• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብን አፍኖና በኃይል ረግጦ መግዛት ያብቃ!

August 1, 2016 08:13 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው እሁድ ትንሽ ትልቅ፣ ወንድ ሴት፣ ከተሜ ገጠሬ፣ ሳይል የጎንደር ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ወጥቶ ከተማዋን ባጨናነቀ መልኩ የህወሓት አገዛዝ የፈጠረውን የሽብርና የፍርሃት አጥር ሰብሮ በመውጣት የተቃውሞ ድምጹን በሰላማዊ መንገድ አሰምቶ ወደቤቱ ተመልሷል። ምንም እንኳን አገዛዙ የተቃውሞ ሰልፉ እንዳይካሄድ ማናቸውንም እርምጃዎች ቢወስድም፣ ግፍ የበዛበት፣ የቆረጠና የተባበረን ሕዝባዊ ማዕበል የሚመክተው አንዳችም ምድራዊ ኃይል የለምና ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላው መልክ ሕዝቡ ተቃውሞውን አሰምቷል። በዕለቱ ካስተጋባቸው መፈክሮች ውስጥ “በኦሮሚያ የሚደረገው የወገኖቻችን ግድያ ይቁም” የሚለው የጎንደር ሕዝብ ምንጊዜም በኢትዮጵያዊነትና በሀገር አንድነት ላይ ያለው የሚታወቀውን ጠንካራ አቋሙን ያሳየበትና የትግል አጋርነቱን በግልጽ ያንጸባረቀበት ነው።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የሕዝብ መብቶች እንዲከበሩና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተብዬው እንዲሰረዝ በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ላሰሙ ኦሮምኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን አገዛዙ የሰጠው ምላሽ የሕዝብን ቁጣ በኃይል ለማፈን መሞከር ነበር። በዚህም ከአራት መቶ በላይ የሰው ሕይወት ጠፍቷል። የሕዝብን ቁጣ በኃይል መደፍጠጥ እንደማይቻል አገዛዙ የተማረ አለመሆኑን ያለፉት 25 ዓመታት የግፍ አገዝዙ ቁልጭ አድርገው አሳይተውናል። እስካሁን በተለያዩ አካባቢዎች በተጠቀመበት ነጣጥሎ ማዳከምና መምታት በሚለው የማፈኛ ስልቱ በትላንትና ዕለት በምሥራቅ ሐረርጌ በአወዳይ ከተማ ውስጥ ባካሄደው ጭፍጨፋ በርካታ ዜጎችን ሲያቆስል የስድስት ወገኖቻችንን ሕይወት ማጥፋቱን የተለያዩ የዜና አውታሮች ዘግበዋል። ህወሓት በጎንደር በተካሄደው ሰላማዊ ተቃውሞና ሕዝባዊ ማዕበልን መቋቋም እንደማይችል ምናልባት ተረድቶት ይሆናል የሚለውን ግምት ውድቅ እንዳደረገው እነሆ በአወዳይ ከተማ የፈጸመው ጭፍጨፋ ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል። በመሆኑም ይህን ህወሓት የፈጸመውን አረመኔያዊ ድርጊት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አጥብቆ ያወግዛል።

ጆሮ ያለህ ስማ እንዲሉ የህወሓትን አፋኝ፣ ጨፍጫፊ፣ ዘረኛና አምባገነን ቡድን ማስታወስ የምንወደው በዓለም ዙሪያ የነበሩ አምባገነን አገዛዞች ሁሉ በውርደት ከሥልጣን መወገዳቸውን ቢያንስ የመንግሥቱን፣ የሙባረክን፣ የጋዳፊን፣ የሳዳምን…ወ.ዘ.ተ እጣ ፈንታ እንዴት እንደነበረ ነው። ስለዚህ የሥልጣን ምንጭና ባለቤት የሆነውን ሕዝብ መብት
አፍኖና በኃይል ረግጦ ለዘለዓለም መግዛት እንደማይቻል ተረድቶ ሕዝብ ለእልቂት፣ ሀገርም ለበለጠ ጉዳት ከመዳረጓ በፊት መብቱን በሰላም ለጠየቀ ሕዝብ ትክክለኛው ምላሽ እንዲሰጠው ይገባል እንላለን። ይህ ሳይሆን ቢቀርና ህወሓት እስካሁን በተከተለው ጎዳና ከቀጠለ ለሚደርሰው የሕይወት መጥፋትና የንብረት መውደም ተጠያቂው ህወሓት ብቻ
መሆኑን ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን። ሕዝቡ የሀገር አንድነቱን ጠብቆ መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለማስከበር የሚያደርገውን ትግል የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ እንደሚደግፍ በማያሻማ ቋንቋ እየገለጸ፣ በሚችለው ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል።

አንድነቷ የተጠበቀ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ በሕዝብ ትግል ትመሠረታለች!

ሐምሌ 26 ቀን 2008 ዓ. ም (August 2, 2016)

Tel: 44 7937600756 , +1 9168486790 E-mail : shengo.derbiaber@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule