• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለመላው የዐማራ ልጅ የተሰጠ ማሳሰቢያ

September 5, 2016 11:33 pm by Editor Leave a Comment

ጉዳዩ፦ የመጭውን ዘመን መለወጫ (መስከረም 1 ቀን 2009 ዓ.ም.) በፈንጠዝያ ሳይሆን፤ ዕለቱን በመሪር ሐዘንና በቁጭት አስቦ ስለመዋል።

ዘረኛው የትግሬ ወያኔ አገዛዝ፣ በዐማራው ወገናችን ላይ ከፋሽስት ጣሊያን በከፋ መልኩ የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ሲፈጽም እነሆ 41ኛ ዓመቱን አገባድዶ በ42ኛው ላይ ይገኛል። በተለይም ካለፈው ሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በጎንደርና በጎጃም በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የጅምላ የጥፋት ዘመቻ አውጇል። የአገዛዙ የኅልውና መሠረት የሆነው ነፍሰ በላው የአጋዚ ሠራዊት ዕድሜና ፆታ ሳይለይ፥  ሕፃናትን፣ ወጣቶችን፣ አዛውንትን፣ ጎልማሶችን፣ ወንዶችና ሴቶችን ቤት ለቤት እያደነ እጅግ መርዘኛ በሆነ ጥይት እየደበደበ የዘር ፍጅት እያደረሰ ነው።

የትግሬ-ወያኔ በከፈተው በዚህ ዐማራን ከምድረ ገጽ የማጥፋት ዘመቻ፣ በሺህዎች የሚቆጠሩ እህት ወንድሞቻችን ተገድለዋል፤ አያሌዎች ቆስለዋል፤ በርካታዎች ታስረዋል፤  ተጫውተው ያልጠገቡ፣ ክፉ ደጉን ያልለዩ ሕፃናት በአረመኔዎቹ ወያኔዎች ተቀጥፈዋል። ልጆቻችን አድገው ከበስቋላው ሕይዎታችን ይታደጉናል ብለው ተስፋ የሰነቁ ወለጆች፣ ተስፋቸውን አጥተዋል፤ ቤተሰብ ፈርሷል። እነዚህ ወንድም እህቶቻችን ሕይዎታቸውን፣ አጥንታቸውን፣ ደማቸውን የሰጡት እና መስዋዕት የሆኑት፣ ለዐማራ የማንነት ጥያቄ ተገቢ መልስ ለማስገኘት ነው። እነርሱ ለእኛ ነፃነት ሲሉ ሞቱ፣ ተሰቃዩ። እኛስ እነርሱ የሞቱለትንና እየተሰቃዩ ላሉበት ክቡር ዓላማ፣ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? ብለን ራሳችን በመጠየቅ፣ ከትውልድና ከታሪክ ተጠያቂነት የሚያድን ተግባር ልንፈጽም ይገባል። ስለሆነም ጀግኖቹ ሰማዕታት እህት ወንድሞቻችን የሞቱለትን ዓላማ ዳር ለማድረስ፣ ዓርማቸውን አንግበን፣ በአንድነት የድሉን ቀን ለማቃረብ በጽናት ወያኔን ልንዋጋው ይገባናል።

ከሁሉም በላይ ትግሉ የሚጠየቀውን ማናቸውንም ዓይነት መስዋዕትነት ለመክፈል፣ የዐማራው ወጣት ትውልድ ራሱን በሁለንተናዊ መልኩ ማዘጋጀትና ትግሉን በቆራጥነት መቀላቀል ነገ ዛሬ የምንለው ጉዳይ አይሆንም። ማድረግ ካሉብን ድርጊቶች  መካከል በጣም በትንሹ በኑሮአችንም ሆነ በሕይዎታችን ምንም ዓይነት ኪሣራ በማያስከትሉት መጀመር ይቻላል። ስለዚህ የሚከተሉትን ተግባሮች በማከናዎን ከዚህ በታች ስማቸው በተዘረዘሩት ሰማዕታት ስም ጥሪያችን እናቀርባለን።

አንደኛ፦   በሚመጣው የዘመን መለወጫ ቀን በዓሉ ከሚጠይቀው ፈንጠዝያ፣ ሣቅና ጨዋታ ተቆጥበን፣ ዕለቱን የሐዘንና የቁጭት መግለጫ የሆነውን ጥቁር ልብስ ለብሰን የኢትዮጵያን ሠንደቅ ዓላማ እያውለበለን እንድንውል፤ ስንበላና ስንጠጣ ሰማዕታቱን በጸሎታችን እንድናስባቸው።

ሁለተኛ፦  ከኢትዮጵያ የሚመጣ እንጀራ እስከ ወዲያኛው ላለመግዛት እንወስን።

ሦስተኛ፦   በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለመጓጓዝ እንወስን።

አራተኛ፦   ከወያኔና ከወያኔ ጋር ንክኪነት ካለቸው ድርጅቶች፣ ሆቴሎች፣ ሱቆች፣ ምግብ ቤቶች፣ ወዘተርፈ አንጠቀም።

አምስተኛ፦      የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች ከሆኑ ሰዎች ጋር የነበረንን ግንኙነት እናቋርጥ።

ስድስተኛ፦      ዐማራው መከበር የሚችለውና ወያኔን እስከ ወዲያኛው ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ሥልጣን አሽንቀጥሮ መጣል የሚችለው በማንነቱ ሲደራጅ ነውና፣ በዐማራ ስም የተደራጁ ድርጅቶችን እንደግፍ፤ እንርዳ።

ሰባተኛ፦  በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመውን ዕልቂት ለዓለም ማኅበረሰብ በስፋት ለማሣወቅ፣ በየአለንበት አካባቢ በሚዘጋጁ ልዩ ልዩ ሕዝባዊ ትዕይንቶች እንሣተፍ፣ የተማጽኖ ደብዳቤዎችን እና መልዕክቶችን ለየአገሩ ፖለቲከኞች፣ መንግሥታት እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች እናድርስ።

ሠንጠረዥ፦ ከሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በጎንደርና በጎጃም በትግሬ-ወያኔ የተጨፈጨፉ ወገኖቻችን ስም ዝርዝር

ተራ ቁጥር የተገዳይ ሙሉ ስም ዕድሜ የመኖሪያ አድራሻ
1. ዕድሜዓለም ዘውዱ 27 ባሕር ዳር
2. ገረመው አበባው 25 ባሕር ዳር
3. ተፈሪ ባዩ 16 ባሕር ዳር
4. ሰሎሞን አስቻለ 25 ባሕር ዳር
5. ሙሉቀን ተፈራ 27 ባሕር ዳር
6. አደራጀው ኃይሉ 19 ባሕር ዳር
7. አስማማው በየነ 22 ባሕር ዳር
8. ታዘበው ጫኔ 21 ባሕር ዳር
9. አሥራት ካሣሁን 24 ባሕር ዳር
10. የሽዋስ ወርቁ 20 ባሕር ዳር
11. ብርሃን አቡሃይ 29 ባሕር ዳር
12. ሽመልስ ታዬ 22 ባሕር ዳር
13. አዛናው ማሙ 20 ባሕር ዳር
14. ሢሣይ አማረ 24 ባሕር ዳር
15. ሞላልኝ አታላይ 21 ባሕር ዳር
16. እንግዳው ዘሩ 20 ባሕር ዳር
17. ዝናው ተሰማ 19 ባሕር ዳር
18. ዋለልኝ ታደሰ 24 ባሕር ዳር
19. ይታያል ካሤ 25 ባሕር ዳር
20. እሸቴ ብርቁ 37 ባሕር ዳር
21. ሞገስ 40 ባሕር ዳር
22. አደራጀው ደሣለኝ 30 ባሕር ዳር
23. ማኅሌት 23 ባሕር ዳር
24. ተስፋዬ ብርሃኑ 58 ባሕር ዳር
25. ፈንታሁን 30 ባሕር ዳር
26. ሰጠኝ ካሤ 28 ባሕር ዳር
27. ባበይ ግርማ 26 ባሕር ዳር
28. አብዮት ዘሪሁን 20 ባሕር ዳር
29. ሀብታሙ ታምራት 27 ባሕር ዳር
30. ሞገስ ሞላ 23 ባሕር ዳር
31. ታደሰ ዘመኑ 26 አዴት
32. እስቲበል አስረስ 19 አዴት
33. አበበ ገረመው 27 ጢስ ዐባይ
34. ይበልጣል ዕውነቱ 24 ጢስ ዐባይ
35. ሰሎሞን ጥበቡ 30 ቻግኒ
36. በረከት ዓለማየሁ 28 ዳንግላ
37. ያየህ በላቸው 30 ዳንግላ
38. ዓለማየሁ ይበልጣል 27 ዳንግላ
39. ሽመልስ ወንድሙ 28 ቡሬ
40. አለበል ዓይናለም 28 ደብረማርቆስ
41. ስሙ ገና የሚጣራ ደካማ እናት ያሉት   ደብረ ማርቆስ ቀበሌ 03
42. ዓይንአዲስ ለዓለም 24 ደብረወርቅ
43. አበጀ ተዘራ 28 ወረታ
44. ደመቀ ዘለቀ 22 ወረታ
45. አለበል ሃይማኖት 24 ወረታ
46. መሣፍንት አማራ 22 እስቴ
47. በለጠ ካሤ 32 ደብረታቦር
48. ይህነው ሽመልስ 30 ደብረታቦር
49.  ማዕረግ ብርሃን   ደብረታቦር ቀበሌ 01
50. መምህር ተስፋዬ ብርሃን   ደብረታቦር ቀበሌ 01
51. ባየሁ   ጎንደር
52. የቻፖራ ወንድም   ጎንደር
53. በለጡ መሐመድ   አዘዞ
54. እንጀራ ባዬ   አዘዞ
55. ግርማቸው ከተማ   ላይ አርማጭሆ
56. አዛናው ደሴ   አርማጭሆ
57. አራጋው መለሰ   አርማጭሆ
58. ሲሣይ ታከለ   አርማጭሆ
59. ሊሻን ከበደ   አይምባ
60. መሌ   አይምባ
61. ሰጠኝ አድማሱ   ደልጊ
62. ታረቀኝ ተሾመ   ደልጊ
63. ኖኖክ አታሎ   ደልጊ
64. ደሴ ደረሰ 53 ሻውራ
65. ግርማቸው ሞገስ   ሻውራ
66. ወርቁ   ሻውራ
67. ማማየ አራጋው   ዳንሻ
68. ፈንታ አህመድ   ዳንሻ
69. ክንፈ ቸኮል   በአከር
70. ፍሥሃ ጥላሁን 25 አዲስ አበባ
71. ቅዱስ ሀብታሙ 16 አዲስ አበባ
72. ይበልጣል ደሴ    

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃል-ኪዳን ነው!

ዐማራው ኅልውናውንና መብቱን በትግሉ ያስከብራል!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት!

ሰኞ ነሐሴ ፴ ቀን ፪ሺህ፰  ዓ.ም.                

ቅፅ ፬ ፣ ቁጥር ፳፯

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule