• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ ዠ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት ውድድር

June 1, 2016 06:27 am by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት ውድድር ተመዝግበው ቅስቀሳ እያካሄዱ ነው። ፍላየር እያደሉ ነው። ፍላየሩ ላይ የዌብ ሳይት፣ ኢሜይል አድራሻ፣ እንዲሁም የትምህርትና የሥራ ልምዳቸው ተደርድሯል። የዌብ ሳይታቸው  www.z.com ይነበባል። የሥራ ልምዳቸውና የትምህርት ደረጃቸው ደግሞ እንደሚከተለው፣

የሥራ ልምድ፣

በዩናይትድ ኔሽንስ ኢትዮጵያን ወክሎ መቀመጥ       ከሃምሌ 2007 ጀምሮ
የባህል ሚኒስቴር፣ ሚኒስትር ዴኤታ                            ከመጋቢት 2007 እስከ ሃምሌ 2007
የማስታወቂያ ሚኒስቴር፣ የቅርንጫፍ ዳሬክተር         ከግንቦት 2007 እስከ ሃምሌ 2007
የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል                               ከምርጫ 2005 ጀምሮ
የኢሃዲግ ፍቅር ቴአትር ቤት አርቲስቲክ ዳሬክተር   ከየካቲት 2007 እስከ  መጋቢት 2007

አዎን፣ አቶ ዠ እንደሮኬት ተተኩሰው ሚኒስቴር ዴኤታ ደርሰዋል።

የትምህርት ደረጃ፣

ዶክትሬት (PhD)
ከ Fastlane University                                         2007

አዎን፣ አቶ ዠ እንዴት እንደሆነ ሳያውቁት ዶክትሬት ተጭኖባቸዋል። አብሮአቸው የህዝብ ምክርቤት የሚቀመጥ የሌላ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ነው ሃሳቡን ያቀረበላቸው። “በመላላክ ተማሩ” በማለት። “ጊዜ አይወስድም እኮ!” ጨመረበት። በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ዶክትሬቱ ተላከላቸው፣ በፖስታ። ከዚያም ባማረ ፍሬም ተደርጎ ቢሮአቸው ውስጥ ግድግዳ ላይ ተሰቀለ። አቶ ዠ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያን፣ የባችለርና የማስተርስ ድግሪ ፕሮግራምን “ትሪፕል” መተው፣ ዶክትሬት ተጫነባቸው። አልከበዳቸውም። ወረቀቱ ቢሮአቸው ባጌጠ ፍሬም ተከንፎ የተሰቀለ ሰሞን ቀና ብለው እንኳን አይተውት አያቁም። ያፈሩት ይመሥል። የኋላ የኋላ ግን በድፍረትና በ“የኔ ነው” ባይነት በኩራት ይመለከቱታል። አንዳንድ “ቀናተኞች” ግን የኼ ድግሪ “የወፍጮ ድግሪ ነው፣ ውሃ አያነሳም!” በማለት ቢተችዋቸውም ይመኩበታል። “የወፍጮ ድግሪ፣ የሙቀጫ ድግሪ፣ ድግሪ ድግሪ ነው” ይላሉ ለራሳቸው፣ “ዶ/ር” ዠ።

******************************

አቶ ዠ በዩናይትድ ኔሽንስ ኢትዮጵያን ወክለው መቀመጥ ከጀመሩ 47 ቀናት እንዳለፉ ዩናይትድ ኔሽንስ አዲስ ዋና ጸሃፊ የሚመርጥበት ጊዜ ደረሰ። በነዚህ 47 ቀናት አቶ ዠ “seasoned diplomat” ሆንኩ ብለው አሰቡ። “Seasoned Diplomat” የሚለውን ሃረግ የሰሙት ጎናቸው ከሚቀመጠው የዩጋንዳ ተወካይ ነው። Seasoned Diplomat መሆናቸውን ለሚጠየቁት ጥያቄ ሁሉ ቀጥተኛ መልስ ባለመሥጠት አረጋገጡ። ለምሳሌ፣

“የሰሜን ኮርያን የኒኩልየር መሳሪያ ፕሮግራምና ከቻይና ጋር ያላትን ግንኙነት፣ ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር ካላት ትብብር ጋር በማነጻጸር እንዴት ይመለከቱታል?” ተብለው ሲጠየቁ፣

መልሳቸው፣

“In fact ነገሩ ሎድድ ነው። It is complicated፣ የተወሳሰበ ነው።” ብለው ይጀምሩና ኢህአዲግ ልማታዊ መንግሥት ሥለመሆኑ ይነግሩሃል።

“ታዲያ ልማታዊ ከሆናችሁ ለምን ህዝባችሁን በተደጋጋሚ ረሃብ ያጠቃዋል?” ብለህ ተከታታይ ጥያቄ ጣል ብታደርግ

“In fact ነገሩ የተወሳሰበ ነው። ትኩረታችን የብረታብረት፣ የስኳር እንዱስትሪና የኮንዶሚኒየም ቤቶች ላይ ነው” ይሉሃል።

“ቤት መሥራት ጥሩ ነው። ታዲያ በብዛት ቤት የምትሰሩ ከሆነ ለምንድነው ታዲያ የቤት ችግር በጣም አንገብጋቢ የሆነው? የቤት ኪራይ ዋጋስ ጣራ ሰንጥቆ ሰማይ የደረሰው?” ብለህ መጠየቅ አትፈልግም። ምክንያቱም መልሱ “complicated፣ የተወሳሰበ” ይሆናልና። ስለዚህ ቀለል ያለ ጥያቄ ነው ብለህ አስበህ፣ ቀጥተኛ መልስ አገኛለሁ ብለህ አስበህ፣

“ቁርስዎን ምን በሉ?” ብለህ ብትጠይቃቸው መልሳቸው የሚጀምረው፣

“In fact ነገሩ ሎድድ ነው. . .” በሚለው ሃረግ ነው። Seasoned Diplomat!

****************************

አቶ ዠ “Seasoned Diplomat” ሆንኩ ብለው አሰበው አላቆሙም። ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት እመጥናለሁ ብለው አሰቡኛ ለመወዳደር ወሰኑ። እና አቶ ዠ የምረጡኝ ቅስቀሳቸውን በዕረፍት ሰዓት ኒው ዮርክ ባለው የዩናይትድ ኔሽንስ ህንጻ በየቢሮውና በየኮሪደሩ እየተዘዋወሩ ውስጥ ውስጡን ጀምረዋል። የአፍሪካ ሃገራት ተወካዮች ጋ እየተዘዋወሩ ሃሳባቸውንና ምኞታቸውን በመግለጽ ድጋፍ እንዲለግሱዋቸው ተማጽነዋል። የዩጋንዳውን ተወካይ ኮሪደር ላይ አግኝተው ሃሳባቸውን ሲያዋዩት “of course Mr. Z (ዚ)” ብሎ ሳቀ። ባቅራቢያው ያልፍ  የነበረው የዛምቢያው ተወካይም “whatever he does, I will too, እሱ የሚያደርገውን እኔም አደርጋለሁ” አለ፣ የድጋፍ ሳቅ እየሳቀ፣ ምን እንደሆነ፣ ምን እንደተነጋገሩ ሳይሰማ።

****************************

አለፍ ብሎ ደግሞ የአረብ ሃገራት ተወካዮች ተሰብስበው ቆመው እየጮሁ ያወጋሉ። ይደግፉኛል ብለው ባይተማመኑም “ግፋ ቢል እምቢ ነው። ካለመናገር ደጃዝማችነት ይቀራል” አሉ አቶ ዠ ለራሳቸው። “ካለመጠየቅም የዩኤን ጸሃፊነት ይቀራል” ብለው ፍላየራቸውን ይዘው ተጠጓቸውና ማስረዳት ጀመሩ።

“how do you say your name? ስሞትን በትክክል እንዴት ያነቡታል?“ሲል አንዱ ጠየቀ። ዠ ማለት ከብዶታል።

“ዠ” አሉ አቶ ዠ።

“ጀ” አለ አረቡ። ‘የለም ዠ ነው’ ሲሉ አሰቡ አቶ ዠ። “አረቦች ለካ ዠ ማለት አይችሉም። ዠበናችን ጀበና፣ ዣንጥላችን ጃንጥላ የሆኑት በነሱ ምክንያት ነው፣ አረብኛ ወደኛ ሃገር በመሰደዱ ነው” ብሎ አንዱ ባህል ሚኒስቴር ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርቦ የሰሙት ትዝ አላቸው።

“you can call me Z፣ ዘ በለኝ።” አሉ ፈገግ ብለው።

“Z like Zebra. . .?” አለ አረቡ እየሳቀ። ”ምናባቱ እንደ ሜዳ አሀያ ያዥጎረጉረኛል?“ሲሉ አሰቡ አቶ ዠ በሆዳቸው። ሆኖም ግን የሆድን በሆድ አድርጎ መስማማት ሳይሻል አይቀርም. . . “ካለመስማማትም ደጃዝማችነት ይቀራል” ተብሎ ይሆን?

“or Z like Zero” አለ ሌላው አረብ።

“Z like Zoro” መለሱ አቶ ዠ. . . እና ሳቁ። የላቲን አሜሪካውን ዝነኛ፣ ለድሆች የቆመ ሽፍታ በማስታወስ።

“Z like Zoro” ሁሉም ተቀባበሉና ሳቁ። የሳቸውን መመረጥ እንደሚደግፉ ሁሉም ተስማሙ። አቶ ዠ ተሰናብተው ሄዱ። አለፍ ካማለታቸው፣

“መጁኑን” የሚል ቃልና ሳቅ ሰሙ። ለእሳቸው የተወረወረ ቃል ይሆን? ቃል አልተነፈሱም። ”ዝም ካለማለትም ደጃዝማችነት ይቀራል“ ተብሎ ይሆን?

*****************************

ከዚያ ቀጥሎ ከምሥራቅ አውሮፓ የመጡ ተወካዮች አንድ ቦታ ተሰብስበው አዩና ቀርበው ሃሳባቸውን አሥረዱ። ሥማቸውን ተናገሩ። ገረማቸው። በትክክል ሥማቸውን ሚሮኮ የሚባለው የክሮኤሽያ ተወካይ አሳምሮ ጠራው።

“ዠ አይደለም? ምን ችግር አለው፣ ቀላል ነው። እኛም እኮ ዠ የሚል ፊደል አለን።” አቶ ዠ ተደሰቱ። ከምሥራቅ አውሮፓ የመጡት ተወካዮች የሳቸውን መመረጥ እንደግፋለንም አንደግፍምም አላሉም። መልካም ዕድል ብቻ ተመኙላቸው።

*****************************

አቶ ዠ ይህንን ቅስቀሳ አካሄደው ከጨረሱ በኋላ ወደ ከተማ አቀኑ። አቶ ዠ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት ያስፈልጋል ብለው ያሰቡትን አይነት አለባበስ ለሟሟላት ወደ ልብስ መገብየት አቀኑ። እናም አንድ ትልቅ የገበያ  አዳራሽ ገብተው ከሱቅ ወደሱቅ እየተዘዋወሩ ልብስ ማማረጥ ያዙ. . .

“አንተ ሌባ” የሚል ድምጽ ሲሰሙ ኮት እየለኩ ነበር።

“አንተን ነው፣ አንተ አጭበርባሪ” ደገመው ሰውየው። ሌሎችም ተከተሉት።

አቶ ዠ ሽምቅቅ ብለው ከኮቱ ውስጥ ሙልጭ ብለው ወለቁ። የሚገቡበት ጠፋቸው። ለካስ የሳቸውን ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋናጸሃፊነት መወዳደር ሰምተው ውድድራቸውን የሚቃወሙ ነበሩ።

“ገና በህግ ትጠየቃለሁ፣ አንተ አጭበርባሪ መፈከር ጸሃፊ! ሥራ መሥራት መፈክር መጻፍ መሰለህ? ‘ሙያ በልብ ነው። በመፈክር አይደለም!’ የሚሉ ሰዎች ሥልጣን ሲይዙ እንዳንተ ያለው አጭበርባሪ በወሬ አዳሪ በህግ ይጠየቃል”

****************************

አቶ ዠ ተወራጩ። ላብ በላብ ሆነዋል።

“ተነሳ እንጂ! ቡና ፈልቷል፣ ቁርስም ተሰርቷል” ባለቤታቸው ወ/ሮ ዘ ነበሩ።

“ምነው ላብ በላብ ሆንክ? ህልም፣ ራዕይ ነው?”

“ቅ’ዠ’ት ነው . . . ተይኝ ባክሽ ቅ’ዠ’ት ነው. . .” አቶ ዠ እየተጎተቱ ካልጋቸው ውስጥ ወጡ።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule