• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአደባባይ የተነገረው እውነት ውሸት ሆኖ ይከስማል ወይም እውነት ሆኖ ይጠበድላል

January 15, 2016 05:55 am by Editor Leave a Comment

ትግርኛ ቋንቋም ያደናብር ጀመረ እንዴ! ዛሬ (ጥር 6) በፌስቡክ ላይ እንዳየሁት አንዲት ሴት ወገብዋን በነጠላዋ አስራ ትግርኛ የማያውቀውንም የሚቀሰቅስ ንግግር ስታደርግ ነበረ፤ የተናገረችው ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበት ነው፤ የሕዝቡን ቀልብ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥራው ነበር ለማለት አያስቸግርም፤ አንዳንድ ትግርኛ ተናጋሪዎች “ጀግና” እያሉ በወያኔ ላይ የተቃውሞ ንግግር ማድረጉዋን ሲገልጹ አንዳንዶቹ የቋንቋው ባለቤቶች ደግሞ በጣም እየተናደዱ የሴትዮዋ ንግግር የተቃውሞ ሳይሆን የድጋፍ ንግግር ነበር እያሉ ይሞግታሉ፤ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተቃውሞንና ድጋፍን ለመለየት ችግር አለባቸው ከማለቴ በፊት ከዚህ በፊት እኔ በትግራይ ሕዝብ ምክንያት የታማሁበትን እንደሚያስታውሰኝ መግለጹ ተገቢ ይመስለኛል፤ የወያኔ ግልጽ ተጽእኖ የትግራይ ሕዝብ በሙሉ በሀሳብ እንዳይለያይ ነው፤ ወያኔ በትግራይ ችጋር የለም ካለ፣ ማንም ትግርኛ ተናጋሪ አጠገቡ በችጋር የሚያቃስት ሰው ቢኖርም የተባለውን መድገምና በትግራይ ችጋር የለም ማለትን መድገም አለበት፤ እንዲህ እያሉ እውነት ከትግርኛ ቋንቋ አይጠፋም ወይ?

ብዙ ሰዎች የተገነዘቡ አይመስለኝም እንጂ ችግሩ ቋንቋን (ማለት ትግርኛን) የትግርኛ ተናጋሪዎች ሞኖፖሊ (የብቻቸው) የማድረግ ጥረት ያለ ቢመስልም፣ ዋናውና ትልቁ አደጋ ሀሳብንም ቀለም እየቀቡ የሚቀበሉትንና የማይቀበሉትን ለመለየት መሞከሩ ነው፡፡

ይቺ ሴት በትግራይም ጉዳይ ይሁን በኢትዮጵያ ጉዳይ አስተያየት የራስዋን አስተያየት ሰጥታለች፤ ትርፋማ የሚሆነው ምን አለች? ምን አስተያየት አቀረበች? ነው እንጂ ወያኔን ተቃውማለች፤ የለም፣ አልተቃወመችም፣ የሚል ነበር፤ መቃወምም፣ መደገፍም መብትዋ መሆኑን ተቀብለን ከተቃውሞዋ ምን እንማራለን? ከድጋፍዋስ ምን እንማራለን? ለትግራይም ሆነ ለኢትዮጵያ (ለትግራይ የሚበጀው ለኢትዮጵያም ይበጃል፡፡)

ወያኔዎች፡– እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ የእውነትን መስቀል ተሸክመው ከትግራይ ብቅ የሚሉ ሰዎች ነበሩ፤ አሉ፤ ይመጣሉ!!! ገብረ መድኅንን፣ አስገደን ከነልጆቹ፣ አብርሃን … እስከዘላለሙ አንረሳቸውም፡፡

(ምንጭ: መስፍን ወልደ ማርያም ብሎግ)
ጥር 2008

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule