• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተመስገን “ሰባት ስምንት ፖሊሶች” ከብበውት ወንድሙ አየው

December 16, 2016 01:07 am by Editor Leave a Comment

ላለፉት 10 ቀናት ደብዛው ጠፍቶ የሰነበተው እና በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዝዋይ ማረሚያ ቤት እንዳገኙት ቤተሰቦቹ አስታወቁ፡፡ ቤተሰቦቹ “ተመስገን ዝዋይ የለንም ተብለናል” ሲሉ አቤቱቻቸውን ለተለያዩ አካላት ሲያቀርቡ ሰንብተዋል፡፡ ዛሬ ለጥቂት ደቂቃዎች ተመስገንን መመልከት እንደቻሉና ጤንነቱ መቃወሱን ተናግረዋል፡፡

በጻፋቸው እና ባሳተማቸው ጽሁፎች ክስ ቀርቦበት እና ተፈርዶበት ዝዋይ ማረሚያ ቤት እስሩን እየገፋ ይገኝ የነበረው የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ደብዛ መጥፋት የሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኖ ነዉ የሰነበተዉ፡፡ ከሰብዓዊ መብት ተቋማት እስከ ጋዜጠኛ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ለጉዳዩ አጽንኦት ሰጥተው መግለጫ እስከ ማውጣት እና በማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ እስከመክፈት ደርሰዋል፡

የተመስገን ደሳለኝ ቤተሰቦች በዝዋይ ማረሚያ ቤት “ተመስገን እዚህ የለም” ተብለናል ካሉበት ቀን አንስቶ በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ስር ባሉ የተለያዩ እስር ቤቶች ጋዜጠኛውን ሲያፈላልጉ ቆይተዋል፡፡ ወደ ዝዋይ ማረሚያ ቤትም በየቀኑ በመሄድ ጥያቄቸውን በተደጋጋሚ አቅርበዋል፡፡ እስከዛሬ ረፋድ ድረስ ግን ያገኙት የነበረው ተመሳሳይ ምላሽ “የለም” እንደነበር ሲገልጹ ነበር፡፡

ዛሬ ዓርብ ታሕሳስ 7 ከአዲስ አበባ ወደ ዝዋይ ተጉዞ የነበረው ወንድሙ አላምረው ደሳለኝ ግን አምስት ደቂቃ ላልሞላ ጊዜ ተመስገንን አግኝቶት እንደነበር ለዶይቸ ቨለ ገልጿል፡፡ ወንድሙን እንዴት ለማየት እንደተፈቀደለት በዝርዝር ያስረዳል፡፡

“ከበር ላይ ጠብቅ ቆይ ተባልኩኝ፡፡ ከዚያ ተደዋወሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ይዘውኝ ሄድን፡፡ በፊት በምንጠይቅበት አይደለም፡፡ በሌላ ቦታ ነው፡፡ ገባን፣ አስጠሩት፣ ጠየቅን፡፡ ከሶስት ደቂቃ እንኳ ያልበለጠ ነው፡፡ ምንም ነገር ያወራነው የለም፡፡ ሰባት ስምንት ፖሊሶች አጠገባችን አሉ፡፡ ስንቅ አልያዝንም፡፡ ሰላምታ [ተለዋወጥን]፡፡ ‘ጤንነትህን ስለው?’ ‘ጨጓራዬን በጣም እያመመኝ ነው’ ያለው፡፡ ሌላው በሽታም እንዳለ ነው- ወገቡም፣ ጆሮውም፡፡ ‘ሌላውን ምን ትጠይቀኛለህ?’ ነው ያለኝ፡፡ ‘ጆሮዬንም ያመኛል፤ ህክምና የለም፤ ግን ጨጓራዬን አሁን በጣም እያመመኝ ነው’ አለ፡፡ አሁን ካልኩህ ውጭ ምንም ነገር ማውራት አትችልም፡፡ ተከብቦ ነበር፡፡ ” ሲል የነበረውን ሁኔታ ገልጿል፡፡

የተመስገን ቤተሰቦች ከዚህ ቀደም “መጎብኘት አትችሉም” በሚል ተከልክለው እንደሚያውቁ እንጂ እንዲህ እንዳሁኑ “ጭራሹኑ በዝዋይ ማረሚያ ቤት የለም” የሚል ምላሽ አጋጥሟቸው እንደማያውቅ ይገልጻሉ፡፡ ይህ ሁኔታ በተለይ የ70 አመት አዛውንት የሆኑትን የተመስገንን እናት ለከፍተኛ ጭንቀት እና ህመም ዳርጓቸው እንደነበር አላምረው ይናገራል፡፡ ተመስገንን በኋላም በቀጥታ የደወለው ወደ እርሳቸው ነበር፡፡

“መጀመሪያ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ ሰልኬን ስቀበል ወደ እናቴ ጋር ነው የደውልኩት፡፡ ‘አገኘሁት’ ብቻ ስላት ለረጅም ጊዜ ነው እልል ያለችው፡፡ ጠዋት ስወጣ እንደውም ‘ልጁ ቅዱስ ሚካኤል አባቱ ነው፤ ለእርሱ ሰጥቼያለሁ ከዚህ በኋላ እኔ አቅም የለኝም’ ብላ ነበር፡፡ እናቴ ስለሆነች አይደለም፡፡ ማውራት ሁሉ የለ፡፡ በጣም ተጎሳቁላለች፡፡ በጣም ትጨነቃለች፡፡ እንቅልፍ የለም፣ ጭንቀት ነው፡፡ አሟት ሁሉ ነበር፡፡ ከሦስት ቀን በፊት ሀኪም ቤት ሁሉ ወስደናታል፡፡ ዶክተሩ ‘ምንም ነገር የለም፤ አትጨነቁ’ ነው ያለው ግን የእርሷ ሁኔታ በጣም ይከብድ ነበር” ሲል እናቱ ያሳለፉትን አስጨናቂ ቀናት መለስ ብሎ ያስታውሳል፡፡

ተመስገን ደሳለኝ መገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ፈጽሟል በሚል ሦስት ዓመት እስራት የተበየነበት በጥቅምት 2007 ነበር፡፡ ሁለት ዓመት ከአንድ ወር በእስር ያሳለፈው ተመስገን አመክሮ ቢጠበቅለት ኖሮ ከእስር ተፈቺ እንደነበር ቤተሰቦቹ ይናገራሉ፡፡ ዓለም አቀፉን የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ድርጅት (ሲፒጄን) ጨምሮ ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተቋማት ጋዜጠኛው ሀሳቡን በነጻነት በመግለጹ ምክንያት መታሰር እንደሌለበት ሲያሳስቡ ቆይተዋል፡፡ (ምንጭ: ዶይቸ ቨለ ተስፋለም ወልደየስና ሸዋዬ ለገሠ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule