• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእርስ በእርስ ግጭት ነገሶበት የከረመው በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ በሰላም ተጠናቀቀ

February 23, 2014 07:55 am by Editor Leave a Comment

 በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚቴ ማህበር ስራ አመራር አባላት እና በቀድሞው የማህበሩ ሊቀመንበር ደጋፊዎች መሃከል በተፈጠረው የስልጣን ሽኩቻ በአባላቱ ላይ አጥልቶ የነበረው የእርስ በእስር ግጨት መቀልበሱን ምንጮች ከሪያድ አስታወቁ። ፌብረዋሪ 21 2014 ምሸት ሲጠበቅ የነበረው በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ በሪያድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደስታቸውን በመግለጽ ፈጣሪያቸውን አመስግነዋል ብለዋል፡፤

በጉባኤው ላይ ከኤንባሲው የተወከሉ ዲፕሎማቶች በታዛቢነት መገኘታቸውን የጠቀሱት አንድ የጉባኤው ተሳታፊ በስራ አመራሩ እና በሼክ መስጠፋ ሁሴን መሃከል ተከስቶ የነበረው ልዩነት በዲፕሎማቱ ብለሃት ከወዲሁ መቀልበሱን ጠቅሰው ስብሰባው ያለምንም ችገር እና ስጋት በሰላም መካሄዱን አረጋግጠዋል። አስተያየት ሰጪው አያይዘው ሲገልጹ ጥቂቶች በብዙሃኑ ደም ዎኝተው የበላይነታቸውን በአቋራጭ ለማረጋገጥ የነበራቸው ህልም መና መቅረቱ የኮሚኒቲው ማህበር ከህግ እና ስረአት ውጭ ለሚንቀሳቀሱ ሃይሎች የማይበገር መሆኑንን ያረጋጋጠበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ብለዋል። በተለይ ይላሉ እኚህ አስተያየት ሰጪ ጉዳይ የሚዲያ ሽፋን አግኝቶ በሚመለከታቸው አካላቶች ትኩረት ሳይሰጠው ቀርቶ ቢሆን ኖሮ አያሌ ወገኖች ዘግናኝ የሆነ ነገር ውስጥ ሊገቡ ይችሉ እንደነበር አውስተው ሶሻል ሚዲያዎች አደጋ ከመድረሱ በፌት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው የህዝቡን እሮሮ በማስተጋባት የኮሚኒቲውን አባላት ከአሰቃቂ ግጨት በመታደጋቸው ሊመስገኑ ይገባልም ብለውል።

በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በዲያስፖራው ዘንድ ተደማጭነት እና ክብር ያላቸው 3 ዲፕሎማቶች ኤንባሲውን ወክለው በታዛቢነት መገኘታቸውን የሚናገሩ ምንጮች ስብሰባው ያለምንም ስጋት እና ሁከት በሰላም እንዲካሄድ ለማስቻል ከፍተኛ አስተዋጾ ማድረጋቸውን አክለው ገልጸዋል። በስብሰው ወቅት የኮሚኒቲው ስራ አመራር የ20 ወራቱን የስራ ሪፖርት በማስደመጥ በአባልቱ መሃከል ከፍተኛ ውይይት መድረጉን የሚናገሩ እማኞች በስራ አመራሩ የቀረበው ሪፖርት በአብዛኛው አባላት ዘንድ ተቃውሞ ገጥሞት እንደነበር ሳይሽሽጉ ተናግረዋል።

በመጨረሻም የኮሚኒቲው ሊቀምንበር አቶ ቃሲም ያሲን በቀረብው ሪፖርት ዙሪያ ከአድማጮች ለቀረበላቸው ጥያቄ ማብራሪያ በመስጠት በጉባኤው ተሳታፊዎች ዘንድ ሰፊ ውይይት ከመደረጉም በላይ የኮሚኒቲው ሁለገብ የመዝናኛ ማዕከል በኮንተራት ለግለስቦች ቢተላለፍ የበለጠ ውጤታማ መሆን እንደሚችል ከአንድ አድማጭ የተሰነዘረውን ሃሳብ የኤንባሲው ተወካይ ክቡር አቶ ተመስገን ኡመር የኮሚኒቲው ንበረት ለዲያስፖራው ያለውን አጋርነት እና ጠቀሜታ በዝርዝር በማስቀመጥ የኮሚኒቲው ንብረቶች በኤንባሲው ስር እንደመሆናቸው መጠን አካሄዱ ህጋዊ መስረት ሊኖረው ስለማይችል የቀርበውን ሃሳብ ውድቅ በማድረግ ተቀባይነት እንደሌለው አረጋግጠዋል፡፤

የማህበሩ ሁለገብ የመዝናኛ ማዕከል የሆነው ካፍቴሪያ ዘንድሮም 61 ሺህ ሪያል ኪሳራ ማሳየቱን ከቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል። በዚህ ስብሰባ ላይ የሃይማኖት አባቶች የህገር ሽማግሌዎች ጨምሮ ከኤንባሲ 1/ ክቡር አቶ አህመድ ጠላህ 2/ ክቡር አቶ ተመስገን ኡመር 3/ ክቡር አቶ መስፍን ድባቡ መገኘታቸውን የሚገልጹ የኮሚኒቲው አባላት ከስጋት እና ጭንቀት ይልቅ የጉባኤውን ምሸት በነጻነት ማሳለፋቸውን አስረድተዋል። ለጉባኤው የቀረበ የተባለው ሪፖርት ግልባጭ በእጃችን እንደገባ ሰሞኑን በዚህ ገጽ በስፋት ለመዳሰስ ይሞከራል።

(Ethiopian Hagere ከጅዳ በዋዲ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule