• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፀረ-ኢትዮጵያዊው ገዥ ሥጦታዎች አያባሩም!

January 15, 2015 01:32 am by Editor Leave a Comment

የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር በተደጋጋሚ ለታጋዩ ክፍል የሚያደርገው ልገሣ፤ ማብቂያ ዲካ የለውም። አሁን ደግሞ እልል የሚያስብል ስጦታ ፊታችን ላይ ዘርግፎልናል። በሰላም የሚታገሉትን ድርጅቶች፤ ለማፈራረስና ለመጪው ውድድር እንዳይሳተፉ ለማድረግ፤ ባለ በሌለ ጉልበቱ ዘምቶባቸዋል። ይህ የሚጠበቅ ነው። በርግጥ ሁሉንም ታጋይ ድርጅቶች በአንድ ጠፍር አንቆ ለማጥፍት መጣሩን የሚሳየው ድርጊቱ፤ ሳያውቀው የታጋይ ድርጅቶቹን በአንድነት እንዲሰልፉ በሩን በርግዶ ከፍቶላቸዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ ታጋይ ድርጅቶች፤ ከገዥው ድርጅት አንጻር አንድ በመሆን፤ አማራጭ ሆነው እንዲቀርቡ ከመጎትጎት ቦዝኖ አያውቅም። አሁን፤ ከመቼውም በላይ ይህ ጉትጎታ በሀገር ውስጥ በሰላም እየታገሉ ያሉትን ሀገራዊ ድርጅቶች፤ እንዲተባበሩ እየገፋቸው ነው። ለዚህም የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ከፍተኛ ድጋፍ ታክሎበታል። ይህ እልል ያሰኛል። ልንጠቀምበት ይገባል፤ ካወቅንበት! ድርጅቶችም እየሰሙና እየተቀበሉት ነው። ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው የነበረው ደስ የሚያሰኘው ዜና እልል አሰኝቶኛል።

የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ከመድረክ ጋር በትብብር፤ ከሰማያዊና ከመኢአድ ጋር ደግሞ ውህደት ፈጥሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ስሰማ፤ አሁን የድሉ መንገድ በደንብ ተጠረገ አልኩ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ድርጅቶቻችሁን መታገያ አድርጉ እንጂ አታምልኳቸው ሲል የነበረውን አዳመጡ። “ትግሉ ትግል የሆነው፤ በዚህ ወይንም በዚያ ስም በሚጠራ ድርጅት በመካሄዱ አይደለም። ትግሉ የሚቀጥለው ድርጅታችንን ስለከለከላችሁን ወይንም ስለፈቀዳችሁልን አይደለም። የምንታገለው በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሀቅ፤ ትግሉን ግድ ስላደረገው ነው።” በማለት ተነሱ። ከመሰሎቻችን ሀገር አቀፍ ድርጅቶች ጋር አንድ ሆነን እንታገላለን አሉ። ስሙን ውሰዱት አሉ። ከዚህ በላይ ለትግል ሕይወትን መሥጠት የት አለ? ቆራጥነት የት አለ። ለዚህ እኮ ነው አንዱዓለም አራጌ፣ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዩት ዓለሙ፣ በቀለ ገርባ እና ሌሎች እስር ቤት የሚማቅቁት። እናም አሁን ትግሉ የሀገር ሆነ። ትግሉ ለሀገር ሆነ። አንድነት፣ መኢአድና ሰላማዊ ተቀላቅለው ሲሰለፉ፤ ማንም ሳይቀድመኝ የመጀመሪያው አባል ለመሆን ለሩጫዬ ተዘጋጅቻለሁ። ያንዳቸውም አባል አልነበርኩም። አሁን የሁሉም ልሆን ነው። ይህን ጥሩ ሥጦታ ከንቱ ላባክነው አልፈልግም።

ድሮውንም ሥልጣን በምንም ዓይነት መንገድ እንደማይለቅ ያሳወቀው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ በሰላም እየታገልን፤ አቤቱታችንን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እናሰማለን ያሉትን ሰላምተኞች፤ መፈናፈኛ አሳጥቶ አፍኗቸዋል። አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ፤ በራሱ የዕለት ተዕለት ሕግ ማውጣትና ማፈረስ ባህርይ፤ ሕጋዊ አይደላችሁም ብሎ አንዳንዶቹን እንዳይወዳደሩ፤ ሌሎችን ደግሞ ሰርጎ በመግባት የሱ ተቀጥላዎች እንዲሆኑ እየኮለኮላቸው ነው። ይህ ሁሉ ድካሙ የሚያሳየው፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ምን ያህል የኢትዮጵያን ሕዝብና ምርጫውን እንደሚፈራ ነው። ባለፈው ጊዜ ምርጫውን 99.6% አቸነፍኩ ያለ ፓርቲ፣ የሀገሪቱን ገንዘብ፣ መንግሥታዊ መዋቅርና የሰው ኃይል በሙሉ ለራሱ ምርጫ ያዋለ ፓርቲ፣ የምርጫ ቦርዱን በቁጥጥሩ ሥር ያደረገ ፓርቲ፣ ለምን ተወዳዳሪዎቹን እና ምርጫውን ይፈራዋል። ግልጽ ነው። በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እምነት የለውም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ታጋዮች ደግሞ፤ አሁንም በሰላም መንገድ፤ ከመቼውም የበለጠ በመጠናከር፤ በገዥው ፓርቲ ፍላጎትና ሕገ-ደንብ ሳይሆን፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ቆራጥነት ትግላቸውን ወደፊት ይገፉታል።

በሰላማዊ ትግል የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ሥልጣኑን ወዶ አይለቅምና በትጥቅ ትግል እንዝመትበት ለሚሉት፤ ይሄ በር አይከፍትም። የትጥቅ ትግል የራሱ የሆነ ሁኔታዎች አሉት። ይልቁንም ያሁኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መደናበር፤ ምን ያህል የሰላማዊውን ትግል እንደሚፈራውና እንዳይካሄድ ያለ የሌለ ጉልበቱን እንደሚያፈስበት ያስረዳናል። ለምን ብንል፤ የሕዝብ ድጋፍ የሌለው ስለሆነ ነው። የሕዝቡ ድጋፍ ከታጋዮች ጋር ነው። የሕዝቡ ድጋፍ ከሰላማዊ ታጋዮች በሆነበት ቦታ፤ ሰላማዊ ትግሉ ያብባል። ያድጋል። ይጎለብታል። የይስሙላ ግደባዎች አያቆሙትም። ጊዜያዊ አጥሮች የሚያዘገዩት አጥሮቹን እስኪያፈርሳቸው ድረስ ብቻ ነው። ሰላማዊ ታጋይ ድርጅቶች በምርጫዎች መሳተፍ አለባቸው። የሚሳተፉት ምርጫውን በመጠቀም ለሕዝቡ መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ፣ ምርጫው ምን ያህል ውሸት እንደሆነ ለማሳየት፣ ለሕዝቡ የትግል ተሳትፎ በር ለማስፋትና ለማሳደግ እንጂ፣ የፓርላማ ወንበር አሟቂዎችን ቁጥር ለማብዛት አይደለም። ይህ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት የሚመራው በፓርላማው ሳይሆን፤ በጀርባው ባስቀመጠው የጉልበት መዋቅሩ ነው።

በዚህ አሁን በሙሉ ኃይሉ እየተካሄደ ባለው ሰላማዊ ትግል ያገኘነው ዋናው ትምህርት፤ ይህ ትግል፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣኑ ባለቤት በማድረግ በኩል፤ የሚሳካው፤ መላ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት፤ በአንድ የትግል ማዕከል በሚመራ ትግል እንጂ፤ በተናጠል በሚደረግ ትግል አለመሆኑን ነው። መፍትሔ ለማምጣት በአንድነት መሰባሰብ፣ በአንድ ራዕይ መነሳትና መታገል ግድ መሆኑ ተስመረበት። ይህ እልል ያስብላል፤ ልንጠቀምበት ከቻልን።

በዚህ እየተደረገ ባለው ሰላማዊ ትግል፤ አንድ ዋና የኢትዮጵያዊያን ጠላት መኖሩን ተማርንበት። ትግሉ የሚያተኩረው የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣኑ ባለቤት ለማድረግ ነው። ለዚህ ደግሞ ዋናው ጠላት የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባርና የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብቻ ነው። ሥልጣኑ በኢትዮጵያ ሕዝብ እጅ እንዲሆን፤ መላ ታጋዮች ባንድነት መታገል ያለባቸው መሆኑን ሁላችን እናውቃለን። እንዳይሰባሰቡ እስካሁን ያገዳቸው ምንም ሆን ምንም፤ አሁን ካሉበት ወጥተው ወደ ስብስቡ እንዲቀርቡ መንገዱ ግልጽ፣ በሩ ክፍት ሆኗል።

የታጋዮች ወደ አንድ መጠቃለልና ከድርጅቶች ሕልውና ይልቅ የሀገር ጉዳይ ቅድሚያ ማግኘቱ፤ የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያዊት ልብ እንደሚያንኳኳ ጥያቄ አያስፈልገውም። በሩጫ የመጀመሪያው አባል ለመሆን ግን የሚቀድመኝ እንዳይኖር ተዘጋጅቻለሁ። በርግጥ ብዙ እጅግ ብዙ ከኔ በፊት አባል ለመሆን እንደሚሽቀዳደሙ ጥርጥር የለኝም። ሁላችንም እልል እንበልና ለሩጫው እንዘጋጅ። እኔ ጫማዬን አጥልቄያለሁ። eske.meche@yahoo.com በሉ የዚህ ስብስብ ድርጅት አባል አብረን እንሁን።

አንዱዓለም ተፈራ

ተጨማሪ ጽሁፎችን በአቶ አንዱ ዓለም ተፈራ ብሎግ ላይ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule