• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል

September 6, 2017 02:15 am by Editor Leave a Comment

የህወሃት አገዛዝ 2010 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ለማክበር የጀመረውን ከባህሪው የወጣ ድርጊት ተመልክተው አንዳንዶች ስርዓቱ እውነተኛ የመንግስትነት ባህርይን እየያዘ ነው ሲሉ ይደመጣል። እነዚህ የዋሆች  ሰሞኑን ከነሀሴ 26 ቀን ጀምሮ የፍቅር ቀን፣ የእናቶችና ህፃናት ቀን፣ የአረጋውያን ቀን፣ የሰላም ቀን፣ የንባብ ቀን፣ የአረንጓዴ ልማት ቀን፣ የመከባበር ቀን፣ የሀገር ፍቅር ቀን፣ የአንድነት ቀን እና የኢትዮጵያ ቀን በሚሉ መለያዎች አዲሱን ኣመት ለመቀበል ህወሀት የያዘውን ፕሮግራም እንደ አንድ ማስረጃነት ሲጠቅሱ ይታያል። ታርሟል በሚል። መሬት ላይ የምናያቸው የስርኣቱ ባህርያት በምክንያት ለገመገመ ሰው ግን ስርዓቱ ለመሻሻል ፍላጎት እንደሌለው ይገነዘባል። በእኔ ምልከታ ችግሩ ከድርጅቱ ፍጥረታዊ ባህርይ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገንዝቤአለሁ።

በመጀመሪያ ደረጃ ህወሀት ከምስረታው ጀምሮ በጠላትነት የሚያሳድደው አመለካከት ፍቅር፣ አንድነት እና ኢትዮጵያ የሚለውን ሀይል አይደለም እንዴ? እስከዚህ ሰዓት ድረስ  የተበዳይና የበዳይ ድርሰት እየደረሰ በህዝቦች መካከል ቁርሾ የሚዘራው ማነው? በሌላ በኩል የዘር ብሄርተኝነትን ከሚገባው በላይ በማራገብ ኢትዮጳዊነትን ያኮሰመነ  መንግስትስ ማን ነው? የህወሃት አገዛዝ አይደለምን? ታዲያ አሁን ምን ተገኘ የሚለው በደንብ መታየት ያለበት ይመስለኛል። በእኔ ምልከታ ይህ እርምጃ  ህወሀት በአሁኑ ወቅት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በአንድነት የተነሳበትን ተቃውሞ ለማቀዝቀዣነት የዘረጋው ስልት ነው። የአንድነት ሀይል ነው ተብሎ የሚታሰበውን የአማራ ሀይል ጉርሻ ነገር በመስጠት ማስታገስ ላይ ያነጣጠረ ስልት። በዚህም በቅርቡ በአማራ ክልል በክልል ደረጃ  ለመተግበት ህዝቡ በእቅድ የያዘውን በቤት ውስጥ የመቀመጥ ህዝባዊ አድማ ማለዘብ የስልቱ ዋና አላማ ነው። ይህም ህወሀት ሙሉ ሀይሉኝ በኦሮሚያውና ሌሎች ክልሎች  ላይ እንዲያተኩር ይረዳዋል። ህወሀት እንደዚህ እይነት ብልጣ ብልጥ እርምጃዎች  ይዞ ሲመጣ ይበልጥ ጠንቃቃ መሆን እንዳለብን ልምዳችን አስተምሮናል። ከትንፋሽ በኋላ ይበልጥ አሳሪ ህግና አሰራሮችን ይዞ በበቀል የመጣባቸው ብዙ ልምዶች ስላሉን። ከ1997 ምርጫ ተከትሎ የአንድነት ህይሉን፣ ነጻ ፕሬስ እና ማህበራትን ለማጥፋት የወሰዳቸው እርምጃዎቹን ማስታወስ ይገባል። ድርጅቱ ግለሰብና ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን ከተማዎችንም በቂ በቀል የሚቀጣ መሆኑን ማስታወስ ይገባል።

የህወሀት እታደሳለሁ የሚሉ ለቁጥር አታካች መሀላዎች ያመጡልን ነገር ቢኖር በተደራጀ መንገድ የሚያካሂደው የሀገር ሀብት ዘረፋ መባባስ ነው። የባርነት ሰንሰለቱ ይበልጥ መጥበቅ ነው። የህዝቦች እርስ በርስ ጥላቻ መበራከት ሌላው ህወሀት እድሜው በጨመረ ቁጥር አብረው የጨመሩ ክስተቶች ናቸው። ስለዚህ “ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል” ብለናል። ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መመስረት ሀገራችን ያላት መንገዱ አንድ ብቻ ነው። ህዝቦች መሪዎቻቸውን በምርጫ ካርድ ወደ ስልጣን የሚያመጡበት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት መዘርጋት ብቻ። ለዚህም ከተጽህኖ ነጻ የመከላከያና ፖሊስ ሰራዊቶች፣ ነጻ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም እንደ ኬንያው  ነጻ ፍርድ ቤቶች በህዝቦች ንቁ ተሳትፎና ውሳኔ ሰጪነት በአጭር ወቅት መገንባት ይኖርባቸዋል።

ያሬድ አውግቸው (yaredawgichew@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule