• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ያለ ምንም ደም አዲስ ዓመትን”

September 13, 2012 02:04 pm by Editor Leave a Comment

በ2001ዓም ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም “እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰህ” በሚል ርዕስ የጻፉት ድንቅ ጽሁፍ የያዘው መልዕክት በዚህ አዲስ ዓመትም ትልቅ ትርጉም ያለው ሆኖ ስላገኘነው “ያለ ምንም ደም አዲስ ዓመትን” በማለት ርዕስ ሰጥተነው እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ በርዕሱ ላይ ላካሄድነው መጠነኛ ለውጥ ኃላፊነቱን እንወስዳለን፡፡

የሰሞኑ መልካም ምኞች የሚመስል ስሜት የምንለዋወጠው “እንኳን አደረሰሽ (አደረሰህ)” በመባባል ነው። ከየት ተነስተን ወዴት እንደደረስን ግን አናውቅም። ምኞቱ የሚገልጸው ሁላችንም በአንድነት ወደተሻለ ደረጃ መሸጋገራችንን ይመስላል፤ እውነቱ ግን ሁላችንም በአንድነት ቁልቁል ወርደናል።

“… ጋሼ ማረኝ ማረኝ፤ ጋሼ ማረኝ ማረኝ
ዶሮ ብር አወጣች እኔን ሥጋ አማረኝ! …”

ተብሎ የተዘፈነበት ጊዜ መቶ ዓመት ሊሆነው ነው፤ ዛሬ እኛ ምን ብለን ልንዘፍን ይቃጣናል?

ለእኔ “ያለምንም ደም” የሚለው የደርግ መዝሙር ተስማሚ ሆኖልኛል። አንድ ዶሮ መቶ ብር፣ አንድ ኪሎ ቅቤ መቶ ብር፣ አንድ ኪሎ ሽንኩርት ስድስት ብር፣ አንድ እንጀራ ሁለት ብር ተኩል፣ አንድ እንቁላል አንድ ብር ከሃምሳ ሲሆን፣ የማገዶውንና የውሀውን ትተን (ውሀ ከዘይት መወዳደር ጀምሮአል፤ በአንድ ዓመት ያህል ጊዜ ውስጥ ወደ ሁለት ሺህ ስድስት መቶ ብር ግድም ከፍያለሁ!) አንድ ድስት የዶሮ ወጥ ምን ያህል ሊያወጣ ነው እንግዲህ እንኳን አደረሳችሁ ማለት መልካም ምኞት ነው ወይስ እርግማን? ብዙ ሰው ከ2000 ወደ 2001 የተላለፈው “ያለምንም ደም” ውሀውም ተወዶበት ነው። ለመሆኑ ለሚሌኒየም ግርግርና ከበሮ ምን ያህል ገንዘብ ወጥቶ ይሆን? ቂል አትበሉኝና የወጣው ገንዘብ ለእያንዳንዱ ገበሬ ለዓመት በዓሉ ሃምሳ ብር ቢታደል የሚያስፈልገው ወጪ 500,000,000 ብቻ ነው፤ ጥድቁ ቀርቶ ሆነና …

የደላቸው ሰዎች በምድረ ኢትዮጵያ የሉም ማለት አይለም። እነሱ አዲሱን ዓመትሲቀበሉ ግቢያቸውን ደም በደም አርጥበውታል፤ የዶሮውንም፣ የበጉንም፣ የፍየሉንም፣ የሰንጋውንም ደም ደሀው አላየም። ሀብታሞቹ ለርኩሳን መንፈሶች ገብረውልን የምሳቸውን ሰጥተው ባይገላግሉን በቅዥት እናልቅ ነበር! ሀብታሞች ርኩሳን መንፈሶችን መክተውልናል። ለአዲስ ዓመት ትልቁ ነገር ደም ማፍሰሱ ነው እንጂ ሥጋ መብላቱ አይደለም። ማን ነበር …

“… እኔ ስበላ አይተህ ደስ ይበልህ እንጂ
ያንተ መከጀልስ ለምንም አይበጅ፤ …” ያለው?

ዛሬ መከጀልም ቅንጦት እየሆነ ነው። “ደሀ በሕልሙ ቅቤ ባይጠጣ” ይባል ነበር – ዱሮ። ዛሬ ሕልም ማለም ቀርቷል፤ ዛሬ ሕልሙ ወደ ቅዠት ተለውጦአል። የዘንድሮው ቅዠት ክፋቱ እስቲተኙ አይጠብቅም፤ የሚያስለፈልፈው ደሀውን ብቻም አይደለም፤ በእውንም በጥጋብም ያቃዣል። “ኢኮኖሚው እያደገ ነው፤ የህዝቡ ኑሮ እየተሻሻለ ነው” እያሉ በጠኔ ለሚሰቃዩት መንገር ቅዠት አይደለም?

እኔ ከልጅነቴ ጀምሮ ለዕንቁጣጣሽ ዶሮ ማረድ ያልቻለ ደሀ አይቼ አላውቅም። በሠፈሬ የተካንሁት እኔ ብቻ ስለነበርሁ፣ ለዶሮ አራጅነት በየቤቱ እጠራ ነበርና በደንብ አውቃለሁ። ደሀው የሚቸገረው የዶሮውን መልክ መረጣ ላይ ነበር። ገብስማ፣ ጥቁር፣ ወይም ዛጎልማ ወይም ሌላ ነበር ትልቁ ችግር። ዛሬ ችግሩ ሌላ ሆነ፤ ዕንቁጣጣሽን የምንቀበለው ያለ ምንም ደም ሆነ። ሃያኛውን ምዕተ-ዓመት ስንቀበል ደሀው ዶሮ ማረድ ይችል እንደነበረ አትጠራጠሩ። ሃያ አንደኛውን ምዕተ-ዓመት ስንቀበል ዶሮ ማረድ ያለመቻላችን ዕድገት መሆኑ ነው? የመቶ ዓመት ዕድገት ለዕንቁጣጣሽ ዶሮ ማጣት!

ደሀነትን ማጠፋት ሲባል ግራ ይገባኝ ነበር፤ ለካስ ያውም ከተገኘ በአምስት ብር ደረቅ ሽሮ፣ የሦስት ብር እንጀራ ለእንቁጣጣሽ መብላት ነው! ማን ነው ይህንን ለደሀው የመረጠለት? ደሀነቱ እንኳን ደሀውን እኔንም ክፉኛ ተሰማኝ። ለዶሮ መግዣ እያልሁ ለዓመት በዓል ትንሽ ገንዘብ የምሰጣቸው ሰዎች ነበሩ። በአቅሜ ያስለመድኋቸው ገንዘብ ዛሬ የዶሮዋን አንድ ክንፍ አይገዛም። ታዲያ እኔ አልደኸየሁም? ዱሮ ለዶሮም፣ ለቅቤም የምሰጠው ዛሬ ለዶሮ ብቻ የሚበቃ ሲሆን አልደኸየሁም? ተያይዘን ነው እየደኸየን ያለነው፤ በደርግ ዘመን አንድ ሰሞን የአምቦ ውሀና ክብሪት ጠፋና ህዝብ ተንጫጫ። በራዲዮና በቴሌቪዥን የተሰጠው መልስ “አድኃርያን ለውስኪ መበረዣና፣ ለሲጃራ ማቀጣጠያ ቢቸግራቸው ሰማይ የተደፋባቸው መሰላቸው” የሚል ነበር። ራዲዮኑንና ቴሌቭዥኑን ሲቆጣጠሩት ማሰብ ይቸግራል መሰለኝ።

እንዲያውም ሌላ ሃሳብ መጣብኝ። አድባሮቹ፣ ቆሌዎቹ፣ ምናምንቴዎቹ የሰው ደም ለምደው እንዳይሆን፤ ያለ ምንም ደም የሰውንም ደም ጨምሮ ከሆነ በዚሁ ይለፍልን፤ ሌላ ምን እንላለን።

ምንጭ: Mesfin Woldemariam Blog

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule