• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተመስገን “ሰባት ስምንት ፖሊሶች” ከብበውት ወንድሙ አየው

December 16, 2016 01:07 am by Editor Leave a Comment

ላለፉት 10 ቀናት ደብዛው ጠፍቶ የሰነበተው እና በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዝዋይ ማረሚያ ቤት እንዳገኙት ቤተሰቦቹ አስታወቁ፡፡ ቤተሰቦቹ “ተመስገን ዝዋይ የለንም ተብለናል” ሲሉ አቤቱቻቸውን ለተለያዩ አካላት ሲያቀርቡ ሰንብተዋል፡፡ ዛሬ ለጥቂት ደቂቃዎች ተመስገንን መመልከት እንደቻሉና ጤንነቱ መቃወሱን ተናግረዋል፡፡

በጻፋቸው እና ባሳተማቸው ጽሁፎች ክስ ቀርቦበት እና ተፈርዶበት ዝዋይ ማረሚያ ቤት እስሩን እየገፋ ይገኝ የነበረው የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ደብዛ መጥፋት የሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኖ ነዉ የሰነበተዉ፡፡ ከሰብዓዊ መብት ተቋማት እስከ ጋዜጠኛ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ለጉዳዩ አጽንኦት ሰጥተው መግለጫ እስከ ማውጣት እና በማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ እስከመክፈት ደርሰዋል፡

የተመስገን ደሳለኝ ቤተሰቦች በዝዋይ ማረሚያ ቤት “ተመስገን እዚህ የለም” ተብለናል ካሉበት ቀን አንስቶ በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ስር ባሉ የተለያዩ እስር ቤቶች ጋዜጠኛውን ሲያፈላልጉ ቆይተዋል፡፡ ወደ ዝዋይ ማረሚያ ቤትም በየቀኑ በመሄድ ጥያቄቸውን በተደጋጋሚ አቅርበዋል፡፡ እስከዛሬ ረፋድ ድረስ ግን ያገኙት የነበረው ተመሳሳይ ምላሽ “የለም” እንደነበር ሲገልጹ ነበር፡፡

ዛሬ ዓርብ ታሕሳስ 7 ከአዲስ አበባ ወደ ዝዋይ ተጉዞ የነበረው ወንድሙ አላምረው ደሳለኝ ግን አምስት ደቂቃ ላልሞላ ጊዜ ተመስገንን አግኝቶት እንደነበር ለዶይቸ ቨለ ገልጿል፡፡ ወንድሙን እንዴት ለማየት እንደተፈቀደለት በዝርዝር ያስረዳል፡፡

“ከበር ላይ ጠብቅ ቆይ ተባልኩኝ፡፡ ከዚያ ተደዋወሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ይዘውኝ ሄድን፡፡ በፊት በምንጠይቅበት አይደለም፡፡ በሌላ ቦታ ነው፡፡ ገባን፣ አስጠሩት፣ ጠየቅን፡፡ ከሶስት ደቂቃ እንኳ ያልበለጠ ነው፡፡ ምንም ነገር ያወራነው የለም፡፡ ሰባት ስምንት ፖሊሶች አጠገባችን አሉ፡፡ ስንቅ አልያዝንም፡፡ ሰላምታ [ተለዋወጥን]፡፡ ‘ጤንነትህን ስለው?’ ‘ጨጓራዬን በጣም እያመመኝ ነው’ ያለው፡፡ ሌላው በሽታም እንዳለ ነው- ወገቡም፣ ጆሮውም፡፡ ‘ሌላውን ምን ትጠይቀኛለህ?’ ነው ያለኝ፡፡ ‘ጆሮዬንም ያመኛል፤ ህክምና የለም፤ ግን ጨጓራዬን አሁን በጣም እያመመኝ ነው’ አለ፡፡ አሁን ካልኩህ ውጭ ምንም ነገር ማውራት አትችልም፡፡ ተከብቦ ነበር፡፡ ” ሲል የነበረውን ሁኔታ ገልጿል፡፡

የተመስገን ቤተሰቦች ከዚህ ቀደም “መጎብኘት አትችሉም” በሚል ተከልክለው እንደሚያውቁ እንጂ እንዲህ እንዳሁኑ “ጭራሹኑ በዝዋይ ማረሚያ ቤት የለም” የሚል ምላሽ አጋጥሟቸው እንደማያውቅ ይገልጻሉ፡፡ ይህ ሁኔታ በተለይ የ70 አመት አዛውንት የሆኑትን የተመስገንን እናት ለከፍተኛ ጭንቀት እና ህመም ዳርጓቸው እንደነበር አላምረው ይናገራል፡፡ ተመስገንን በኋላም በቀጥታ የደወለው ወደ እርሳቸው ነበር፡፡

“መጀመሪያ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ ሰልኬን ስቀበል ወደ እናቴ ጋር ነው የደውልኩት፡፡ ‘አገኘሁት’ ብቻ ስላት ለረጅም ጊዜ ነው እልል ያለችው፡፡ ጠዋት ስወጣ እንደውም ‘ልጁ ቅዱስ ሚካኤል አባቱ ነው፤ ለእርሱ ሰጥቼያለሁ ከዚህ በኋላ እኔ አቅም የለኝም’ ብላ ነበር፡፡ እናቴ ስለሆነች አይደለም፡፡ ማውራት ሁሉ የለ፡፡ በጣም ተጎሳቁላለች፡፡ በጣም ትጨነቃለች፡፡ እንቅልፍ የለም፣ ጭንቀት ነው፡፡ አሟት ሁሉ ነበር፡፡ ከሦስት ቀን በፊት ሀኪም ቤት ሁሉ ወስደናታል፡፡ ዶክተሩ ‘ምንም ነገር የለም፤ አትጨነቁ’ ነው ያለው ግን የእርሷ ሁኔታ በጣም ይከብድ ነበር” ሲል እናቱ ያሳለፉትን አስጨናቂ ቀናት መለስ ብሎ ያስታውሳል፡፡

ተመስገን ደሳለኝ መገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ፈጽሟል በሚል ሦስት ዓመት እስራት የተበየነበት በጥቅምት 2007 ነበር፡፡ ሁለት ዓመት ከአንድ ወር በእስር ያሳለፈው ተመስገን አመክሮ ቢጠበቅለት ኖሮ ከእስር ተፈቺ እንደነበር ቤተሰቦቹ ይናገራሉ፡፡ ዓለም አቀፉን የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ድርጅት (ሲፒጄን) ጨምሮ ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተቋማት ጋዜጠኛው ሀሳቡን በነጻነት በመግለጹ ምክንያት መታሰር እንደሌለበት ሲያሳስቡ ቆይተዋል፡፡ (ምንጭ: ዶይቸ ቨለ ተስፋለም ወልደየስና ሸዋዬ ለገሠ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule