• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ነው…” “BBN (አቶ አብዲረሂም አህመድ)

November 29, 2016 07:01 am by Editor 1 Comment

በኦሮሞ ስም እየተደረጉ ያሉትን አብዛኛዎቹን ስብሰባዎች ላስተዋለ ሰው፣ የኦሮሞ ጎሳ ብቻ ሳይሆን በአመዛኙ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ስብስብ እየመሰለም (“ሆኗል” አለማለታችን ይያዝልን) ሄዷል። አቶ ጃዋር ሙስሊም ከመሆኑ እና ራሱን የኦሮሞ የፖለቲካ ተወካይ/ተጠሪ አድርጎ በየመድረኩ ብቅ ካለበት ጊዜ ጀምሮ፤ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የኦሮሞ ተውላጅ ልሂቃን፣ አቶ ጃዋርን “በሜጫ አንገት የመቁረጥ” ፉከራው ጋር አዝለው፣ አንድም ጊዜ በአደባባይ ይቅርታ እንዲጠይቅ ማድረግ ሳይችሉ እና እነሱም ሳያወግዙ፣ እስካሁን ድረስ ተሸክመው የመዝለቃቸውም ነገር እኛ በ“ኢትዮጵያ ሴኩላር ሰብዓዊያን” ስር የተሰባሰብነውን ግለሰቦች እጅግ አሳዝኖናል፣ አሳስቦናልም።

እሱ ሲገርመን አሁን ደግሞ በቅርቡ BBN በሚባል ስም የሚታወቀው፣ በጸረ-ህወሃት የፖለቲካ አቋሙ እና በእስልምና ሃይማኖት አራማጅነቱ የሚታወቀው የመገናኛ ብዙሃን አዘጋጅ አቶ አብዲረሂም አህመድ “…የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ከመሆኑ አንጻር…(ይቺን ይጫኑ)” ሲል ተናግሯል። ይህ ተቆርጦ እዚህ ከተለጠፈው ንግግር በፊትም ሆነ በኋላ የተነገረው ሁሉ በቋንቋውም ሆነ በአውድ ደረጃ ደጋግመው ቢያዳምጡት “ኦሮሞ ሙስሊም ነው” የሚለውን የግለሰቡን አባባል ጨርሶ አይቀይረውም (እነሆ ንግግሩን በሙሉ ማዳመጥ ይቻላል። እንዲህ አይነት ሃላፊነት የጎደላቸውን እና ውሸት የሆኑ ንግግሮች በማንኛውም ግለሰብ፣ ድርጅትም ሆነ ተቋም ሲነገር፣ ይኼን ለማውገዝ የመጀመሪያዎቹ መሆን የነበረባቸው ራሳቸው የእስልምና ተከታይ የሆኑ አድማጮች መሆን ነበረባቸው። የሆነ ግን አይመስለንም። አሳዛኝም አስፈሪም ነው። እናም እስካሁን ለተነገሩትም ሆነ ለወደፊት ለሚነገሩት፣ እና ንግግሮቹ በአገራችን ኢትዮጵያ ለወደፊት ለሚያደርሱት መዘዝ ተጠያቂ በሚያደርግ መልኩ ለሚመመለከታቸው ተቋማት ሁሉ ሪፖርት የማድረግ ሃላፊነት እንዳለብን እንገልጻለን።

ይህ ከእውነት የራቀ የBBNኑ አቶ አብዲራሂም እና የOMNኑ አቶ ጃዋር የሜጫ ንግግር፣ በግለሰብ ደረጃ ለግለሰብ የተነገረ ቢሆን “ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም…” ተብሎ እንዲሁ ሊታለፍ ይችል ይሆናል። በአገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ እየደረሰ ያለውን የፍትህ መዛባት (ግድያ፣ ስቅየት፣ እስራት፣ እንግልት፣ ስደት፣ ተስፋ መቁረጥ…) እና የግለሰብ መብት የሆነውን ሃይማኖትን ያህል ነገር እንኳን በነጻነት ማምለክ በማይቻልበት አገር ውስጥ፣ እንዲህ አይነት ንግግሮች ሊያስከትሉ የሚችሉትን መዘዝ አለመገመት፣ አምባገነንነት በገነነባቸው አገሮች (ሶማሊያ፣ ናይጄሪያ፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ቦስኒያ/ዩጎዝላቪያ…) ውስጥ አሁን እየደረሰ ያለውን (የደረሰውን) የርስ በርስ ጦርነት እና በሩዋንዳ ላይ የደረሰውን የቅርብ ጊዜ አሳዛኝ ክስተት መርሳት ይሆናል።

ሃይማኖትን በተመለከተ የሚደረጉ ንግግሮች፣ በተለይም ከእንደ “… 99% እስላም ነው [1% የሚሆነውን ክርስቲያኑን] በሜጫ አንገት እንቆርጣለን”፣ የመሰለ እጅግ ግልብ እና አደገኛ የሆነ የአመጽ እና የግድያ ዛቻ ሲደረግ፣ “ኦሮሞ እስላም ነው” የመሳሰሉ ሃላፊነት የጎደለው እና ፍጹም ውሸት የሆነ ንግግር፣ በተለይም የመገናኛ ብዙሃንን በእጃቸው ያደረጉ ግለሰቦች (ጃዋር የኦ.ኤም.ኤን፣ አብዲረሂም ደግሞ የቢ.ቢ.ኤን. መስራቾች እና አሁንም የሚቆጣጠሯቸው ናቸው) ሲናገሩ እየሰማን ዝም ማለት፣ በማናቸውም መልኩ ተቀባይነት የለውም። በመገናኛ ብዙሃን የሚተላለፉ ንግግሮች እጅግ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የ“BBNኑ አዘጋጅ በዚህ ቃለ-መጠይቅ ላይ ያነሳቸው ነጥቦች እና ያነጋገራቸው የኦሮሞ አክቲቪስቶች (ሮባ እና ጃውሃር [የOMNኑ ጃዋር አይደለም])፣ ዋና አጀንዳቸው የለንደኑ ኮንፈንስ ሆኖ፣ የ“ኢትዮጵያ ትበተን” እና መሰል ንግግሮችን አስመልክቶ የሰጧቸው አስያየቶች ህወሃትን ለማስወገድ በሚደረገው ትግል ላይ ያሳደረውን አፍራሽ ሚና በተመለከተ መሆኑን እና ተሳታፊዎቹ ሮባ እና ጃውሃር የሰጧቸው አስተያየቶች፣ በኮንፈረንሱ ላይ የተደረገውን አፍራሽ ንግግር በማውገዝ ላይ የተመሰረተ መሆኑን እና የቢቢኤኑ አዘጋጅም እነዚህን አክቲቪስቶች ለማነጋገር ያደረገው ተነሳሽነት የሚበረታታ ነው። “… የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ነው…” የሚል አደገኛ ውሸት (ካፍ ያመለጠ ስህተት ነው ለማለት እጅግ ይከብደናል) ግን የ“ተሳስቻለሁ ይቅርታ” ብቻውን የሚበቃ አይመስለንም። እጅግ ደጋግሞ በመገናኛ ብዙሃኑ አማካይነት ማንሳት እና ማስተባበል ይገባ ይመስለናል። እውነት ለመናገር “በሜጫ አንገት እንቆርጣለን” እና “ኦሮሞ እስላም ነው” ከመሳሰሉት ከእንደዚህ አይነት ሃላፊነት የጎደላቸው ንግግሮች ለመዳን “… አገር ቤት ውስጥ ብሆን ኖሮ እንዲህ ብዬ እናገር ነበርን?” ብሎ ራስን መጠየቅ ከጥፋት የሚያድን ይመስለናል።

እኛ እጅግ ጥቂት ሆነን የኢትዮጵያ ሴኩላር ሰብዓዊያን ማህበርን የመሰረትን መስራች አባላት፣ ከማንኛውም ሃይማኖት ጋር ያልወገንን መሆናችንን እየገለጽን እና ሃይማኖት የግል መሆኑን ከመገንዘብ ጋር፣ ሃይማኖተኞች ከመሆናችን በፊት ሰው ሁነን የተፈጠርን በመሆኑ ሰብአዊነትን እናስቀድማለን። እናም በህዝባችን መካከል ያለው እጅግ አስፈሪ እና አስጨናቂ የሃይማኖት ውድድር ሩጫ፣ እና በሃገራችን ያለው መንግስትም እጅግ ሃላፊነት የማይሰማው፣ በስልጣን ለመቆየት ሲል ማንኛውንም ህዝብን ለመከፋፈል የሚያስችል ክፍተት ለመጠቀም የማያመነታ እና እስካሁንም የተጠቀመበት አካሄድ ከመሆኑ እና አብዛኛው ህዝብ የገባበት የድህነት፣ ስራ አጥነት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ነጻነት ማጣት፣ የዘር ፖለቲካ ወዘተ… ተደራርበው የህዝባችን መጨረሻው ያሳስበናል።

የጃዋር እና መሰሎቹ አይነት እኩይ ራዕይ እውን የሚሆነው፣ እንደ ቢቢኤኑ አብዲራሂም አይነት ፍጹም ሃሰት የሆኑ ያላፊነት የጎደላቸው ሃይማኖት ነክ ንግግሮች ሊያስከትሉ የሚችሉትን መዘዝ ማስወገድ የምንችለው፣ ሃይማኖት የግል እና የግለሰብ ብቻ መሆኑን በሚያምኑ፣ በሚያረጋግጡ ከሁሉም በላይ ግን ከሃይማኖት በፊት ሰብዓዊነትን በሚያስቀድሙ ሰዎች ተሳትፎ ነውና፣ ሃሳባችንን የምትጋሩ ሁሉ በየሜዲያው ሃሳባችሁን በመግለጽ እንድትቀላቀሉን በአክብሮት እንጠይቃለን። (ፎቶ: Advocacy for Oromia)

በፌስ ቡክ እና ትዊተር ላይም ተከተሉን እንከተላችሁ
የኢትዮጵያ ሴኩላር ሰብዓዊያን
Ethiopian Secular Human (ethiopiansh@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Eunetu Yeneger says

    December 8, 2016 06:26 pm at 6:26 pm

    ለእንደዚህ መሰል አፍራሺና ግላዊ የእብድ መገለጫ ንግግሮች ዳኛው በስሙ የሚነገድበትና በእሳት ውስጥ ሆኖ የመከራውን ጽዋ በጉልበተኞች በግድ እየጨለጠ ያለው የኦሮሞ ሰፊ ሕዝብ መሆን አለበት!የሚያሳዝነው ግን የእብዱ ተናጋሪ ”ኢትዮጵያን ማፍረስ አለበን” ንግግር ሳይሆን በአገር ቤት ባለው አብዛኛው የኦሮሞ ሕዝብ ስም ነጻ በሆነች በለንደን ሲቲ ማክዶናል እየበሉ የሚኖሩ የስብሰባው ታዳሚዎች በጭብጨባ ያሳዩት ድጋፍ ነው! በዚች ታላቅ ሲቲ የምትኖሩ ታማኝ ኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ምስሉን ደጋግማችሁ በማየትና በመለየት ልታናግሯቸውና ልታርሟቸው ትችላላችሁ፤ የሚሰሙ ከሆነ!ተናጋሪው ግለሰብ የግለሰቦችን ድጋፍ ባያገኝ እንደዚህ ባለ ድፍረት መናገር ባልቻለ ነበርና!አንዳንድ በስብሰባው ላይ የነበሩ ሰዎችም ንግግሩ ለኢሕአዴግ መንግሥት ያስገኘለትን የፖለቲካ ፍጆታ ተመልክተው ”የተናጋሪው የግል ድካም ነው” በማለት የሰጡት አዲስ የሽፋን አስተያየት ህሊና ላለው ሰው አብረው በመሆን አጨብጨብው ያጸደቁትን አገርን የማፍረስ አጀንዳ መልሰው መቃረን ስለሚሆን ገና ወደፊት ላለው ለጋራ ዓላማ አብሮ መሰለፍ የሚያስችል አቅምና የመታመን ብቃት የሌላቸው ስለመሆናቸው ታላቅ የማንነት መገለጫ ምልክት ነው የሚሆነው።

    ስለዚህ እንደዚህ ላሉ ወገኖቻችን ያለኝ ወንድማዊ ምክር የጠራና ለጋራ ዓላማ መሳካት የሚጠቅም እውነተኛ አቋም ይኑራችሁ፤ መታመን ከሊለ እንኳን እንደዚህ ያለ ታላቅ ሃገራዊ ሥራ ከሌሎች ወገኖች ጋር መሥራት ይቅርና የየእለት የግል ኑሮንም መምራት ያስቸግራል!ለውጤት ጽናት ያለው አቋም እጅግ ወሳኝ ነውና አብሮነትን በዚህ መልኩ እናጠናክረው!!!ቸሩ በቸርና ፍሬ ባለው ሥራ በጋራ ይጥመደን!!!

    ምንጊዜም ቢሆን
    እውነቱ ይነገር
    ካለሁበት

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule