• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸንጎ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚያገለግለውን አመራር መረጠ

October 24, 2015 09:33 am by Editor 1 Comment

በኦታዋ ካናዳ በተካሄደው ጉባኤ በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2012 የተመሠረተውና የኢትዮጵያ የአንድነት ኃይሎች ትልቁ ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣ (ሸንጎ) በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምክር ቤት ስብሰባ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ድርጅቱን የሚመሩ የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባላትን መርጧል።

በዚህም መሰረት ከስራ አስኪያጅ ኮሚቴው አባላት ውስጥ ዶክተር ታዬ ዘገዬን፣ ሊቀመንበር ወይዘሮ ጽጌረዳ ሙሉጌታን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ግደይ ዘርአጽዮንን ዋና ጸሀፊ እና አቶ መሐመድ ጀሚልን ምክትል ዋና ጸሀፊ አድርጎ መርጧል፡፡ የተቀሩት የኮሚቴው አባላት ደግሞ የተለያዩ የተግባር ኮሚቴወችን በኃላፊነት ይመራሉ።

ሸንጎው በቅርቡ አጠቃላይ ጉባዔ በማካሄድ ኢትዮጵያችንና ሕዝቧ የሚገኙበትን ሁኔታ በጥልቅ ከመረመረ በኋላ ሀገራችን ከምትገኝበት አስከፊና አደገኛ የግፍ ሥርዓት ተላቃ አንድነቷ ተጠብቆ እኩልነት፣ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲሁም የህግ የበላይነት ወደ ተከበረበት ለሁሉም ዜጎቿ የሚሆን ህገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለመሸጋገር የሚያስችለውን ለውጥ እውን ለማድረግ መደረግ በሚገባቸው መሠረታዊ ጎዳዮች ላይ የትግል አቅጣጫ ነድፏል።

ይሀ አሁን የተመረጠው የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ በሀገራችንና በሕዝባችን ላይ ብቻ ሳይሆን በአንድነት ኃይሎችም ላይ የተነጣጠረውን ጥቃት በመመከትና የአንድነት ኃይሎችን በማጠናከር የሕዝባችን የነፃነት ራዕይ እውን እንዲሆን ለማስቻል ከፍተኛ አደራን ተቀብሏል።

ይህን ለማድረግም ከባዕዳን ተጽእኖ ነፃ ሆኖ ራሱ የጉዳዩ ባለቤት የሆነውን ሕዝብ ያማከለና መሠረት ያደረገ ትግልን አጠናክሮ ይቀጥላል።

የሸንጎው የጋራ አቋሞች

  • በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት በሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነትና ሉዓላዊነት ላይ የማያወላውል እምነት
  • ፍትህ የሰፈነበትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ጸንቶ መታገል
  • ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቹ መከበር አለባቸው ብሎ ማመን
  • በኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል ምንም ዓይነት አድሏዊነት እንዳይኖርና ኢትዮጵያውያን ሁሉ በሕግ ፊትና በሶሻልና የፖለቲካ ነፃነታቸው እኩል ዜጎች መሆናቸውን በተግባር ማረጋገጥ
  • የህወሀት/ኢህአዴግ መንግስትና አገዛዝ ሥርዓት የአፈናና የጭቆና ሥርዓት በመሆኑ መለወጥና በህገ-መንግሥታዊ ዴሞክራሲያዊ የአስተዳደር ሥርዓት መተካት እንዳለበት መቀበል

የሚሉት ሲሆኑ እነዚህን መሠረታዊ መተክሎች የሚቀበል ማንኛውም ግለሰብ፤ ስብስብ ወይም ድርጅት ሸንጎውን በመቀላቀል ወይም በጋራ በመሥራት ሕዝባችንንና ሀገራችንን በጋራ እንድንታደግ ጥሪያችንን በድጋሜ እናቀርባለን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

ጥቅምት 13፣ 2008 (ኦክቶበር 24፣ 2015)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    November 4, 2015 02:33 pm at 2:33 pm

    I donot see the difference between your goals and that of AG7 so would you please elaborate. I thought your group is just “alen lemalet” and in preparation for another London conference just to have parliamentary sits or power. If you really care for Ethiopia and Ethiopians right to choose their leaders narrow your differences with AG7 and fight together to shorten the suffering of our people and the disintegration of Ethiopia.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule