• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ናቡቴ” የኢትዮጵያ ሕዝብና “አክዓብ” ገዢዎቹ – ፩

January 31, 2016 07:53 am by Editor 2 Comments

በኢትዮጵያ የግማሽ ምዕተዓመት የፖለቲካዊ ለውጥ ንቅናቄ ታሪክ የመሬት ጥያቄ ዋነኛውና አብዮትን ማሳካት የሚችል ጉልበት ያለው የህዝብ ብሶት መገለጫ መሆኑ የማያሻማ ነው፡፡ ፍውዳላዊውን የሰለሞናዊ ስርወ መንግሰት ንጉሳዊ ስርዓት ግብዓተ መሬት ካፈጠኑት አብይ የሕዝባዊ ብሶትና ምሬት መገለጫ የለውጥ ንቅናቄ መርሆች መኸል “መሬት ለአራሹ” የተሰኘው የተማሪዎች ንቅናቄ መርህ የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል፡፡

በንጉሳዊው የፊውዳል ስርዓት የንጉሱ ጋሻ ዣግሬዎች ማለትም መኳንንቱ እና መሳፍንቱ መላውን የሀገሪቱ ሰፊ የገጠር እርሻ መሬት በባለቤትነት (በባላባትነት) ተቀራምተው፤ ባለርስት በመባል ድኸውን ገበሬ ጭሰኛ በማድረግ ጉልበቱንና ምርቱን እየበዘበዙ ለዘመናት ህልውናውን እየፈተኑ፣ ኑሮውን ከድጥ ወደ ማጥ እየገፉ ጭቆናንና በደልን አንሰራፈተው ቢቆዩም የጭሰኛው ገበሬ ልጆች የሆኑት የለውጥ ፋኖ ያነገቡ ተማሪዎች “መሬት ለአራሹ” በተሰኘ መርህ ባፋፋሙት የአብዮት ንቅናቄ ሰርዓቱ ለማክተም ተገዷል፤ ምንም እንኳ ይህ አብዮት ፍሬ ያላፈራና በጥቂት ወቶአደሮች የግል አምባገነናዊ ባህርይ ምክንያት የአብዮቱ ባለቤት ከሆነው የኢትዮጵያ ሕዘብ የተቀማና እስከዛሬም ያልተመለሰ ቢሆንም የ“መሬት” ጥያቄ ፖለቲካዊ ንቅናቄ ግን ምን ያህል አቅም እንዳለው ለመገንዘብ ይረዳል፡፡

ኢትዮጵያ ዛሬም በህዝብ መሬት ላይ አዛዡ ናዛዡ አኔ ነኝ ብሎ አዋጅ ባስነገረ አንዲሁም የመሬት ባለሙሉ መብት አርሱ ብቻ አንደሆነ የሚያትት ፖሊሲ በቀረፀ ገዢ ቡድን ነው የምትተዳደረው፤ ዛሬ ላይ ማንኛውም የሀገሪቱ ዜጋ ስለሚኖርበት፣ ስለሚያርስበት፣ ሞቶ ስለሚቀበርበት የቀዬ መንደሩ መሬት ዋሰትና የለውም፤ ገዢው ቡድን በፈለገ ጊዜ የእርሻውን መሬት ወደ ኢንዱስትሪ ዞን ፣ የመኖሪያውን መንደር ወደ ንግድ ማዕከል ሕንፃ መገንቢያነት የመለወጥ ስልጣን ባለቤት ነው፤ መሬትን ሽጦና ለውጦ ትርፍን አጋብሶ ማደርም ለገዢው ብቻ የተፈቀደ መብት ነው፡፡

ለአርሶ ኗሪው የሀገሬ 85% ህዝብ የእርሻው መሬትና እስትንፋሱ፤ የስጋና ነብስን የመሰለ ጋብቻ የመሰረቱ ናቸው፤ ይህ ማለት ደግሞ ለመኖር ያርሳል፣ ለማረስ ደግሞ የሚታረስ መሬት ይሻል ማለት ነው፤ እናም የሚያርስበትን መሬት ማንም ሊያሳጠው፤ በፈለገም ጊዜ ሊነጥቀው አይገባም!! አርሶ የሚበላበትን የእርሻ መሬት መንጠቅ አስትንፋሱን ከስጋው ከመለየት የሚተናነስም አይደለም፤ ለምስኪኑ የኢትዮጵያ ገበሬ ማረስ እና መተንፈስ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው፡፡ naboth and ahab

የክርስትናው ቅዱስ መፅሐፍ ከክርሰቶስ ልደት በፊት በእስራኤል ህዝብ ላይ ነግሰው የነበሩ ነገስታትን ታሪክ በሚተርክበት መፅሐፈ ነገስት በተሰኘው ንዑስ መፅሐፍ የመጀመሪያ ክፍል በምዕራፍ ፳ ከቁጥር ፩ አስከ ፳፱ ላይ አንድ ታሪክ ያስነብበናል፤ ጊዜው በሰማሪያ ላይ አክዓብ የተባለ ንጉስ የነገሰበት ዘመን ሲሆን በዚህ ንጉስ መኖሪያ አጠገብ የወይን ቦታ (መሬት) ያለው ናቡቴ የተሰኘ ምስኪን ሰው ነበረ፤ ንጉሱ አክዓብም የናቡቴን የወይን ቦታ ለራሱ ሊያደርግ ወደደና “ይህ የወይን ቦታህ በቤቴ አቅራቢያ ነውና የአትክልት ስፍራ አደርገው ዘንድ ስጠኝ አኔም በርሱ ፈንታ የተሻለ የወይን ቦታ ልስጥህ የምትወድም ቢሆንና ከተሻለህ ግምቱን ገንዘብ ልስጥህ” ብሎ ናቡቴን ተናገረው፤ ናቡቴ ግን የአባቶቹን ርስት ይሰጠው ዘንድ ፈቃደኛ አንዳይደለ ለንጉስ አክዓብ መለሰለት፤ ንጉሱም አጅግ ተበሳጨ፣ ተናደደም፤ ሚስቱ ኤልዛቤልም ይህን ብስጭቱንና ንዴቱን ተመልክታ የሚፈልውን ማግኘት ካልቻለ የንግስናው ፋይዳ ምን አንደሆነ ጠየቀቸው፣ በክፉ ምክርም ልቡን መርዛ ናቡቴን ገድሎ የወይኑን ስፍራ ያለከልካይ ሊወርስ አንደሚቻለው ተስፋ ሰጠችው፤ አንደእርሷም ክፉ አሳብ ናቡቴ በሐሰት ምስክር በግፍ ተገደለ፣ አክዓብም የናቡቴን የወይን ቦታ ይወርስ ዘንድ ወደ ስፍራው ወረደ ነገር ግን ምስኪኑ ናቡቴ ለርስቱ በግፍ ቢገደልም ንጉሱ አክዓብ የወይን ስፍራውን አይወርስም፡፡

የአሻውን ይፈፅም ዘንድ ከልካይ የሌለበት የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ገዢ ቡድንም አክዓብ በመኖሪያ ስፍራው አጠገብ የነበረውን የምስኪኑ ናቡቴን የወይን ስፍራ በተመለከተበት ዓይን የመንበረ መንግሰቱ መቀመጫ በሆነቸው አዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ የኦሮሚያ አርሶ አደሮችን መሬት ከምስራቅና ምዕራብ እንዲሁም ከሰሜንና ደቡብ አየ፣ ተመለከተ፤ በተመለከተውም ነገር ምን ያህል ሊጠቀምበት፣ እልፍ አእላፍ ትርፍም ሊያጋብስበት አንደሚችል አስቦ ጥቅሙን አሰላ፤ በስሌቱም ውጤት አጅግ ሐሴት አደረገ፤ ለሐሴቱም ስኬት በኤልዛቤል ክፉ ምክር አምሳል ያዘጋጀውን የአዲስ አበባና የአሮሚያ ልዩ ዞን የጋራ ማስተር ፕላን (ዕቅድ) የሚል ሴራ ይዞ ቀረበ፡፡

ናቡቴ የንጉስ አክዓብን ህልውና የሚፈትን ጥያቄ ውድቅ አንዳደረገ ሁሉ፤ ምስኪኑ የአዲስአበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ገበሬና ልጆቹም ይህን ከመኖሪያቸው መንደርና ከእርሻቸው መሬት የሚያፈናቅል፤ ህልውናቸውንም አደጋ ላይ የሚጥል ሸረኛ ፕላን (ዕቅድ) እንደማይቀበሉ አደባባይ ወተው ተቃወሙ፤ ኤልዛቤላዊው ስርዓትም ናቡቴያውያን የመሬት ባለመብቶችን የህይወት ዋጋ አስከፍሎ አሳቡን ለማሳካት ብዙ ቢጥርም፤ አክዓብ ከናቡቴ ደም መፍሰስ በኃላ የወይን ስፍራውን ሊወርስ ወርዶ አንዳልተሳካለት ሁሉ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሐን ዜጎችና ተማሪዎችን ውድ የሕይወት ዋጋ ካስከፈለ የእምቢተኝነት ፅናት በኃላ የኢትዮጵያ ገዢ ቡድንም በአዲስ አበባ ዙሪያ ያለውን የኦሮሚያ ምስኪን ገበሬዎች የመኖሪያና የእርሻ መሬት ሊወርስ አልተቻለውም!! አይቻለውምም!!(leጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ በተለይ የተላከ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    February 2, 2016 07:37 pm at 7:37 pm

    Religion mixed with politics .
    Poor mix

    Reply
  2. gud says

    February 2, 2016 07:39 pm at 7:39 pm

    Every thing is about striking a balance .
    Development vs human right
    Trust vs suspicion
    Love vs hate etc
    I support the master plan as long as it is implemented fairly .

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule