• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃናን በመድፈር የተጠረጠሩት ክስ ተመሰረተባቸው

December 20, 2014 02:34 am by Editor 4 Comments

በ16 ዓመቷ ታዳጊ ሃና ላላንጎ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በመፈፀም ለሞት አብቅተዋታል በተባሉ አምስት ተጠርጣሪዎች ላይ የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ክስ መሰረተባቸው። ዐቃቤ ሕግ ትናንት ማክሰኞ ታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ ሁለት ሲሆን፤ ለአካለመጠን ያልደረሰችን ሴት በአሰቃቂ ሁኔታ መድፈር እና ከባድ የሰው መግደል ወንጀል የሚሉት ክሶች ተጠቅሶባቸዋል። ከትናንት በስቲያ ሜክሲኮ በሚገኘው በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የነበረውን የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ያጠናቀቀው ይህ ጉዳይ ከዚህ በኋላም በልደታ ፍርድ ቤት መታየቱን ይቀጥላል።

በመሆኑም በዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ዝርዝር ውስጥ ስማቸው የተጠቀሰው አምስቱ ተጠርጣሪዎች 1ኛ ተከሳሽ ሳምሶን ስለሺ ሙያ ሹፌር፣ 2ኛ ተከሳሽ በዛብህ ገ/ማርያም ሾፌር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቃሉ ገ/መድህን የታክሲ ረዳት፣ 4ኛ ተከሳሽ ኤፍሬም አየለ የታክሲ ረዳት እና 5ኛ ተከሳሽ ተመስገን ፀጋዬ ሾፌር ናቸው። ትናንት በችሎት ቀርበው ማንነታቸውን ለፍርድ ቤቱ ያረጋገጡ ሲሆን፤ የተከሰሱበት ወንጀል የዋስትና መብት የማያሰጥ በመሆኑም ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ሲል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

hana3ዐቃቤ ሕግ በክስ ዝርዝሩ ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ለመፈፀም አስበው መስከረም 20 ቀን 2007 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 11 ሰዓት ሲሆን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ልዩ ስሙ ጦር ኃይሎች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ16 ዓመት ዕድሜ ያላትን ታዳጊ ሟች ሃና ላላንጎን ታክሲ ቆማ በምትጠብቅበት ወቅት 1ኛ ተከሳሽ ከሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-21253 አ.አ. ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ጠርቶ በማስገባት ቀራኒዮ አደባባይ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ አብረው እስከምሽቱ 2፡30 ከቆዩ በኋላ 1ኛ ተከሳሽ 2ኛ ተከሳሽን በስልክ ደውሎ በመጥራት፤ 2ኛ ተከሳሽም በሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1-17035 አ.አ. ሚኒባስ ታክሲ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾችን ይዞ በመምጣት ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር በመገናኘት ሟችን ወደቤቱ ይዞ እንደወሰዳትና እርሱም የሚያሽከረክረውን ታክሲ አቁሞ ተመልሶ እንደሚያገኛቸው በመናገር 4ኛ ተከሳሽ ደግሞ ሟችን 2ኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው ታክሲ እንድትገባ በማድረግ 2ኛ፣ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ሟችን ይዘዋት ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ልዩ ቦታው አንቺን አሉ ህንፃ አካባቢ ከሚገኘው የ2ኛ እና የ3ኛ ተከሳሾች መኖሪያ ቤት በመውሰድ በግምት ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ሌሊቱን በሙሉ ሁሉም ተከሳሾች እየተፈራረቁ በአሰቃቂ ሁኔታ የግብረስጋ ግንኙነት ሲፈፅሙባት ያደሩ በመሆኑ ዐቃቤ ሕግ 18 ዓመት ባልሞላቸው ልጆች ላይ የሚፈፀም የግብረስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ከስሻቸዋለሁ ይላል።

በሁለተኛው ክስ ስርም ተከሳሾቹ ድርጊታቸው ህገወጥና የሚያስቀጣ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል እያወቁ በግዴለሽነት እየተፈራረቁ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል እንደፈፀሙባት፤ የድረሱልኝ ጥሪ እያሰማች ማህፀኗ እየደማ በተለይ ጨካኝነታቸውን፣ ነውረኝነታቸውን እና አደገኝነታቸውን በሚያሳይ ሁኔታ ለአምስት ቀናት አቆይተዋታል ይላል ዐቃቤ ሕግ በክሱ፤ ከዚያም ከአምስት ቀናት በኋላ 2ኛ ተከሳሽ በ3ኛ ተከሳሽ አማካኝነት ሟችን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ክልል ልዩ ቦታው ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ወስደው ጥለዋታል፡፡ ለመጣል ሟች በደረሰባት ጉዳት የሰውነት ክፍሎቿ ስራ በማቆማቸውና ብዛት ያለው ደም የፈሰሳት በመሆኑ ከቀናት በኋላ ህይወቷ ያለፈ በመሆኑ በፈፀሙት ከባድ የሰው መግደል ወንጀል ተከሰዋል ይላል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎትም በትናንትናው ዕለት የተከሳሾችን ማንነት በማጣራትና ክሱ እንዲደርሳቸው በማድረግ፤ በችሎቱ ፊት ክሱ ከመነበቡ በፊት በማረሚያ ቤት ቆይተው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ እና ተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ የማቆም አቅም የለንም በማለታቸውም መንግሥት ጠበቃ እንዲቆምላቸው ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡ ክሱን ለማንበብም ለታህሳስ 30 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። (ምንጭ: ሰንደቅ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. ስለሺ says

    December 22, 2014 01:04 pm at 1:04 pm

    አስተማሪ የሆነ ቅጣት በአፋጣኝ ልሠጣቸው ይገባል ፡፡ ግቢ ውስጥ ያሉትም ተከራዮችም ሆኑ ነዋሪዎች ልቀጡ ይገባል ፡፡

    Reply
  2. dij mj says

    December 23, 2014 07:30 am at 7:30 am

    ለካ! ሞኞች ናቸዉ የደፈሩ፤ከሞት የምበልጥ ዉሳኔ ካለ ይሰጥ !!!

    Reply
    • Adferes solomon says

      January 10, 2015 11:37 am at 11:37 am

      ቅጣቱ የማያዳግምና ለሌሎች ወጣቶች ከፍተኛ ግንዛቤ የሚሰጥ መሆን አለበት ሌላው በዚህ ወንጀል ላይ ሊጠየቁ የሚችሉ የፖሊሰ አካላቶች ካሉ ሊካተቱ ይገባል

      Reply
  3. Sara says

    January 20, 2015 06:50 pm at 6:50 pm

    Death penalty is a good lesson in future. Right noq.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule