• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል

September 6, 2017 02:15 am by Editor Leave a Comment

የህወሃት አገዛዝ 2010 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ለማክበር የጀመረውን ከባህሪው የወጣ ድርጊት ተመልክተው አንዳንዶች ስርዓቱ እውነተኛ የመንግስትነት ባህርይን እየያዘ ነው ሲሉ ይደመጣል። እነዚህ የዋሆች  ሰሞኑን ከነሀሴ 26 ቀን ጀምሮ የፍቅር ቀን፣ የእናቶችና ህፃናት ቀን፣ የአረጋውያን ቀን፣ የሰላም ቀን፣ የንባብ ቀን፣ የአረንጓዴ ልማት ቀን፣ የመከባበር ቀን፣ የሀገር ፍቅር ቀን፣ የአንድነት ቀን እና የኢትዮጵያ ቀን በሚሉ መለያዎች አዲሱን ኣመት ለመቀበል ህወሀት የያዘውን ፕሮግራም እንደ አንድ ማስረጃነት ሲጠቅሱ ይታያል። ታርሟል በሚል። መሬት ላይ የምናያቸው የስርኣቱ ባህርያት በምክንያት ለገመገመ ሰው ግን ስርዓቱ ለመሻሻል ፍላጎት እንደሌለው ይገነዘባል። በእኔ ምልከታ ችግሩ ከድርጅቱ ፍጥረታዊ ባህርይ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገንዝቤአለሁ።

በመጀመሪያ ደረጃ ህወሀት ከምስረታው ጀምሮ በጠላትነት የሚያሳድደው አመለካከት ፍቅር፣ አንድነት እና ኢትዮጵያ የሚለውን ሀይል አይደለም እንዴ? እስከዚህ ሰዓት ድረስ  የተበዳይና የበዳይ ድርሰት እየደረሰ በህዝቦች መካከል ቁርሾ የሚዘራው ማነው? በሌላ በኩል የዘር ብሄርተኝነትን ከሚገባው በላይ በማራገብ ኢትዮጳዊነትን ያኮሰመነ  መንግስትስ ማን ነው? የህወሃት አገዛዝ አይደለምን? ታዲያ አሁን ምን ተገኘ የሚለው በደንብ መታየት ያለበት ይመስለኛል። በእኔ ምልከታ ይህ እርምጃ  ህወሀት በአሁኑ ወቅት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በአንድነት የተነሳበትን ተቃውሞ ለማቀዝቀዣነት የዘረጋው ስልት ነው። የአንድነት ሀይል ነው ተብሎ የሚታሰበውን የአማራ ሀይል ጉርሻ ነገር በመስጠት ማስታገስ ላይ ያነጣጠረ ስልት። በዚህም በቅርቡ በአማራ ክልል በክልል ደረጃ  ለመተግበት ህዝቡ በእቅድ የያዘውን በቤት ውስጥ የመቀመጥ ህዝባዊ አድማ ማለዘብ የስልቱ ዋና አላማ ነው። ይህም ህወሀት ሙሉ ሀይሉኝ በኦሮሚያውና ሌሎች ክልሎች  ላይ እንዲያተኩር ይረዳዋል። ህወሀት እንደዚህ እይነት ብልጣ ብልጥ እርምጃዎች  ይዞ ሲመጣ ይበልጥ ጠንቃቃ መሆን እንዳለብን ልምዳችን አስተምሮናል። ከትንፋሽ በኋላ ይበልጥ አሳሪ ህግና አሰራሮችን ይዞ በበቀል የመጣባቸው ብዙ ልምዶች ስላሉን። ከ1997 ምርጫ ተከትሎ የአንድነት ህይሉን፣ ነጻ ፕሬስ እና ማህበራትን ለማጥፋት የወሰዳቸው እርምጃዎቹን ማስታወስ ይገባል። ድርጅቱ ግለሰብና ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን ከተማዎችንም በቂ በቀል የሚቀጣ መሆኑን ማስታወስ ይገባል።

የህወሀት እታደሳለሁ የሚሉ ለቁጥር አታካች መሀላዎች ያመጡልን ነገር ቢኖር በተደራጀ መንገድ የሚያካሂደው የሀገር ሀብት ዘረፋ መባባስ ነው። የባርነት ሰንሰለቱ ይበልጥ መጥበቅ ነው። የህዝቦች እርስ በርስ ጥላቻ መበራከት ሌላው ህወሀት እድሜው በጨመረ ቁጥር አብረው የጨመሩ ክስተቶች ናቸው። ስለዚህ “ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል” ብለናል። ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መመስረት ሀገራችን ያላት መንገዱ አንድ ብቻ ነው። ህዝቦች መሪዎቻቸውን በምርጫ ካርድ ወደ ስልጣን የሚያመጡበት የመድብለ ፓርቲ ስርዓት መዘርጋት ብቻ። ለዚህም ከተጽህኖ ነጻ የመከላከያና ፖሊስ ሰራዊቶች፣ ነጻ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም እንደ ኬንያው  ነጻ ፍርድ ቤቶች በህዝቦች ንቁ ተሳትፎና ውሳኔ ሰጪነት በአጭር ወቅት መገንባት ይኖርባቸዋል።

ያሬድ አውግቸው (yaredawgichew@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule