• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካሰቡት ግብ ለመድረስ ፣ያመኑበትን ዓላማ አንግቦ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ!

January 21, 2017 10:51 pm by Editor 1 Comment

የዛሬ አራት ዓመት ዐማራ ነኝ ብሎ ደፍሮ ለመናገር ብዙ ማሰብና ማውጠንጠን ይጠይቅ ነበር። ምክንያቱም ላለፉት 50 እና 60 ዓመታት በዐማራው ነገድ ላይ የተነዛው ፕሮፓጋንዳ በሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች ዐማራ ነኝ እንዳይሉ ገደብ የጣሉ ነበሩ። የመጀመሪያው ምክንያት ዐማራው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምን በመሆኑ፣ ራሱን ወደ ነገድ ደረጃ ማውረድ ውርደት ወይም ከኢትዮጵያዊነት የሚያፋታው አድርጎ መቁጠሩ አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት ነው። ሁለተኛው በኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ የሩቅና የቅርብ፣ የውጭና የውስጥ ጠላቶች የተራገበው ኢትዮጵያን የማጥፋት የተቀነባበረ ዘመቻ ዋነኛው ዒላማ ዐማራው በመሆኑ፣ የዐማራውን ማንነት ጥላሸት የቀባ፣ መልካም ስሙንና ዝናውን ያጎደፈ፣ «በጡት ቆራጭነት፣ በወራሪነት፣ በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝ ብሔርነት፣ በነፍጠኝነትና በኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጠሩ ለተባሉ ችግሮች ሁሉ ፈጣሪ» ተደርጎ በመወንጀሉ ምክንያት የዐማራው ልጆች ራሳቸውን ዐማራ ነኝ እንዳይሉ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳደረ መሆኑ ነው።

በነዚህና በሌሎች ተዛማጅ ምክንያቶች የዐማራው ልጆች፣ በመሰል የሌሎች ነገድ ልጆች ተክደውና ተገድፈው በነገዱ ላይ፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ ቡድኖችና ስብስቦች ከስም ማጥፋት እስከ ዘር ማጥፋትና ዘር ማጽዳት ወንጀል ሲፈጸምበት፣ ‘ለምን? እንዴት?’ ያሉት እምብዛም እንደነበሩ በነገዱ ላይ የደረሰው ዕልቂትና የዕልቂቱ አለማቋረጥ ጉልህ ማሳያ ነው። ይህን የዐማራው ነገድ ልጆች፣ በኢትዮጵያዊነት ራሱን ደብቆ  የወገኑን ዕልቂት እያየ እንዳላየ፣ እየሰማ እንዳልሰማ የሆነውን፣ ወደራሱ ኅሊና ተመልሶ ዘሩን ከፈጽሞ ጥፋት ለመታደግ እንዲችል፣ ዐማራው በማንነቱ ዙሪያ ተደራጅቶ፣ ማንነቱን አስጠብቆ፣ የኢትዮጵያን አንድነት እንዲያስጠብቅ ጥሪ ያቀረቡት ክቡር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ እንደነበሩ እናስታውሳለን።

ሆኖም ዐማራው፣ ለቀረበው ኅልውናውን የማስጠበቅ ጥሪ የሰጠው ምላሽ፣ ከተደገሰለት ጥፋት ጋር የተጣጣመ ባለመሆኑ፣ ፕሮፌሰር አሥራት በዘረኛው ወያኔ አገዛዝ ታስረው እንዲገደሉ መደረጉን የምናስታውሰው በቁጭት ነው።  የአሥራት መገደል በተወሰነ ደረጃ ተነሳስቶ የነበረው የዐማራዊነት ማንነት እንቅስቃሴ ከመዳከም አልፎ፣ እንዲከስም አደረገ። ይህም ዐማራን ለማጥፋት የዘመናት ዝግጅት ያደረገው ወያኔ፣ የዐማራውን ልጆች፣ ያለይሉኝታና እሳ፣ በተገኘበት እንደክፉ አውሬ እያደኑ ጨረሱት። ዐማራውን በገፍና በግፍ እያደኑ ሲጨርሱ፣ ከዐማራው ወገን ኧረ ለምን? የሚል ድምፅ ባለመሰማቱ፣ ወያኔ በመሀል፣ በምሥራቅ፣ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብ  ለዘመናት የኖረውን ዐማራ አገርህ አይደለም፣ ካገር ለቀህ ውጣ በማለት ሀብት ንብረቱን ዘርፈው አባረሩት። ዐማራው በአያት እና ባባቶቹ  ሕይዎት፣ አጥንትና ደም ተጠብቃ በኖረችው አገር የመኖር መብቱን ተነጠቀ።

ይህስ በዛ! ያሉ ወገኖች፣ ከተሸፈኑበት ኢትዮጵያዊ ካባ ራሳቸውን ገልጠው፣ ለወገናቸው ድምፅ መሆንን መረጡ። እነዚህ ለወገናቸው ራሳቸውን ቤዛ ለማድረግ የቆረጡ ወገኖች« ዐማራውን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደግ!» በሚል መፈክር  ጥፋት ለታወጀበት የዐማራ ነገድ ድምፅ ለመሆንና ዐማራው ራሱን አደራጅቶ ኅልውናውን እንዲያስጠብቅ ሲንቀሳቀሱ፣ ከማኅበረሰቡ የተገኘው መልስ ቀና አልነበረም። በማንነት ዙሪያ መደራጀት፣« ወያኔን መሆን ነው»፣« ወያኔ በቀደደው ቦይ ገብቶ መፍሰስ ነው»፣ «ኢትዮጵያን ማፍረስ ነው» ከማለት አልፎ፣« ዐማራ የሚባል ነገር የለም»፣ «ዐማራ ማነው?» የሚሉ ጭፍን ሀሳቦችን በመርጨት ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት፣ ለዐማራው ድምፅ የመሆን እንቅስቃሴውን በለጋው ለመቅጨት ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።

ይሁን እንጂ፣ካሰቡት ግብ ለመድረስ ፤ያመኑበትን ዓላማ አንግቦ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ለድል እንደሚያቃርብ ከልብ የሚያምኑት፣ በቁጥር እጅግ ትንሽ፣ በዓላማ እጅግ ግዙፍ የሆኑት የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት መሥራች አባሎች፣ ሳይሰለቹና ሳይታክቱ ባደረጉት የዐማራውን ነገድ የማሳወቅ፣ የማንቃት፣ የማደራጀትና መረጃዎችን የማሰራጨት ትግል፣ ይኸውና ዛሬ እንደ ተርብ የሚናደፉ፣ እለፈ አዕላፍ የዐማራ ልጆች ዝምታቸውን ሰብረው፣ በማንነታቸው ኮርተው ወገናቸውን ከፈጽሞ ጥፋት ለመታደግና የኢትዮጵያን አንድነት ዳግም ትንሣዔ ዕውን ለማድረግ ሌት ተቀን ከሳይበር እስከ አካላዊ ጦርነት ገጥመው ወያኔንና አጋሮቹን የተፉትን ምራቅ እንዲልሱ እያስገደዱት ይገኛሉ። ይህ የጽናትና የቁርጠኝነት ውጤት ነው። ያለቁርጠኝነት ለድል መብቃት አይቻልምና፣ ሞረሽ ወገኔ ባለፉት አራት ዓመታት በቁርጠኝነት ያካሄደው ዐማራውን የማንቃትና የማደራጀት ትግል ፣ ትግሉን ወደ ትጥቅ ትግል ያሸጋገረው ስለሆነ፣ ይህንም በድል አድራጊነት ለመወጣት ቁርጠኝነቱን በእጥፍ ድርብ ማሳደግ ይጠበቃል።

ስለሆነም፣ የዐማራው ልጆች፣ የተፋፋመው የዐማራው  የመደራጀትና ማንነትን የማስከበር ትግል ለድል እንዲበቃ፣ ሁሉም የዐማራ ልጅ፣ በሀሳብ፣ በቁሳቁስ፣ በገንዘብ፣ በምክር፣ በሰው ኃይል ወዘተ ሊተባበር ይገባል። «ድር ቢያብር  አንበሳ ያስር» ነውና ብሂሉ፣ ሊያጠፋን የዘመተውን አጥፊ ቡድን ጨርሶ ሳያጠፋን፣ አጥፊውን ለማጥፋት ድጋፋችሁን ከምንጊዜውም በበለጠ ዛሬ እንሻለን። ብረትን መቀጥቀጥና ተፈላጊውን ቅርጽ ማስያዝ የሚቻለው ሲግል ሲቀጠቅጡት ነውና፣ ወያኔውም የሚወድቀው ራሱን በፈጠረው ሁለንተናዊ ችግር ተማሮ አደባባይ የወጣው የሕዝብ ቁጣ ሳይበርድ፣ቁጣውን ማጋጋል ለነገ የሚባል ተግባር ሳይሆን አሁኑኑ ልንያያዘው የሚገባን ነው። በመሆኑም በውስጥና በውጭ ለሚደረገው ትግል ገንዘብ ወሳኝ ድርሻ ያለው ስለሆነ፣ ጀግኖቻችን ከእኛ ድጋፍ ማነስ የተነሳ ትግላቸው እንዳይጓተት የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ጥሪውን እያቀረበ ሳይውሉ ሳያድሩ በሚችሉት መጠን የወገናችንን ትግል በገንዘብ ለመርዳት የሞረሽ ወገኔ አማራ ድርጅት ድሕረገጽን (http://www.moreshwegenie.org/) በመጎብኘት፡ የጎፈንድሚ (GoFundMe)፤ የፔይፓል (Paypal)፤ ወይም የባንክ አካውንታችንን  ቁጥር ተጥቅመው የዚህ ታሪካዊ ትግል አካል በመሆን የማያቋርጥ ድጋፍዎን በአንክሮና በትሀትና ያሳስባል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት              ቅዳሜ  ጥር ፲፫ ቀን ፪ሺህ ፱ ዓ.ም.             ቅፅ፭፣ ቁጥር  ፲


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ali says

    February 6, 2017 12:45 am at 12:45 am

    በሁለት ጉዳዮች ለመርዳት ዝግጁ አይደለሁም፦
    1) የገባንበት አዘቅት ጥልቀት እና ስፋት፤ እንክዋን ተለያይተን አንድ ሆነንም በቻልነው፤
    2) እንደ ሄኖክ ያሉ የሞራል መሰረታቸው የተናጋ፤ ለአማራ ሳይሆን ለቲፔኤል ኤፍ የቆሙ በሚመስል ደረጃ እጅግ የወረደ ሃሳብ የሚያቀርቡ ሰዎችን ይዛችሁ የትም አትደርሱም፤ ለአንድነት ፤ በአንድነት ከሚሰሩ ድርጅቶች ጋር ህብረት መፍጠር ያለባችሁ ይመስለኛል፡፡

    አብሲቴ…እያለ የሚጽፍ ሰው ይዝችሁ፡ ከጾታ እኩልነት አንጽር እንክዋን … ኢትዮጵያዊያት እንስት እይታዘብዋችሁም?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule