• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግርና የመፍትሄ አቅጣጫ በሚመለከት የተሰጠ መግለጫና የሰላም ጥሪ

November 22, 2016 12:21 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያን ችግር የመፍትሄ መንገድ በሚመለከት “ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር” በሚል ርእስ ቀደም ሲል አንድ የሰላም ጥሪ ማቅረባችንን እናስታውሳለን። መልእክቱም ባጭሩ ይህች ታላቅ ሀገር የገጠማት ችግር ሊፈታ የሚችለው በመሪዎቿና በልዩ ልዩ የተቃውሞ ጎራ በተሰለፉ የራሷ ልጆች ብቻ መሆኑን፤ መፍቻ መንገዱም ውይይትና ንግግር መሆኑን፤ ጊዜውም አሁን መሆኑን የሚያመላክት ነበር። ለዚህም ሁሉም ወገኖች ቢያንስ በችግሩ ላይ ለመነጋገር መስማማት እንዳለባቸው በመጠቆም ለሰላማዊ ውይይት እንዲተባበሩና ሃሳባቸውን እንዲገልፁልን አሳስበንም ነበር።

ጥሪውን የተመለከቱ ድርጅቶችና ግለሰቦች  የሰጡንን በጎ ምላሽና ማበረታቻ በምስጋናና በአክብሮት ተቀብለናል፤ ደስ ብሎናልም። የሰላም ውይይት ወደሰላም በር የሚወስድ ጠቃሚ ስልት መሆኑን በማመን ድርጅታችን ላቀረበው የውይይት መድረክ ዝግጅት ሃሳብ በፅሁፍም ሆነ በቃል ድጋፍና በጎ ምላሽ ለሰጣችሁ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ወንድምና እህትማማች የሆኑ የኢትዮጵያን ልጆች በሰላም ተነጋግረው ችግራቸውን የመፍታት አቅም እንዳላቸው በማመን የሚገናኙበትን መድረክ ለመፍጠር የጀመርነውን ጉዞ በፅናት እንድንቀጥል ያገኘነው በጎ ምላሽና የትብብር ተስፋ አዲስ ጉልበት የሰጠን ስለሆነ ለስኬቱ ተግተን እንሰራለን።

ኢትዮጵያውያን ዛሬ የገጠማቸውን ችግር በውይይት ለመፍታት ቆርጠው እንዲነሱ ለቀረበው ጥሪ እስካሁን የተሰጠው በጎ ምላሽና የድጋፍ አስተያየት ተስፋ ሰጪ ነው። ይሁን እንጂ ስራው ገና ብዙ ድካም እንደሚጠይቅ መታመን አለበት። ሰላማዊ ውይይት ሃሳቡ ማራኪ የመሆኑን ያህል ዋጋው ውድ ነው። የተለያየ ሃሳብ ያላቸው የአንዲት ኢትዮጵያ ልጆች እንድትኖራቸው የሚናፍቋትንና በፍቅር የሚኖሩባትን  የጋራ ሀገር እንደገና ለመፍጠር በሚቻልበት መንገድ ላይ ለመምከር በአንድ የውይይት ማእድ ቀርበው ሲወያዩ ማየትን ለመሰለ ታላቅ እድል ለመብቃት ወሰን የሌለው መስዋእትነት መክፈል ያስፈልጋል። ድርጅታችን በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ  ምድር ጭምር ሰላምና የህግ የበላይነት ይሰፍኑ ዘንድ የአቅሙን ለመስራት የተነሳው ይህ ታላቅ ግብ  የሚጠይቀውን የመስዋእትነት ክብደት በመዘንጋት ሳይሆን የመስዋእትነቱን አስፈላጊነት ጭምር በመቀበል ነው።

ኢትዮጵያውያን ወገኖችም የራሳቸውን ችግር ለመፍታት እስከፈቀዱና ለመተባበር እስከቆረጡ ድረስ  የሰላም ጉዞው የቱንም ያህል ዋጋ ቢጠይቅ ለስኬት እንደምንበቃ ጥርጥር የለንም። በዚህ ነጥብ ላይ ለሰላማዊ ድርድር ተስፋ ቆርጠናል ከሚሉ ወገኖች እንለያለን። በመሆኑም ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ ወንድምና እህት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ የገጠመውን ጊዚያዊ ፈተና አሸንፎ እንዲወጣ መሪዎቹና ተቃዋሚ ሀይሎች እስካሁን የሄዱበትን ጎዳና ዳግም በማጤን በሆደ ሰፊነትና በሀላፊነት ስሜት ለትውልድ በኩራት የሚተላለፍ ታሪክ እንዲሰሩ ለመርዳት በጀመረው ጥረት ይቀጥላል። ሃሳቡ መልካም የመሰላችሁ ወገኖች ሁሉ በምትችሉት መንገድ ድጋፋችሁ እንዲቀጥል እናሳስባለን።

ለሀገራቸው የየራሳቸው ህልም ያላቸው ግን ደግሞ የአንድ እናት ልጆች የሆኑ ኢትዮጵያውያን በአንድ መድረክ  ለሰላም እንዲመክሩ የምናደርገው ጥረት ይሳካ      ዘንድ ሁሉም ወገኖች የየበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱና ትብብር እንዲያደርጉ  እንጠብቃለን።

የሰላም ውይይት መድረክ አስፈላጊነትና አጣዳፊነት

መንግስትና ሌሎች የፖለቲካ ሀይሎች ሁሉ የሚሳተፉበት የሰላም ውይይት መድረክ ባስቸኳይ መዘጋጀት አለበት የምንልበት አጣዳፊ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው።

  • ችግሩን ለመፍታት የሚያስችል የሰላም ምክክር ባጣዳፊ ካልተጀመረ ግጭቱ ተዳፍኖ ከቆየ በኋላ ባልተጠበቀ መንገድ መልኩን ሊለውጥ ይችላል። በመሆኑም ችግሩ ከፍቶ ወደ ብሄር ወይም ጎሳ ግጭት ሳይለወጥ አሁን ባለበት ደረጃ እያለ መፍታት ይቻላል።
  • የሰላም ጥረቱ በዘገየ ቁጥር በየስፍራው በሚደረጉ ስብሰባዎች ላይ የሚነሱ አዳዲስ አመለካከቶች አዳዲስ ችግሮችን በመፍጠር ግጭቱን እያባባሱት ስለሆነ ችግር በችግር ላይ እየተደራረበ በየትኛውም መንገድ ለመፍታት በሚከብድ የተወሳሰበ ደረጃ ላይ ሳይደርስ በጊዜ መቆጣጠር አስፈላጊ ስለሆነ ነው።
  • የሰላም መፍትሄው በዘገየ ቁጥር አዳዲስ የፖለቲካ አጀንዳ ያላቸው አዳዲስ የፖለቲካ ሀይሎች እንዲፈጠሩ ምክንያት ስለሚሆንና ይህም የመፍትሄ ማፈላለጉን ተግባር የበለጠ የሚያከብደው በመሆኑ ነው።

ስለዚህ መንግስትና ተቃዋሚ ሀይሎች ሁሉ የሰላም ውይይት አስፈላጊነትንና አጣዳፊነቱም ጭምር በመገንዘብ በተለይ የሚከተሉትን ሀሳቦች በማጤን  የስነልቡና ቁርጠኝነት እንዲያሳዩና ተጨባጭ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪያችንን በድጋሚ እናስተላልፋለን።

  1. ኢትዮጵያን የገጠማትን ችግር በሰላማዊ ውይይትና ድርድር መፍታት ይቻላል፤ በዚህ መንገድ የሚደረስበትም ስምምነትና መፍትሄ ዘላቂ ስለሚሆን ጠቃሚ ነው። ስለዚህ መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ሀይሎች ለሰላማዊ ውይይትና ድርድር ቁርጠኝነት ማሳየትና ይፋ አቋማቸውን መግለፅ ይኖርባቸዋል። በሰላም ምክክርና ድርድር ጉዳይ ላይ ያላቸውንም አቋም በደብዳቤ 840 1st St NE Washington DC 20002 በኢሜል peaceafrica16@gmail.comቢልኩልንእናመሰግናለን።
  2. የወቅቱን የኢትዮጵያን ችግር ባስተማማኝና ዘላቂ መንገድ ለመፍታት በተናጠል ከሚወሰድ እርምጃ ይልቅ የጋራ ምክክርና ስምምነት የበለጠ ጠቃሚ እንደሚሆን መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ሀይሎች ሊያምኑበት ይገባል።
  3. የሰላማዊ ውይይት ፍላጎት የሽንፈት መገለጫ ሳይሆን የብስለትና የስልጣኔ እርምጃ መሆኑን ከልብ አምኖ መቀበል ያስፈልጋል። ለዚህም እልህን ማሸነፍና በሰላምና በሰከነ መንገድ የሚደረግ ውይይት ከመንግስትና ተቃዋሚ ሀይሎች በላይ ለህዝብና ለሀገር የሚበጅ ተግባር መሆኑን ማመንን ይጠይቃል።
  4. ዛሬ ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታና የገጠማትም ችግር አዲስ አቀራረብና አመለካከት የሚጠይቅ ነው። ስለሆነም መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ሀይሎች የድርጅት መርሃ-ግብርና የፖሊሲ አጥርን በመሻገር ተቀናቃኝን ፊት ለፊት ገጥሞ በመከራከር ረገድ እስካሁን የሄዱትን ርቀት አልፈው ለመጓዝ ሊዘጋጁ ይገባል።
  5. በሰላምና ድርድር ጉዳይ ላይ የሚሰሩ አካላትም ሆኑ የድርጅታችንን የሰላም ጥረት የሚደግፉ አካላት በሚችሉት መንገድ ሁሉ እንዲረዱና እንዲተባበሩ ጥሪያችንን በድጋሚ እናቀርባለን። በዚህ አጋጣሚ ሃሳባችን ቀና መሆኑን በመመልከት ገንቢ አስተያየት የሰጣችሁንንና ድጋፍ ልታደርጉልን ጥረት እያደረጋችሁ ላላችሁ አካላት ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ሰላምና ፍትህ ለአፍሪካ

ህዳር 6 ቀን 2009 ዓ.ም
ዋሽንግተን ዲሲ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    November 26, 2016 02:26 pm at 2:26 pm

    This is a good idea to create the dream land that is always in our minds.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule