• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ካሰቡት ግብ ለመድረስ ፣ያመኑበትን ዓላማ አንግቦ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ!

January 21, 2017 10:51 pm by Editor 1 Comment

የዛሬ አራት ዓመት ዐማራ ነኝ ብሎ ደፍሮ ለመናገር ብዙ ማሰብና ማውጠንጠን ይጠይቅ ነበር። ምክንያቱም ላለፉት 50 እና 60 ዓመታት በዐማራው ነገድ ላይ የተነዛው ፕሮፓጋንዳ በሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች ዐማራ ነኝ እንዳይሉ ገደብ የጣሉ ነበሩ። የመጀመሪያው ምክንያት ዐማራው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምን በመሆኑ፣ ራሱን ወደ ነገድ ደረጃ ማውረድ ውርደት ወይም ከኢትዮጵያዊነት የሚያፋታው አድርጎ መቁጠሩ አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት ነው። ሁለተኛው በኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ የሩቅና የቅርብ፣ የውጭና የውስጥ ጠላቶች የተራገበው ኢትዮጵያን የማጥፋት የተቀነባበረ ዘመቻ ዋነኛው ዒላማ ዐማራው በመሆኑ፣ የዐማራውን ማንነት ጥላሸት የቀባ፣ መልካም ስሙንና ዝናውን ያጎደፈ፣ «በጡት ቆራጭነት፣ በወራሪነት፣ በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝ ብሔርነት፣ በነፍጠኝነትና በኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጠሩ ለተባሉ ችግሮች ሁሉ ፈጣሪ» ተደርጎ በመወንጀሉ ምክንያት የዐማራው ልጆች ራሳቸውን ዐማራ ነኝ እንዳይሉ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳደረ መሆኑ ነው።

በነዚህና በሌሎች ተዛማጅ ምክንያቶች የዐማራው ልጆች፣ በመሰል የሌሎች ነገድ ልጆች ተክደውና ተገድፈው በነገዱ ላይ፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ ቡድኖችና ስብስቦች ከስም ማጥፋት እስከ ዘር ማጥፋትና ዘር ማጽዳት ወንጀል ሲፈጸምበት፣ ‘ለምን? እንዴት?’ ያሉት እምብዛም እንደነበሩ በነገዱ ላይ የደረሰው ዕልቂትና የዕልቂቱ አለማቋረጥ ጉልህ ማሳያ ነው። ይህን የዐማራው ነገድ ልጆች፣ በኢትዮጵያዊነት ራሱን ደብቆ  የወገኑን ዕልቂት እያየ እንዳላየ፣ እየሰማ እንዳልሰማ የሆነውን፣ ወደራሱ ኅሊና ተመልሶ ዘሩን ከፈጽሞ ጥፋት ለመታደግ እንዲችል፣ ዐማራው በማንነቱ ዙሪያ ተደራጅቶ፣ ማንነቱን አስጠብቆ፣ የኢትዮጵያን አንድነት እንዲያስጠብቅ ጥሪ ያቀረቡት ክቡር ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ እንደነበሩ እናስታውሳለን።

ሆኖም ዐማራው፣ ለቀረበው ኅልውናውን የማስጠበቅ ጥሪ የሰጠው ምላሽ፣ ከተደገሰለት ጥፋት ጋር የተጣጣመ ባለመሆኑ፣ ፕሮፌሰር አሥራት በዘረኛው ወያኔ አገዛዝ ታስረው እንዲገደሉ መደረጉን የምናስታውሰው በቁጭት ነው።  የአሥራት መገደል በተወሰነ ደረጃ ተነሳስቶ የነበረው የዐማራዊነት ማንነት እንቅስቃሴ ከመዳከም አልፎ፣ እንዲከስም አደረገ። ይህም ዐማራን ለማጥፋት የዘመናት ዝግጅት ያደረገው ወያኔ፣ የዐማራውን ልጆች፣ ያለይሉኝታና እሳ፣ በተገኘበት እንደክፉ አውሬ እያደኑ ጨረሱት። ዐማራውን በገፍና በግፍ እያደኑ ሲጨርሱ፣ ከዐማራው ወገን ኧረ ለምን? የሚል ድምፅ ባለመሰማቱ፣ ወያኔ በመሀል፣ በምሥራቅ፣ በደቡብ፣ በደቡብ ምዕራብ  ለዘመናት የኖረውን ዐማራ አገርህ አይደለም፣ ካገር ለቀህ ውጣ በማለት ሀብት ንብረቱን ዘርፈው አባረሩት። ዐማራው በአያት እና ባባቶቹ  ሕይዎት፣ አጥንትና ደም ተጠብቃ በኖረችው አገር የመኖር መብቱን ተነጠቀ።

ይህስ በዛ! ያሉ ወገኖች፣ ከተሸፈኑበት ኢትዮጵያዊ ካባ ራሳቸውን ገልጠው፣ ለወገናቸው ድምፅ መሆንን መረጡ። እነዚህ ለወገናቸው ራሳቸውን ቤዛ ለማድረግ የቆረጡ ወገኖች« ዐማራውን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደግ!» በሚል መፈክር  ጥፋት ለታወጀበት የዐማራ ነገድ ድምፅ ለመሆንና ዐማራው ራሱን አደራጅቶ ኅልውናውን እንዲያስጠብቅ ሲንቀሳቀሱ፣ ከማኅበረሰቡ የተገኘው መልስ ቀና አልነበረም። በማንነት ዙሪያ መደራጀት፣« ወያኔን መሆን ነው»፣« ወያኔ በቀደደው ቦይ ገብቶ መፍሰስ ነው»፣ «ኢትዮጵያን ማፍረስ ነው» ከማለት አልፎ፣« ዐማራ የሚባል ነገር የለም»፣ «ዐማራ ማነው?» የሚሉ ጭፍን ሀሳቦችን በመርጨት ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት፣ ለዐማራው ድምፅ የመሆን እንቅስቃሴውን በለጋው ለመቅጨት ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።

ይሁን እንጂ፣ካሰቡት ግብ ለመድረስ ፤ያመኑበትን ዓላማ አንግቦ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ለድል እንደሚያቃርብ ከልብ የሚያምኑት፣ በቁጥር እጅግ ትንሽ፣ በዓላማ እጅግ ግዙፍ የሆኑት የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት መሥራች አባሎች፣ ሳይሰለቹና ሳይታክቱ ባደረጉት የዐማራውን ነገድ የማሳወቅ፣ የማንቃት፣ የማደራጀትና መረጃዎችን የማሰራጨት ትግል፣ ይኸውና ዛሬ እንደ ተርብ የሚናደፉ፣ እለፈ አዕላፍ የዐማራ ልጆች ዝምታቸውን ሰብረው፣ በማንነታቸው ኮርተው ወገናቸውን ከፈጽሞ ጥፋት ለመታደግና የኢትዮጵያን አንድነት ዳግም ትንሣዔ ዕውን ለማድረግ ሌት ተቀን ከሳይበር እስከ አካላዊ ጦርነት ገጥመው ወያኔንና አጋሮቹን የተፉትን ምራቅ እንዲልሱ እያስገደዱት ይገኛሉ። ይህ የጽናትና የቁርጠኝነት ውጤት ነው። ያለቁርጠኝነት ለድል መብቃት አይቻልምና፣ ሞረሽ ወገኔ ባለፉት አራት ዓመታት በቁርጠኝነት ያካሄደው ዐማራውን የማንቃትና የማደራጀት ትግል ፣ ትግሉን ወደ ትጥቅ ትግል ያሸጋገረው ስለሆነ፣ ይህንም በድል አድራጊነት ለመወጣት ቁርጠኝነቱን በእጥፍ ድርብ ማሳደግ ይጠበቃል።

ስለሆነም፣ የዐማራው ልጆች፣ የተፋፋመው የዐማራው  የመደራጀትና ማንነትን የማስከበር ትግል ለድል እንዲበቃ፣ ሁሉም የዐማራ ልጅ፣ በሀሳብ፣ በቁሳቁስ፣ በገንዘብ፣ በምክር፣ በሰው ኃይል ወዘተ ሊተባበር ይገባል። «ድር ቢያብር  አንበሳ ያስር» ነውና ብሂሉ፣ ሊያጠፋን የዘመተውን አጥፊ ቡድን ጨርሶ ሳያጠፋን፣ አጥፊውን ለማጥፋት ድጋፋችሁን ከምንጊዜውም በበለጠ ዛሬ እንሻለን። ብረትን መቀጥቀጥና ተፈላጊውን ቅርጽ ማስያዝ የሚቻለው ሲግል ሲቀጠቅጡት ነውና፣ ወያኔውም የሚወድቀው ራሱን በፈጠረው ሁለንተናዊ ችግር ተማሮ አደባባይ የወጣው የሕዝብ ቁጣ ሳይበርድ፣ቁጣውን ማጋጋል ለነገ የሚባል ተግባር ሳይሆን አሁኑኑ ልንያያዘው የሚገባን ነው። በመሆኑም በውስጥና በውጭ ለሚደረገው ትግል ገንዘብ ወሳኝ ድርሻ ያለው ስለሆነ፣ ጀግኖቻችን ከእኛ ድጋፍ ማነስ የተነሳ ትግላቸው እንዳይጓተት የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ጥሪውን እያቀረበ ሳይውሉ ሳያድሩ በሚችሉት መጠን የወገናችንን ትግል በገንዘብ ለመርዳት የሞረሽ ወገኔ አማራ ድርጅት ድሕረገጽን (http://www.moreshwegenie.org/) በመጎብኘት፡ የጎፈንድሚ (GoFundMe)፤ የፔይፓል (Paypal)፤ ወይም የባንክ አካውንታችንን  ቁጥር ተጥቅመው የዚህ ታሪካዊ ትግል አካል በመሆን የማያቋርጥ ድጋፍዎን በአንክሮና በትሀትና ያሳስባል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት              ቅዳሜ  ጥር ፲፫ ቀን ፪ሺህ ፱ ዓ.ም.             ቅፅ፭፣ ቁጥር  ፲


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ali says

    February 6, 2017 12:45 am at 12:45 am

    በሁለት ጉዳዮች ለመርዳት ዝግጁ አይደለሁም፦
    1) የገባንበት አዘቅት ጥልቀት እና ስፋት፤ እንክዋን ተለያይተን አንድ ሆነንም በቻልነው፤
    2) እንደ ሄኖክ ያሉ የሞራል መሰረታቸው የተናጋ፤ ለአማራ ሳይሆን ለቲፔኤል ኤፍ የቆሙ በሚመስል ደረጃ እጅግ የወረደ ሃሳብ የሚያቀርቡ ሰዎችን ይዛችሁ የትም አትደርሱም፤ ለአንድነት ፤ በአንድነት ከሚሰሩ ድርጅቶች ጋር ህብረት መፍጠር ያለባችሁ ይመስለኛል፡፡

    አብሲቴ…እያለ የሚጽፍ ሰው ይዝችሁ፡ ከጾታ እኩልነት አንጽር እንክዋን … ኢትዮጵያዊያት እንስት እይታዘብዋችሁም?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule