• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብን አፍኖና በኃይል ረግጦ መግዛት ያብቃ!

August 1, 2016 08:13 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው እሁድ ትንሽ ትልቅ፣ ወንድ ሴት፣ ከተሜ ገጠሬ፣ ሳይል የጎንደር ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ወጥቶ ከተማዋን ባጨናነቀ መልኩ የህወሓት አገዛዝ የፈጠረውን የሽብርና የፍርሃት አጥር ሰብሮ በመውጣት የተቃውሞ ድምጹን በሰላማዊ መንገድ አሰምቶ ወደቤቱ ተመልሷል። ምንም እንኳን አገዛዙ የተቃውሞ ሰልፉ እንዳይካሄድ ማናቸውንም እርምጃዎች ቢወስድም፣ ግፍ የበዛበት፣ የቆረጠና የተባበረን ሕዝባዊ ማዕበል የሚመክተው አንዳችም ምድራዊ ኃይል የለምና ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላው መልክ ሕዝቡ ተቃውሞውን አሰምቷል። በዕለቱ ካስተጋባቸው መፈክሮች ውስጥ “በኦሮሚያ የሚደረገው የወገኖቻችን ግድያ ይቁም” የሚለው የጎንደር ሕዝብ ምንጊዜም በኢትዮጵያዊነትና በሀገር አንድነት ላይ ያለው የሚታወቀውን ጠንካራ አቋሙን ያሳየበትና የትግል አጋርነቱን በግልጽ ያንጸባረቀበት ነው።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ የሕዝብ መብቶች እንዲከበሩና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተብዬው እንዲሰረዝ በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ላሰሙ ኦሮምኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን አገዛዙ የሰጠው ምላሽ የሕዝብን ቁጣ በኃይል ለማፈን መሞከር ነበር። በዚህም ከአራት መቶ በላይ የሰው ሕይወት ጠፍቷል። የሕዝብን ቁጣ በኃይል መደፍጠጥ እንደማይቻል አገዛዙ የተማረ አለመሆኑን ያለፉት 25 ዓመታት የግፍ አገዝዙ ቁልጭ አድርገው አሳይተውናል። እስካሁን በተለያዩ አካባቢዎች በተጠቀመበት ነጣጥሎ ማዳከምና መምታት በሚለው የማፈኛ ስልቱ በትላንትና ዕለት በምሥራቅ ሐረርጌ በአወዳይ ከተማ ውስጥ ባካሄደው ጭፍጨፋ በርካታ ዜጎችን ሲያቆስል የስድስት ወገኖቻችንን ሕይወት ማጥፋቱን የተለያዩ የዜና አውታሮች ዘግበዋል። ህወሓት በጎንደር በተካሄደው ሰላማዊ ተቃውሞና ሕዝባዊ ማዕበልን መቋቋም እንደማይችል ምናልባት ተረድቶት ይሆናል የሚለውን ግምት ውድቅ እንዳደረገው እነሆ በአወዳይ ከተማ የፈጸመው ጭፍጨፋ ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል። በመሆኑም ይህን ህወሓት የፈጸመውን አረመኔያዊ ድርጊት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አጥብቆ ያወግዛል።

ጆሮ ያለህ ስማ እንዲሉ የህወሓትን አፋኝ፣ ጨፍጫፊ፣ ዘረኛና አምባገነን ቡድን ማስታወስ የምንወደው በዓለም ዙሪያ የነበሩ አምባገነን አገዛዞች ሁሉ በውርደት ከሥልጣን መወገዳቸውን ቢያንስ የመንግሥቱን፣ የሙባረክን፣ የጋዳፊን፣ የሳዳምን…ወ.ዘ.ተ እጣ ፈንታ እንዴት እንደነበረ ነው። ስለዚህ የሥልጣን ምንጭና ባለቤት የሆነውን ሕዝብ መብት
አፍኖና በኃይል ረግጦ ለዘለዓለም መግዛት እንደማይቻል ተረድቶ ሕዝብ ለእልቂት፣ ሀገርም ለበለጠ ጉዳት ከመዳረጓ በፊት መብቱን በሰላም ለጠየቀ ሕዝብ ትክክለኛው ምላሽ እንዲሰጠው ይገባል እንላለን። ይህ ሳይሆን ቢቀርና ህወሓት እስካሁን በተከተለው ጎዳና ከቀጠለ ለሚደርሰው የሕይወት መጥፋትና የንብረት መውደም ተጠያቂው ህወሓት ብቻ
መሆኑን ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን። ሕዝቡ የሀገር አንድነቱን ጠብቆ መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለማስከበር የሚያደርገውን ትግል የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ እንደሚደግፍ በማያሻማ ቋንቋ እየገለጸ፣ በሚችለው ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል።

አንድነቷ የተጠበቀ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ በሕዝብ ትግል ትመሠረታለች!

ሐምሌ 26 ቀን 2008 ዓ. ም (August 2, 2016)

Tel: 44 7937600756 , +1 9168486790 E-mail : shengo.derbiaber@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule