• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸንጎ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚያገለግለውን አመራር መረጠ

October 24, 2015 09:33 am by Editor 1 Comment

በኦታዋ ካናዳ በተካሄደው ጉባኤ በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2012 የተመሠረተውና የኢትዮጵያ የአንድነት ኃይሎች ትልቁ ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣ (ሸንጎ) በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምክር ቤት ስብሰባ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ድርጅቱን የሚመሩ የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባላትን መርጧል።

በዚህም መሰረት ከስራ አስኪያጅ ኮሚቴው አባላት ውስጥ ዶክተር ታዬ ዘገዬን፣ ሊቀመንበር ወይዘሮ ጽጌረዳ ሙሉጌታን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ግደይ ዘርአጽዮንን ዋና ጸሀፊ እና አቶ መሐመድ ጀሚልን ምክትል ዋና ጸሀፊ አድርጎ መርጧል፡፡ የተቀሩት የኮሚቴው አባላት ደግሞ የተለያዩ የተግባር ኮሚቴወችን በኃላፊነት ይመራሉ።

ሸንጎው በቅርቡ አጠቃላይ ጉባዔ በማካሄድ ኢትዮጵያችንና ሕዝቧ የሚገኙበትን ሁኔታ በጥልቅ ከመረመረ በኋላ ሀገራችን ከምትገኝበት አስከፊና አደገኛ የግፍ ሥርዓት ተላቃ አንድነቷ ተጠብቆ እኩልነት፣ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲሁም የህግ የበላይነት ወደ ተከበረበት ለሁሉም ዜጎቿ የሚሆን ህገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለመሸጋገር የሚያስችለውን ለውጥ እውን ለማድረግ መደረግ በሚገባቸው መሠረታዊ ጎዳዮች ላይ የትግል አቅጣጫ ነድፏል።

ይሀ አሁን የተመረጠው የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ ብቻ ሳይሆን በአንድነት ኃይሎችም ላይ የተነጣጠረውን ጥቃት በመመከትና የአንድነት ኃይሎችን በማጠናከር የሕዝባችን የነፃነት ራዕይ እውን እንዲሆን ለማስቻል ከፍተኛ አደራን ተቀብሏል።

ይህን ለማድረግም ከባዕዳን ተጽእኖ ነፃ ሆኖ ራሱ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን ሕዝብ ያማከለና መሠረት ያደረገ ትግልን አጠናክሮ ይቀጥላል።

የሸንጎው የጋራ አቋሞች

  • በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት በሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነትና ሉዓላዊነት ላይ የማያወላውል እምነት
  • ፍትህ የሰፈነበትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ጸንቶ መታገል
  • ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቹ መከበር አለባቸው ብሎ ማመን
  • በኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል ምንም ዓይነት አድሏዊነት እንዳይኖርና ኢትዮጵያውያን ሁሉ በሕግ ፊትና በሶሻልና የፖለቲካ ነፃነታቸው እኩል ዜጎች መሆናቸውን በተግባር ማረጋገጥ
  • የህወሀት/ኢህአዴግ መንግስትና አገዛዝ ሥርዓት የአፈናና የጭቆና ሥርዓት በመሆኑ መለወጥና በህገ-መንግሥታዊ ዴሞክራሲያዊ የአስተዳደር ሥርዓት መተካት እንዳለበት መቀበል

የሚሉት ሲሆኑ እነዚህን መሠረታዊ መተክሎች የሚቀበል ማንኛውም ግለሰብ፤ ስብስብ ወይም ድርጅት ሸንጎውን በመቀላቀል ወይም በጋራ በመሥራት ሕዝባችንንና ሀገራችንን በጋራ እንድንታደግ ጥሪያችንን በድጋሜ እናቀርባለን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

ጥቅምት 13፣ 2008 (ኦክቶበር 24፣ 2015)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    November 4, 2015 02:33 pm at 2:33 pm

    I donot see the difference between your goals and that of AG7 so would you please elaborate. I thought your group is just “alen lemalet” and in preparation for another London conference just to have parliamentary sits or power. If you really care for Ethiopia and Ethiopians right to choose their leaders narrow your differences with AG7 and fight together to shorten the suffering of our people and the disintegration of Ethiopia.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule