• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል

September 6, 2017 02:15 am by Editor Leave a Comment

የህወሃት አገዛዝ 2010 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ለማክበር የጀመረውን ከባህሪው የወጣ ድርጊት ተመልክተው አንዳንዶች ስርዓቱ እውነተኛ የመንግስትነት ባህርይን እየያዘ ነው ሲሉ ይደመጣል። እነዚህ የዋሆች  ሰሞኑን ከነሀሴ 26 ቀን ጀምሮ የፍቅር ቀን፣ የእናቶችና ህፃናት ቀን፣ የአረጋውያን ቀን፣ የሰላም ቀን፣ የንባብ ቀን፣ የአረንጓዴ ልማት ቀን፣ የመከባበር ቀን፣ የሀገር ፍቅር ቀን፣ የአንድነት ቀን እና የኢትዮጵያ ቀን በሚሉ መለያዎች አዲሱን ኣመት ለመቀበል ህወሀት የያዘውን ፕሮግራም እንደ አንድ ማስረጃነት ሲጠቅሱ ይታያል። ታርሟል በሚል። መሬት ላይ የምናያቸው የስርኣቱ ባህርያት በምክንያት ለገመገመ ሰው ግን ስርዓቱ ለመሻሻል ፍላጎት እንደሌለው ይገነዘባል። በእኔ ምልከታ ችግሩ ከድርጅቱ ፍጥረታዊ ባህርይ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገንዝቤአለሁ።

በመጀመሪያ ደረጃ ህወሀት ከምስረታው ጀምሮ በጠላትነት የሚያሳድደው አመለካከት ፍቅር፣ አንድነት እና ኢትዮጵያ የሚለውን ሀይል አይደለም እንዴ? እስከዚህ ሰዓት ድረስ  የተበዳይና የበዳይ ድርሰት እየደረሰ በህዝቦች መካከል ቁርሾ የሚዘራው ማነው? በሌላ በኩል የዘር ብሄርተኝነትን ከሚገባው በላይ በማራገብ ኢትዮጳዊነትን ያኮሰመነ  መንግስትስ ማን ነው? የህወሃት አገዛዝ አይደለምን? ታዲያ አሁን ምን ተገኘ የሚለው በደንብ መታየት ያለበት ይመስለኛል። በእኔ ምልከታ ይህ እርምጃ  ህወሀት በአሁኑ ወቅት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በአንድነት የተነሳበትን ተቃውሞ ለማቀዝቀዣነት የዘረጋው ስልት ነው። የአንድነት ሀይል ነው ተብሎ የሚታሰበውን የአማራ ሀይል ጉርሻ ነገር በመስጠት ማስታገስ ላይ ያነጣጠረ ስልት። በዚህም በቅርቡ በአማራ ክልል በክልል ደረጃ  ለመተግበት ህዝቡ በእቅድ የያዘውን በቤት ውስጥ የመቀመጥ ህዝባዊ አድማ ማለዘብ የስልቱ ዋና አላማ ነው። ይህም ህወሀት ሙሉ ሀይሉኝ በኦሮሚያውና ሌሎች ክልሎች  ላይ እንዲያተኩር ይረዳዋል። ህወሀት እንደዚህ እይነት ብልጣ ብልጥ እርምጃዎች  ይዞ ሲመጣ ይበልጥ ጠንቃቃ መሆን እንዳለብን ልምዳችን አስተምሮናል። ከትንፋሽ በኋላ ይበልጥ አሳሪ ህግና አሰራሮችን ይዞ በበቀል የመጣባቸው ብዙ ልምዶች ስላሉን። ከ1997 ምርጫ ተከትሎ የአንድነት ህይሉን፣ ነጻ ፕሬስ እና ማህበራትን ለማጥፋት የወሰዳቸው እርምጃዎቹን ማስታወስ ይገባል። ድርጅቱ ግለሰብና ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን ከተማዎችንም በቂ በቀል የሚቀጣ መሆኑን ማስታወስ ይገባል።

የህወሀት እታደሳለሁ የሚሉ ለቁጥር አታካች መሀላዎች ያመጡልን ነገር ቢኖር በተደራጀ መንገድ የሚያካሂደው የሀገር ሀብት ዘረፋ መባባስ ነው። የባርነት ሰንሰለቱ ይበልጥ መጥበቅ ነው። የህዝቦች እርስ በርስ ጥላቻ መበራከት ሌላው ህወሀት እድሜው በጨመረ ቁጥር አብረው የጨመሩ ክስተቶች ናቸው። ስለዚህ “ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል” ብለናል። ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መመስረት ሀገራችን ያላት መንገዱ አንድ ብቻ ነው። ህዝቦች መሪዎቻቸውን በምርጫ ካርድ ወደ ስልጣን የሚያመጡበት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት መዘርጋት ብቻ። ለዚህም ከተጽህኖ ነጻ የመከላከያና ፖሊስ ሰራዊቶች፣ ነጻ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም እንደ ኬንያው  ነጻ ፍርድ ቤቶች በህዝቦች ንቁ ተሳትፎና ውሳኔ ሰጪነት በአጭር ወቅት መገንባት ይኖርባቸዋል።

ያሬድ አውግቸው (yaredawgichew@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule