• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃናን በመድፈር የተጠረጠሩት ክስ ተመሰረተባቸው

December 20, 2014 02:34 am by Editor 4 Comments

በ16 ዓመቷ ታዳጊ ሃና ላላንጎ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በመፈፀም ለሞት አብቅተዋታል በተባሉ አምስት ተጠርጣሪዎች ላይ የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ክስ መሰረተባቸው። ዐቃቤ ሕግ ትናንት ማክሰኞ ታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ ሁለት ሲሆን፤ ለአካለመጠን ያልደረሰችን ሴት በአሰቃቂ ሁኔታ መድፈር እና ከባድ የሰው መግደል ወንጀል የሚሉት ክሶች ተጠቅሶባቸዋል። ከትናንት በስቲያ ሜክሲኮ በሚገኘው በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የነበረውን የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ያጠናቀቀው ይህ ጉዳይ ከዚህ በኋላም በልደታ ፍርድ ቤት መታየቱን ይቀጥላል።

በመሆኑም በዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ዝርዝር ውስጥ ስማቸው የተጠቀሰው አምስቱ ተጠርጣሪዎች 1ኛ ተከሳሽ ሳምሶን ስለሺ ሙያ ሹፌር፣ 2ኛ ተከሳሽ በዛብህ ገ/ማርያም ሾፌር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቃሉ ገ/መድህን የታክሲ ረዳት፣ 4ኛ ተከሳሽ ኤፍሬም አየለ የታክሲ ረዳት እና 5ኛ ተከሳሽ ተመስገን ፀጋዬ ሾፌር ናቸው። ትናንት በችሎት ቀርበው ማንነታቸውን ለፍርድ ቤቱ ያረጋገጡ ሲሆን፤ የተከሰሱበት ወንጀል የዋስትና መብት የማያሰጥ በመሆኑም ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ሲል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

hana3ዐቃቤ ሕግ በክስ ዝርዝሩ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ለመፈፀም አስበው መስከረም 20 ቀን 2007 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 11 ሰዓት ሲሆን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ልዩ ስሙ ጦር ኃይሎች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ16 ዓመት ዕድሜ ያላትን ታዳጊ ሟች ሃና ላላንጎን ታክሲ ቆማ በምትጠብቅበት ወቅት 1ኛ ተከሳሽ ከሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-21253 አ.አ. ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ጠርቶ በማስገባት ቀራኒዮ አደባባይ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ አብረው እስከምሽቱ 2፡30 ከቆዩ በኋላ 1ኛ ተከሳሽ 2ኛ ተከሳሽን በስልክ ደውሎ በመጥራት፤ 2ኛ ተከሳሽም በሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-17035 አ.አ. ሚኒባስ ታክሲ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾችን ይዞ በመምጣት ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር በመገናኘት ሟችን ወደቤቱ ይዞ እንደወሰዳትና እርሱም የሚያሽከረክረውን ታክሲ አቁሞ ተመልሶ እንደሚያገኛቸው በመናገር 4ኛ ተከሳሽ ደግሞ ሟችን 2ኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው ታክሲ እንድትገባ በማድረግ 2ኛ፣ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ሟችን ይዘዋት ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ልዩ ቦታው አንቺን አሉ ህንፃ አካባቢ ከሚገኘው የ2ኛ እና የ3ኛ ተከሳሾች መኖሪያ ቤት በመውሰድ በግምት ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ሌሊቱን በሙሉ ሁሉም ተከሳሾች እየተፈራረቁ በአሰቃቂ ሁኔታ የግብረስጋ ግንኙነት ሲፈፅሙባት ያደሩ በመሆኑ ዐቃቤ ሕግ 18 ዓመት ባልሞላቸው ልጆች ላይ የሚፈፀም የግብረስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ከስሻቸዋለሁ ይላል።

በሁለተኛው ክስ ስርም ተከሳሾቹ ድርጊታቸው ህገወጥና የሚያስቀጣ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል እያወቁ በግዴለሽነት እየተፈራረቁ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል እንደፈፀሙባት፤ የድረሱልኝ ጥሪ እያሰማች ማህፀኗ እየደማ በተለይ ጨካኝነታቸውን፣ ነውረኝነታቸውን እና አደገኝነታቸውን በሚያሳይ ሁኔታ ለአምስት ቀናት አቆይተዋታል ይላል ዐቃቤ ሕግ በክሱ፤ ከዚያም ከአምስት ቀናት በኋላ 2ኛ ተከሳሽ በ3ኛ ተከሳሽ አማካኝነት ሟችን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ልዩ ቦታው ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ወስደው ጥለዋታል፡፡ ለመጣል ሟች በደረሰባት ጉዳት የሰውነት ክፍሎቿ ስራ በማቆማቸውና ብዛት ያለው ደም የፈሰሳት በመሆኑ ከቀናት በኋላ ህይወቷ ያለፈ በመሆኑ በፈፀሙት ከባድ የሰው መግደል ወንጀል ተከሰዋል ይላል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎትም በትናንትናው ዕለት የተከሳሾችን ማንነት በማጣራትና ክሱ እንዲደርሳቸው በማድረግ፤ በችሎቱ ፊት ክሱ ከመነበቡ በፊት በማረሚያ ቤት ቆይተው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ እና ተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ የማቆም አቅም የለንም በማለታቸውም መንግሥት ጠበቃ እንዲቆምላቸው ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡ ክሱን ለማንበብም ለታህሳስ 30 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። (ምንጭ: ሰንደቅ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. ስለሺ says

    December 22, 2014 01:04 pm at 1:04 pm

    አስተማሪ የሆነ ቅጣት በአፋጣኝ ልሠጣቸው ይገባል ፡፡ ግቢ ውስጥ ያሉትም ተከራዮችም ሆኑ ነዋሪዎች ልቀጡ ይገባል ፡፡

    Reply
  2. dij mj says

    December 23, 2014 07:30 am at 7:30 am

    ለካ! ሞኞች ናቸዉ የደፈሩ፤ከሞት የምበልጥ ዉሳኔ ካለ ይሰጥ !!!

    Reply
    • Adferes solomon says

      January 10, 2015 11:37 am at 11:37 am

      ቅጣቱ የማያዳግምና ለሌሎች ወጣቶች ከፍተኛ ግንዛቤ የሚሰጥ መሆን አለበት ሌላው በዚህ ወንጀል ላይ ሊጠየቁ የሚችሉ የፖሊሰ አካላቶች ካሉ ሊካተቱ ይገባል

      Reply
  3. Sara says

    January 20, 2015 06:50 pm at 6:50 pm

    Death penalty is a good lesson in future. Right noq.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule