• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግርና የመፍትሄ አቅጣጫ በሚመለከት የተሰጠ መግለጫና የሰላም ጥሪ

November 22, 2016 12:21 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያን ችግር የመፍትሄ መንገድ በሚመለከት “ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር” በሚል ርእስ ቀደም ሲል አንድ የሰላም ጥሪ ማቅረባችንን እናስታውሳለን። መልእክቱም ባጭሩ ይህች ታላቅ ሀገር የገጠማት ችግር ሊፈታ የሚችለው በመሪዎቿና በልዩ ልዩ የተቃውሞ ጎራ በተሰለፉ የራሷ ልጆች ብቻ መሆኑን፤ መፍቻ መንገዱም ውይይትና ንግግር መሆኑን፤ ጊዜውም አሁን መሆኑን የሚያመላክት ነበር። ለዚህም ሁሉም ወገኖች ቢያንስ በችግሩ ላይ ለመነጋገር መስማማት እንዳለባቸው በመጠቆም ለሰላማዊ ውይይት እንዲተባበሩና ሃሳባቸውን እንዲገልፁልን አሳስበንም ነበር።

ጥሪውን የተመለከቱ ድርጅቶችና ግለሰቦች  የሰጡንን በጎ ምላሽና ማበረታቻ በምስጋናና በአክብሮት ተቀብለናል፤ ደስ ብሎናልም። የሰላም ውይይት ወደሰላም በር የሚወስድ ጠቃሚ ስልት መሆኑን በማመን ድርጅታችን ላቀረበው የውይይት መድረክ ዝግጅት ሃሳብ በፅሁፍም ሆነ በቃል ድጋፍና በጎ ምላሽ ለሰጣችሁ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ወንድምና እህትማማች የሆኑ የኢትዮጵያን ልጆች በሰላም ተነጋግረው ችግራቸውን የመፍታት አቅም እንዳላቸው በማመን የሚገናኙበትን መድረክ ለመፍጠር የጀመርነውን ጉዞ በፅናት እንድንቀጥል ያገኘነው በጎ ምላሽና የትብብር ተስፋ አዲስ ጉልበት የሰጠን ስለሆነ ለስኬቱ ተግተን እንሰራለን።

ኢትዮጵያውያን ዛሬ የገጠማቸውን ችግር በውይይት ለመፍታት ቆርጠው እንዲነሱ ለቀረበው ጥሪ እስካሁን የተሰጠው በጎ ምላሽና የድጋፍ አስተያየት ተስፋ ሰጪ ነው። ይሁን እንጂ ስራው ገና ብዙ ድካም እንደሚጠይቅ መታመን አለበት። ሰላማዊ ውይይት ሃሳቡ ማራኪ የመሆኑን ያህል ዋጋው ውድ ነው። የተለያየ ሃሳብ ያላቸው የአንዲት ኢትዮጵያ ልጆች እንድትኖራቸው የሚናፍቋትንና በፍቅር የሚኖሩባትን  የጋራ ሀገር እንደገና ለመፍጠር በሚቻልበት መንገድ ላይ ለመምከር በአንድ የውይይት ማእድ ቀርበው ሲወያዩ ማየትን ለመሰለ ታላቅ እድል ለመብቃት ወሰን የሌለው መስዋእትነት መክፈል ያስፈልጋል። ድርጅታችን በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ  ምድር ጭምር ሰላምና የህግ የበላይነት ይሰፍኑ ዘንድ የአቅሙን ለመስራት የተነሳው ይህ ታላቅ ግብ  የሚጠይቀውን የመስዋእትነት ክብደት በመዘንጋት ሳይሆን የመስዋእትነቱን አስፈላጊነት ጭምር በመቀበል ነው።

ኢትዮጵያውያን ወገኖችም የራሳቸውን ችግር ለመፍታት እስከፈቀዱና ለመተባበር እስከቆረጡ ድረስ  የሰላም ጉዞው የቱንም ያህል ዋጋ ቢጠይቅ ለስኬት እንደምንበቃ ጥርጥር የለንም። በዚህ ነጥብ ላይ ለሰላማዊ ድርድር ተስፋ ቆርጠናል ከሚሉ ወገኖች እንለያለን። በመሆኑም ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ ወንድምና እህት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ የገጠመውን ጊዚያዊ ፈተና አሸንፎ እንዲወጣ መሪዎቹና ተቃዋሚ ሀይሎች እስካሁን የሄዱበትን ጎዳና ዳግም በማጤን በሆደ ሰፊነትና በሀላፊነት ስሜት ለትውልድ በኩራት የሚተላለፍ ታሪክ እንዲሰሩ ለመርዳት በጀመረው ጥረት ይቀጥላል። ሃሳቡ መልካም የመሰላችሁ ወገኖች ሁሉ በምትችሉት መንገድ ድጋፋችሁ እንዲቀጥል እናሳስባለን።

ለሀገራቸው የየራሳቸው ህልም ያላቸው ግን ደግሞ የአንድ እናት ልጆች የሆኑ ኢትዮጵያውያን በአንድ መድረክ  ለሰላም እንዲመክሩ የምናደርገው ጥረት ይሳካ      ዘንድ ሁሉም ወገኖች የየበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱና ትብብር እንዲያደርጉ  እንጠብቃለን።

የሰላም ውይይት መድረክ አስፈላጊነትና አጣዳፊነት

መንግስትና ሌሎች የፖለቲካ ሀይሎች ሁሉ የሚሳተፉበት የሰላም ውይይት መድረክ ባስቸኳይ መዘጋጀት አለበት የምንልበት አጣዳፊ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው።

  • ችግሩን ለመፍታት የሚያስችል የሰላም ምክክር ባጣዳፊ ካልተጀመረ ግጭቱ ተዳፍኖ ከቆየ በኋላ ባልተጠበቀ መንገድ መልኩን ሊለውጥ ይችላል። በመሆኑም ችግሩ ከፍቶ ወደ ብሄር ወይም ጎሳ ግጭት ሳይለወጥ አሁን ባለበት ደረጃ እያለ መፍታት ይቻላል።
  • የሰላም ጥረቱ በዘገየ ቁጥር በየስፍራው በሚደረጉ ስብሰባዎች ላይ የሚነሱ አዳዲስ አመለካከቶች አዳዲስ ችግሮችን በመፍጠር ግጭቱን እያባባሱት ስለሆነ ችግር በችግር ላይ እየተደራረበ በየትኛውም መንገድ ለመፍታት በሚከብድ የተወሳሰበ ደረጃ ላይ ሳይደርስ በጊዜ መቆጣጠር አስፈላጊ ስለሆነ ነው።
  • የሰላም መፍትሄው በዘገየ ቁጥር አዳዲስ የፖለቲካ አጀንዳ ያላቸው አዳዲስ የፖለቲካ ሀይሎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ስለሚሆንና ይህም የመፍትሄ ማፈላለጉን ተግባር የበለጠ የሚያከብደው በመሆኑ ነው።

ስለዚህ መንግስትና ተቃዋሚ ሀይሎች ሁሉ የሰላም ውይይት አስፈላጊነትንና አጣዳፊነቱም ጭምር በመገንዘብ በተለይ የሚከተሉትን ሀሳቦች በማጤን  የስነልቡና ቁርጠኝነት እንዲያሳዩና ተጨባጭ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪያችንን በድጋሚ እናስተላልፋለን።

  1. ኢትዮጵያን የገጠማትን ችግር በሰላማዊ ውይይትና ድርድር መፍታት ይቻላል፤ በዚህ መንገድ የሚደረስበትም ስምምነትና መፍትሄ ዘላቂ ስለሚሆን ጠቃሚ ነው። ስለዚህ መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ሀይሎች ለሰላማዊ ውይይትና ድርድር ቁርጠኝነት ማሳየትና ይፋ አቋማቸውን መግለፅ ይኖርባቸዋል። በሰላም ምክክርና ድርድር ጉዳይ ላይ ያላቸውንም አቋም በደብዳቤ 840 1st St NE Washington DC 20002 በኢሜል peaceafrica16@gmail.comቢልኩልንእናመሰግናለን።
  2. የወቅቱን የኢትዮጵያን ችግር ባስተማማኝና ዘላቂ መንገድ ለመፍታት በተናጠል ከሚወሰድ እርምጃ ይልቅ የጋራ ምክክርና ስምምነት የበለጠ ጠቃሚ እንደሚሆን መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ሀይሎች ሊያምኑበት ይገባል።
  3. የሰላማዊ ውይይት ፍላጎት የሽንፈት መገለጫ ሳይሆን የብስለትና የስልጣኔ እርምጃ መሆኑን ከልብ አምኖ መቀበል ያስፈልጋል። ለዚህም እልህን ማሸነፍና በሰላምና በሰከነ መንገድ የሚደረግ ውይይት ከመንግስትና ተቃዋሚ ሀይሎች በላይ ለህዝብና ለሀገር የሚበጅ ተግባር መሆኑን ማመንን ይጠይቃል።
  4. ዛሬ ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታና የገጠማትም ችግር አዲስ አቀራረብና አመለካከት የሚጠይቅ ነው። ስለሆነም መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ሀይሎች የድርጅት መርሃ-ግብርና የፖሊሲ አጥርን በመሻገር ተቀናቃኝን ፊት ለፊት ገጥሞ በመከራከር ረገድ እስካሁን የሄዱትን ርቀት አልፈው ለመጓዝ ሊዘጋጁ ይገባል።
  5. በሰላምና ድርድር ጉዳይ ላይ የሚሰሩ አካላትም ሆኑ የድርጅታችንን የሰላም ጥረት የሚደግፉ አካላት በሚችሉት መንገድ ሁሉ እንዲረዱና እንዲተባበሩ ጥሪያችንን በድጋሚ እናቀርባለን። በዚህ አጋጣሚ ሃሳባችን ቀና መሆኑን በመመልከት ገንቢ አስተያየት የሰጣችሁንንና ድጋፍ ልታደርጉልን ጥረት እያደረጋችሁ ላላችሁ አካላት ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ

ህዳር 6 ቀን 2009 ዓ.ም
ዋሽንግተን ዲሲ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    November 26, 2016 02:26 pm at 2:26 pm

    This is a good idea to create the dream land that is always in our minds.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule