• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸንጎ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚያገለግለውን አመራር መረጠ

October 24, 2015 09:33 am by Editor 1 Comment

በኦታዋ ካናዳ በተካሄደው ጉባኤ በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2012 የተመሠረተውና የኢትዮጵያ የአንድነት ኃይሎች ትልቁ ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣ (ሸንጎ) በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምክር ቤት ስብሰባ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ድርጅቱን የሚመሩ የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባላትን መርጧል።

በዚህም መሰረት ከስራ አስኪያጅ ኮሚቴው አባላት ውስጥ ዶክተር ታዬ ዘገዬን፣ ሊቀመንበር ወይዘሮ ጽጌረዳ ሙሉጌታን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ግደይ ዘርአጽዮንን ዋና ጸሀፊ እና አቶ መሐመድ ጀሚልን ምክትል ዋና ጸሀፊ አድርጎ መርጧል፡፡ የተቀሩት የኮሚቴው አባላት ደግሞ የተለያዩ የተግባር ኮሚቴወችን በኃላፊነት ይመራሉ።

ሸንጎው በቅርቡ አጠቃላይ ጉባዔ በማካሄድ ኢትዮጵያችንና ሕዝቧ የሚገኙበትን ሁኔታ በጥልቅ ከመረመረ በኋላ ሀገራችን ከምትገኝበት አስከፊና አደገኛ የግፍ ሥርዓት ተላቃ አንድነቷ ተጠብቆ እኩልነት፣ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲሁም የህግ የበላይነት ወደ ተከበረበት ለሁሉም ዜጎቿ የሚሆን ህገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለመሸጋገር የሚያስችለውን ለውጥ እውን ለማድረግ መደረግ በሚገባቸው መሠረታዊ ጎዳዮች ላይ የትግል አቅጣጫ ነድፏል።

ይሀ አሁን የተመረጠው የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ ብቻ ሳይሆን በአንድነት ኃይሎችም ላይ የተነጣጠረውን ጥቃት በመመከትና የአንድነት ኃይሎችን በማጠናከር የሕዝባችን የነፃነት ራዕይ እውን እንዲሆን ለማስቻል ከፍተኛ አደራን ተቀብሏል።

ይህን ለማድረግም ከባዕዳን ተጽእኖ ነፃ ሆኖ ራሱ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን ሕዝብ ያማከለና መሠረት ያደረገ ትግልን አጠናክሮ ይቀጥላል።

የሸንጎው የጋራ አቋሞች

  • በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት በሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነትና ሉዓላዊነት ላይ የማያወላውል እምነት
  • ፍትህ የሰፈነበትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ጸንቶ መታገል
  • ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቹ መከበር አለባቸው ብሎ ማመን
  • በኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል ምንም ዓይነት አድሏዊነት እንዳይኖርና ኢትዮጵያውያን ሁሉ በሕግ ፊትና በሶሻልና የፖለቲካ ነፃነታቸው እኩል ዜጎች መሆናቸውን በተግባር ማረጋገጥ
  • የህወሀት/ኢህአዴግ መንግስትና አገዛዝ ሥርዓት የአፈናና የጭቆና ሥርዓት በመሆኑ መለወጥና በህገ-መንግሥታዊ ዴሞክራሲያዊ የአስተዳደር ሥርዓት መተካት እንዳለበት መቀበል

የሚሉት ሲሆኑ እነዚህን መሠረታዊ መተክሎች የሚቀበል ማንኛውም ግለሰብ፤ ስብስብ ወይም ድርጅት ሸንጎውን በመቀላቀል ወይም በጋራ በመሥራት ሕዝባችንንና ሀገራችንን በጋራ እንድንታደግ ጥሪያችንን በድጋሜ እናቀርባለን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

ጥቅምት 13፣ 2008 (ኦክቶበር 24፣ 2015)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    November 4, 2015 02:33 pm at 2:33 pm

    I donot see the difference between your goals and that of AG7 so would you please elaborate. I thought your group is just “alen lemalet” and in preparation for another London conference just to have parliamentary sits or power. If you really care for Ethiopia and Ethiopians right to choose their leaders narrow your differences with AG7 and fight together to shorten the suffering of our people and the disintegration of Ethiopia.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule