራዊና ዓለምአቀፍ የጤና ሕግ ተቋም ዳይሬክተር የሆኑት ሎውረንስ ጎስቲን ናቸው፡፡ ጎስቲን እንደሚሉት ቴድሮስ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረበት ዓመታት (2005 – 2012) እኤአ በ2006፣ 2009 እና 2011 በኢትዮጵያ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ይፋ እንዳይሆን በምሥጢር እንዲያዝ አድርጓል፤ ይህም ዓለምአቀፉን የጤና ጥበቃ ድርጅት እንዳይመራ ከበቂ በላይ ምክንያት መሆን ይችላል የሚል መከራከሪያ ነው፡፡

ሎውረንስ ጎስቲን

ዶ/ር ናባሮ ስለጉዳዩ ሲጠየቁ “እኔ በጭራሽ ይህንን አላውቅም፤ ዶ/ር ቴድሮስ ብቃት ያለው የጤና ባለሙያ ነው፤ ጎስቲን ይህንን የተናገረው እኔን ሳያማክር ነው፤ ሆኖም ግን ቴድሮስ እውነቱን መናገር፤ ለረጅም ጊዜ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ሪፖርት ማድረግ፤ እውነትን መናገር ይገባዋል” በማለት ከቻይና በስልክ ለኒው ዮርክ ታይምስ ተናግረዋል፡፡ ጎስቲን ከኢመደበኛ አማካሪነት በተጨማሪ ከናባሮ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው መሆኑ ቢታወቅም ጎስቲን ይህንን ያጋለጡት ለዓለምአቀፉ ድርጅት ከመቆርቆር የተነሳ መሆኑ ተነግሯል፡፡

ቴድሮስ አድሃኖም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረባቸው ዓመታት ጎስቲን በሚመሩት ተቋም ጥሪ እየተደረገለት በጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ “የተከበሩ” ተብሎ ንግግሮችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ዓይነቱን የምዕራባውያን “ወዳጅነት” ነበር ቴድሮስ እንደ ብቃት መለኪያ አድርጎ ሲያቀርብ የነበረው፡፡

የዛሬ አሥር ዓመት አካባቢ በኢትዮጵያ የኮሌራ በሽታ ተነስቶ እኤአ በ2007ዓም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ 700 ያህል ሕዝብ ሲልቅና ከ60ሺህ በላይ በበሽታው ሲጠቃ የህወሃት ሹሞች “ውሃ ተቅማጥ” ነው ከማለት ባላለፈ የሽታውን መከሰት ሲክዱ ነበር፡፡ ዜናው በዓለምአቀፍ ሚዲያ ላይ ቢዘገብም “የድርብ አኻዝ” ዕድገት ስሌቱን የሚያዛባና ቱሪዝምን የሚደናቅፍ ሆኖ በመገኘቱ የሰዎች መሞት ለህወሃት ብዙም አላስጨነቀውም፡፡ ቴድሮስም በወቅቱ ከአውሮጳና አሜሪካ የሚሰጠውን ትዕዛዝ በመፈጸም ተግባር ተይዞ “ዛሬን” አላሰበም ነበር፡፡ ይኸው በሽታ አሁን ደግሞ “አተት” (አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት) የሚል የቁልምጫ ስም ተሰጥቶታል፡፡

የኮሌራ ወረርሽኝ በተደጋጋሚ በሚከሰትበት ወቅት ከህወሃት/ኢህአዴግ የበላይ ሹሞች ሚዲያውም ሆነ የጤና ሠራተኞች “ኮሌራ” የሚለውን ቃል እንዳይጠቀሙ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ ሆኖም በድብቅ እንዲወጣ በተደረገ የሰገራ ናሙና ምርመራ በርግጥ የኮሌራ ወረርሽን ለመከሰቱ ዓለምአቀፍ የጤና ባለሙያዎች ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ ዘገባው በዝርዝር እንደሚያስረዳው ከዚህ በፊት የበሽታው ወረርሽን ታይቶባቸው በማይታወቀው በጉጂ፣ በባሌ እና በምስራቅ ሸዋ ዞኖች እኤአ ከሴፕቴምበር 15 እስከ ኦክቶበር 9፣ 2006ዓም (መስከረም5 እስከ 29፤1999ዓም) ቦታዎቹን የቃኙና ምርምር ያደረጉ ባለሙያዎች ኮሌራ በአካባቢዎቹና አጎራባች ክልሎችና ዞኖች መከሰቱን አረጋግጠዋል፡፡ (ኒው ዮርክ ታይምስ የጠቀሰውን የባለሙያዎቹን ዘገባ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል)፡፡

በኢትዮጵያ ማንኛውንም ተቃውሞ በማፈን ለህዝብን ስቃይ “ጥሪ አይቀበልም” ሲል የኖረው ህወሃት/ኢህአዴግ አሁን በራሱ ገመድ ለመታነቅ ጊዜው የደረሰበት ይመስላል፡፡ በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ ለምርጫ ውድድር ያቀረበው ዕጩ ተወዳዳሪ በዚህ ሁኔታ መከሰሱ ባለቀ ሰዓት ተስፋ አስቆራጭ ሆኖበታል፤ ቴድሮስም ይህንኑ ያመነ ይመስላል፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት በዕጩነት ሲቀርብ የተጠየቀውን ጥያቄ በአግባቡ ለመመለስ አቅቶት ሲጨነቅ የነበረው ቴድሮስ አድሃኖም፤ ይህንን በመጨረሻ ሰዓት ላይ የተከፈተበትን የተቀነባበረ ዘመቻ ለመቋቋም አይችልም የሚል አስተያየት እየተሰጠ ነው፡፡ የኮ/ሎ ጎሹ ወልዴን አስደናቂ ብቃት ባስናፈቀ መልኩ ቴድሮስ ያቀረበው የምረጡኝ ቃለ ምልልስ ጎልጉል በዘገበበት ወቅት የሕዝብንም ኃፍረት አብሮ ዘግቦ ነበር፡፡

በአሜሪካ የፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሲካሄድ በህዳር ወር መጀመሪያ ምርጫው ከመደረጉ በፊት በጥቅምት ወር አንዱ ዕጩ ስለ ሌላኛው ጊዜ ጠብቆ የሚያወጣው ምሥጢር አለ፡፡ ይህ በተለምዶ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” (the October Surprise) በሚባለው የመመረጥ ዕድላቸው በቀላሉ እንዲሳካ የተደረገላቸው የመኖሩን ያህል በአስከፊ ሁኔታ ሽንፈትን እንዲከናነቡ የተደረጉም ጥቂቶች አይደሉም፡፡ የተደበቀው የኮሌራ ምሥጢር የቴድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” ይሆን?


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. rasdejen says

    May 15, 2017 10:04 pm at 10:04 pm

    If the Western politicians approve the appointment of Adhanom for heading theWHO, they are boldly telling the world that they are wedging disguised war against humanity.

    Adhanom is one of the evil gangs put in power to destroy Ethiopia/Ethiopians and beyond.
    Also: https://www.nytimes.com/2017/05/13/health/candidate-who-director-general-ethiopia-cholera-outbreaks.html?_r=1

    Reply
  2. mertcha says

    May 16, 2017 12:32 am at 12:32 am

    Tedros should go to The Hague, by no means to the WHO!

    Reply
  3. Aman says

    May 16, 2017 06:00 am at 6:00 am

    ግዜኣችሁ በከንቱ እያበከናችሁ ነው። ኣሁን ኣሁን’ማ ቀይ መስመሩን እያለፋችሁ ነው። 7 ሚልዮን የትግራይ ህዝብን በጣም በሚግርም መልኩ መልኩ ኢትዮጵያውነት ነጥቃችሁ፡ መድረሻችሁ የት እንደሆነ ማወቅ የተሳናችሁ ናችሁ።
    ዶ/ር ቴድሮስ፡ የትግራይ ተወላጅ በመሆኑ ብቻ ይህን ያክል የጥላቻ ዘመቻ፡ ከባድ ዕዳ እተሸከማሁ መሆናችሁን ማወቅ ተስኖችሃል።

    Reply
  4. Ras Dejen says

    May 17, 2017 04:13 pm at 4:13 pm

    Thank you Reeyot!
    Most of all, I like your synthesis “After all, as Dr. Martin Luther King Jr. said: “Injustice anywhere is a threat to justice everywhere.” We cannot overlook not only the injustices across the world but also the perpetrators and their enablers that cause so much pains and suffering.”
    [http://www.ethiomedia.com/1000bits/reeyot-alemu-letter-to-WHO-general-assembly.html]

    Post Cold war Western politicians are pursuing disguised war against the powerless humanity using a very simple tact: enabling ill-willed individuals and dictators in the East. If you critically analyse the post cold war world order, Western politicians are pursuing in concert two parallel seemingly disguised tact against the weak societies (the East):
    1. demolishing by enabling traitors
    2. demolishing by wedging direct war based on fictitious claims
    I think they will appoint Adhanom for two reasons:
    1. because they have to award him for his tremendous services to them in demolishing Ethiopia and killing/crippling lives of numerous Ethiopians.
    2. to demolish more African nations and abolish more African lives in the near future

    We should realize that TPLF is an ideal partner of the post cold war disguised inhuman world order (WO) lead by US and UK.
    Many other TPLF like junta’s who effectively served the post cold war WO will be elevated and awarded for their extraordinary records against their own people and nations. Enabling traitors and dictators will continue until another global revolution or the 3rd world war. I hope at least the second will take place soon.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule