• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ “የፌደራል ሥርዓት” ችግሮችና አማራጭ መፍትሄዎች

September 17, 2016 11:01 pm by Editor Leave a Comment

እንደ መግቢያ

ከዚህ በፊት “ኢትዮጵያ የፌደራል ሥርዓትን የምትከተል አገር አይደለችም” ብዬ ፅፌ ነበር። ዛሬም ትንሽ አዳብሬ በዚሁ ላይ ትንታኔ መስጠት አምሮኛል። ይህ ጽሁፍ ደግሞ እንዲነሳልኝ የፈለኩበት ምክንያት በቅርቡ የህወሃት አንጋፋ ታጋዮች የሆኑት አቶ ስዩም መስፍንና አቶ አባይ ፀሃየ በቅርቡ በኢትዮጵያ “ወቅታዊ” ጉዳይ ላይ የተሰኘ መግለጫ ሰጥተው ነበር። የነዚህን ከፍተኛ ባለስልጣናት ንግግር ያዳመጠ ሁሉ የየራሱን ምልከታ ያስቀምጣል። እጅግ ብዙ ሰው ግን አዲስ ነገር የማይገኝበት ወቅታዊ የማይባል ያደርገዋል። አገሪቱን ህዝባዊ ተቃውሞ በሚንጥበት በዚህ ሰአት ቢያንስ ስለብሄራዊ መግባባት ስለ ብሄራዊ እርቅ ስለ ይቅርታ ማውራት ተገቢ ነበር። የፓለቲካ መሪ ምንም እንኳን የያዘው አቅጣጫ ለራሱ አዋጭ ቢመስለውም ነገር ግን ህዝብ ካልተቀበለው ራሱን ይመረምራል። ይህ ግን በኛ ሃገር ፓለቲካ አለመታየቱ ያሳዝናል። ስልጣን ለሚወዱ ባለስልጣናትም የስልጣን እድሜ የሚጨምረው ይቅርታና መታረም መለወጥ ነበር።

tigray-abayበዚህ “ወቅታዊ” በተሰኘው የነዚህ የህወሃት መሪዎች መግለጫ ውስጥ አንድ ነገር ስላስደመመኝ በዚያ ላይ በተለይ ለነዚህ ለሁለቱ መሪዎችና ለተከታዮቻቸው ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። በዚህ ገለፃ ወቅት አቶ ስዩም ስለ ፌደራል ስርአት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት “አለም የሚቀናበት” ነው ይሉናል። እንዴውም የኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት የሌሎች ፌደራል አገሮችን የፌደራል ስርአት የገለበጠ ነው ይላሉ። ይህንን ሲያስረዱ የሌሎች ሃገራት የፌደራል ስርአት ፌደራሉ የተወሰኑ ስልጣኖችን ይሰጥና ከዚያ ቀሪው በሙሉ የኔ ነው ይላል ይሉናል።ይሰስታል አይነት ነው። ስልጣን የሚሸነሽነው ከላይ ያለው የፌደራል ስርአት ነው ይላሉ። በአንፃሩ የኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት ደግሞ የተገነባው ብሄሮች ትንሽ ትንሽ ቆንጥረው ስልጣን ወርውረውለት የተቋቋመ የፌደራል ሥርዓት ሲሆን ብዙውን ስልጣን ግን ብሄሮች ለራሳቸው እየተደሰቱበት እንደሆነ ያስረዱናል። ይህንን ሳዳምጥ አቶ ስዩም በከፍተኛ ሁኔታ የፌደራልን ጽንሰ ሃሳብ አለመረዳታቸውን አሳየኝ። ተከታዮቻቸው ሁሉ እንዲሁ ከተረዱት በውነት ከስረዋል። እኚህ ሰው እንደኔው ተራ ሰው ቢሆኑ አልሟገትም ነበር። ነገር ግን እኚህ ሰውና ፓርቲያቸው ያመኑበትን ተግባራዊ የሚያደርጉና ያደረጉ በመሆናቸው የኝህ ሰው ግንዛቤ አገርን ስላወከ ነው ለሙግት ያስነሳኝ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule