• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መጪው ቅዳሜ ለት በመላው ኦሮሚያ ሰላማዊ ሰልፍ ይካሄዳል

August 4, 2016 08:44 am by Editor 1 Comment

እሁድ እለት በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በአስርታት ሺዎች የሚቆጠር ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቶ ወያኔን ተቃውሞ በሰላም ወደ ቤቱ ተመለሰ። በጣም ጥሩና ታሪካዊ ሰልፍ ነበር። በእለቱ ከጥቂት ሰዓታት በኋል ግን በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሀረርጌ አወዳይ ከተማ ወጣቶች ሰልፍ ወጥተው በአጋዚ አልሞ ተኳሾች 26ቱ ቆስለው እስከ አሁን 6 ሞተዋል።

ይሄንን እንደምሳሌ ጠቀስኩ እንጂ ኦሮሚያ ውስጥ ወያኔ ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት እሩምታ ሲፈጅ አዲስ አይደላም። ባለፉት 9 ወራት ካ600 በላይ ዜጎች ተገድለዋል፣ 5000 የሚሆኑ የመቁሰል ጉዳት ደርሶባቸውል። ይሄንን ቁጥር ወስደን ብናሰላው፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ በየእለቱ ባማካይ ከሁለት እስከ ሶስት ሰዎች ኦሮሚያ ውስጥ በመንግስት ታጣቂ ሃይሎች ሲገደሉ እንደነበረ ማየት ይቻላል። ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈጸም የአምባገኖች ጸባይ ነው ተብሎ ሲታለፍ ነበር። ነገር ግን ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ የሚገደልው የኦሮሚያ ህዝብ ብቻ መሆኑ ግልጽ እየሆነ ሲመጣ ነገሮችን መለሰን እንድናጤን አድርጎናል።

ለመሆኑ በተለያዩ ክልሎች ለወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች የተለያየ ምላሽ ምክንያቱ ምንድነው?

1) የኦሮሚያ ሰልፈኞች የጦር መሳሪያ ይዘው አለመውጣታቸው። ምክንያቱም እንደሚታወቀው ባለፉት 25 አመታት ተደጋጋሚ ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻ በኦሮሚያ ሲካሄድ ነበር። እናም በግልጽ የታጠቀው ህዝብ አናሳ ነው። በተጨማሪም የኦሮሞ አመራሮች ህዝቡ መሳሪያ ይዞ እንዳይወጣ ሲማጸኑ ነበር። ይሄም የተደረገበት ምክንያት ያቺ ሀገር እና ህዝብ ወደ ዳግም ጦርነት ሳይገቡ በነፍጥ-አልባ ትግል ለውጥ ለማምጣት ካለ ምኞት የተነሳ ነው። ነገር ግን ይህን የኦሮሞን ሰላም ወዳድነት ህወሀቶች እንደ ፈሪነት መቁጠራቸው ገሃድ ወጥቷል።

2) ባለፉት 9 ወራት በኦሮሚያ ውስጥ በተካሄደው ትግል ብዙ ከተሞች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ሲወጡ እንኳን የትግሬዎች ንብረት እና ህይወት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ጥንቃቄ ተደርጓል። ይህ አቋም ግን ህወሀቶች እንደ ጅልነት (naivety and harmlessness) የተቆጠረ ይመስላል።

ባጠቃላይ የህወሀት መሪዎች እንድን ህዝብ የሚሰሙት በጠመንጃ ሲጋፈጣቸው እና ዘመዶቻቸው ሲነካ ብቻ መሆኑን ደጋግመው አረጋግጠዋል። ለኦሮሞ ህዝብ ያላቸውን መጠን ያለፈ ንቀት እና ጥላቻ በተደጋጋሚ አሳይተዋል። እናም አንድ እጅ ብቻውን ማጨብጨ ስለማይችል የኦሮሞ ህዝብ እራሱን ከተከፈተበት የዘር ማጥፋት ዘመቻ ለመታገድ የስትራቴጂ ለውጥ ሊያደርግ እየተገደደ ነው። ሆኖም ግን ወደዚህ ዓይነቱ መመለሻ የሌለው መንገድ ከመግባታችን በፊት የመጨረሻ እንድል መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚሁም መሰረት የሚቀጥሉት እርምጃዎች ይወሰዳሉ:

1. በመጪው ቅዳሜ በኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጁ ሰልፎች ይካሄዳሉ። እነዚህ ሰልፎች ልክ እንደ ከዚህ በፊቶቹ ሁሉ ፍጹም ሰላማዊ ይሆናሉ። በሰላማዊ ሰልፎቹ ላይ መንግስት ኦሮሞ ላይ እያካሄደ ያለውን ግድያ ባስቸኳይ እንዲያቆም፣ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ካላንዳች ቅድመ ሁናቴ እንዲፈቱ፣ ኦሮሚያን በኣጋዚ ጦር ማስተዳደር እንዲቆም፣ ህዝቡ ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብቱ እንዲጠበቅ የሚሉና የመሳሰሉ ሌሎች መሰረታዊ መብቶችን መከበር የሚጠይቁ ጥያቄዎችና መፈክሮች እንዲንጸባረቁ ይደረጋል።

2. ለዚህ ሰልፍ ፍቃድ አይጠየቅም። በህጉ መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የሚያስፈልገው መንግስትን ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው። ይህ ጽሁፍ እንደማስታወቂያ እንዲረዳ ለኦሮሚያ እና ለፌደራሉ መግስት መሰራቤቶች ገቢ አድርገናል።

የኦሮሚያም ሆነ የፌደራል የታጠቁ ሀይሎች ሰላማዊ ሰልፎቹን ለማስተጓጎልም ሆነ በእለቱ በህዝቡ ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ ከሆነ ቀጥሎ ለሚመጣው አደጋ ተጠያቂ እንደሚሆኑ በዚሁ ማስጠንቀቅ እንወዳለን። የተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብም ለምስክረነት ይህን ግልጽ ማስታወቂያ በጥሞና እንዲያነብልንና ከጎናችንም እንዲሰለፍ ባክብሮት እንጠይቃለን።

‪#‎OromoProtests‬

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    August 11, 2016 10:43 pm at 10:43 pm

    Free Bekele Gerba and all political, religious leaders as well as journalists and bloggers. There is only state terrorism in Ethiopia and the main terrorists are TPLF fascists bred and nurtured by the US/UK/EU and their allies – the Arabs. Ethnic federalism/ethnic cleansing is a total failure and should be dismantelled with the fascists and their constitution. Federalism in a free and democratic Ethiopia and with the participation and full understanding of the Ethiopian people. The current ethnic federalism only serves TPLF and OLF and harmfull to the Amharas. The number of languages to be used and the adminstration divisions should be decided by a freely and democratically elected parliament. The forcefully land grabbing and expansion of TPLF is wrong and it should be corrected. Wolqait will not be part of Tigrai unless the fascists kill all Amharas. Besides all should stand together on this issue because it is unjust and we all should stand for truth and justice.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule