• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለመላው የዐማራ ልጅ የተሰጠ ማሳሰቢያ

September 5, 2016 11:33 pm by Editor Leave a Comment

ጉዳዩ፦ የመጭውን ዘመን መለወጫ (መስከረም 1 ቀን 2009 ዓ.ም.) በፈንጠዝያ ሳይሆን፤ ዕለቱን በመሪር ሐዘንና በቁጭት አስቦ ስለመዋል።

ዘረኛው የትግሬ ወያኔ አገዛዝ፣ በዐማራው ወገናችን ላይ ከፋሽስት ጣሊያን በከፋ መልኩ የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ሲፈጽም እነሆ 41ኛ ዓመቱን አገባድዶ በ42ኛው ላይ ይገኛል። በተለይም ካለፈው ሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በጎንደርና በጎጃም በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የጅምላ የጥፋት ዘመቻ አውጇል። የአገዛዙ የኅልውና መሠረት የሆነው ነፍሰ በላው የአጋዚ ሠራዊት ዕድሜና ፆታ ሳይለይ፥  ሕፃናትን፣ ወጣቶችን፣ አዛውንትን፣ ጎልማሶችን፣ ወንዶችና ሴቶችን ቤት ለቤት እያደነ እጅግ መርዘኛ በሆነ ጥይት እየደበደበ የዘር ፍጅት እያደረሰ ነው።

የትግሬ-ወያኔ በከፈተው በዚህ ዐማራን ከምድረ ገጽ የማጥፋት ዘመቻ፣ በሺህዎች የሚቆጠሩ እህት ወንድሞቻችን ተገድለዋል፤ አያሌዎች ቆስለዋል፤ በርካታዎች ታስረዋል፤  ተጫውተው ያልጠገቡ፣ ክፉ ደጉን ያልለዩ ሕፃናት በአረመኔዎቹ ወያኔዎች ተቀጥፈዋል። ልጆቻችን አድገው ከበስቋላው ሕይዎታችን ይታደጉናል ብለው ተስፋ የሰነቁ ወለጆች፣ ተስፋቸውን አጥተዋል፤ ቤተሰብ ፈርሷል። እነዚህ ወንድም እህቶቻችን ሕይዎታቸውን፣ አጥንታቸውን፣ ደማቸውን የሰጡት እና መስዋዕት የሆኑት፣ ለዐማራ የማንነት ጥያቄ ተገቢ መልስ ለማስገኘት ነው። እነርሱ ለእኛ ነፃነት ሲሉ ሞቱ፣ ተሰቃዩ። እኛስ እነርሱ የሞቱለትንና እየተሰቃዩ ላሉበት ክቡር ዓላማ፣ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? ብለን ራሳችን በመጠየቅ፣ ከትውልድና ከታሪክ ተጠያቂነት የሚያድን ተግባር ልንፈጽም ይገባል። ስለሆነም ጀግኖቹ ሰማዕታት እህት ወንድሞቻችን የሞቱለትን ዓላማ ዳር ለማድረስ፣ ዓርማቸውን አንግበን፣ በአንድነት የድሉን ቀን ለማቃረብ በጽናት ወያኔን ልንዋጋው ይገባናል።

ከሁሉም በላይ ትግሉ የሚጠየቀውን ማናቸውንም ዓይነት መስዋዕትነት ለመክፈል፣ የዐማራው ወጣት ትውልድ ራሱን በሁለንተናዊ መልኩ ማዘጋጀትና ትግሉን በቆራጥነት መቀላቀል ነገ ዛሬ የምንለው ጉዳይ አይሆንም። ማድረግ ካሉብን ድርጊቶች  መካከል በጣም በትንሹ በኑሮአችንም ሆነ በሕይዎታችን ምንም ዓይነት ኪሣራ በማያስከትሉት መጀመር ይቻላል። ስለዚህ የሚከተሉትን ተግባሮች በማከናዎን ከዚህ በታች ስማቸው በተዘረዘሩት ሰማዕታት ስም ጥሪያችን እናቀርባለን።

አንደኛ፦   በሚመጣው የዘመን መለወጫ ቀን በዓሉ ከሚጠይቀው ፈንጠዝያ፣ ሣቅና ጨዋታ ተቆጥበን፣ ዕለቱን የሐዘንና የቁጭት መግለጫ የሆነውን ጥቁር ልብስ ለብሰን የኢትዮጵያን ሠንደቅ ዓላማ እያውለበለን እንድንውል፤ ስንበላና ስንጠጣ ሰማዕታቱን በጸሎታችን እንድናስባቸው።

ሁለተኛ፦  ከኢትዮጵያ የሚመጣ እንጀራ እስከ ወዲያኛው ላለመግዛት እንወስን።

ሦስተኛ፦   በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላለመጓጓዝ እንወስን።

አራተኛ፦   ከወያኔና ከወያኔ ጋር ንክኪነት ካለቸው ድርጅቶች፣ ሆቴሎች፣ ሱቆች፣ ምግብ ቤቶች፣ ወዘተርፈ አንጠቀም።

አምስተኛ፦      የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች ከሆኑ ሰዎች ጋር የነበረንን ግንኙነት እናቋርጥ።

ስድስተኛ፦      ዐማራው መከበር የሚችለውና ወያኔን እስከ ወዲያኛው ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ሥልጣን አሽንቀጥሮ መጣል የሚችለው በማንነቱ ሲደራጅ ነውና፣ በዐማራ ስም የተደራጁ ድርጅቶችን እንደግፍ፤ እንርዳ።

ሰባተኛ፦  በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመውን ዕልቂት ለዓለም ማኅበረሰብ በስፋት ለማሣወቅ፣ በየአለንበት አካባቢ በሚዘጋጁ ልዩ ልዩ ሕዝባዊ ትዕይንቶች እንሣተፍ፣ የተማጽኖ ደብዳቤዎችን እና መልዕክቶችን ለየአገሩ ፖለቲከኞች፣ መንግሥታት እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች እናድርስ።

ሠንጠረዥ፦ ከሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በጎንደርና በጎጃም በትግሬ-ወያኔ የተጨፈጨፉ ወገኖቻችን ስም ዝርዝር

ተራ ቁጥር የተገዳይ ሙሉ ስም ዕድሜ የመኖሪያ አድራሻ
1. ዕድሜዓለም ዘውዱ 27 ባሕር ዳር
2. ገረመው አበባው 25 ባሕር ዳር
3. ተፈሪ ባዩ 16 ባሕር ዳር
4. ሰሎሞን አስቻለ 25 ባሕር ዳር
5. ሙሉቀን ተፈራ 27 ባሕር ዳር
6. አደራጀው ኃይሉ 19 ባሕር ዳር
7. አስማማው በየነ 22 ባሕር ዳር
8. ታዘበው ጫኔ 21 ባሕር ዳር
9. አሥራት ካሣሁን 24 ባሕር ዳር
10. የሽዋስ ወርቁ 20 ባሕር ዳር
11. ብርሃን አቡሃይ 29 ባሕር ዳር
12. ሽመልስ ታዬ 22 ባሕር ዳር
13. አዛናው ማሙ 20 ባሕር ዳር
14. ሢሣይ አማረ 24 ባሕር ዳር
15. ሞላልኝ አታላይ 21 ባሕር ዳር
16. እንግዳው ዘሩ 20 ባሕር ዳር
17. ዝናው ተሰማ 19 ባሕር ዳር
18. ዋለልኝ ታደሰ 24 ባሕር ዳር
19. ይታያል ካሤ 25 ባሕር ዳር
20. እሸቴ ብርቁ 37 ባሕር ዳር
21. ሞገስ 40 ባሕር ዳር
22. አደራጀው ደሣለኝ 30 ባሕር ዳር
23. ማኅሌት 23 ባሕር ዳር
24. ተስፋዬ ብርሃኑ 58 ባሕር ዳር
25. ፈንታሁን 30 ባሕር ዳር
26. ሰጠኝ ካሤ 28 ባሕር ዳር
27. ባበይ ግርማ 26 ባሕር ዳር
28. አብዮት ዘሪሁን 20 ባሕር ዳር
29. ሀብታሙ ታምራት 27 ባሕር ዳር
30. ሞገስ ሞላ 23 ባሕር ዳር
31. ታደሰ ዘመኑ 26 አዴት
32. እስቲበል አስረስ 19 አዴት
33. አበበ ገረመው 27 ጢስ ዐባይ
34. ይበልጣል ዕውነቱ 24 ጢስ ዐባይ
35. ሰሎሞን ጥበቡ 30 ቻግኒ
36. በረከት ዓለማየሁ 28 ዳንግላ
37. ያየህ በላቸው 30 ዳንግላ
38. ዓለማየሁ ይበልጣል 27 ዳንግላ
39. ሽመልስ ወንድሙ 28 ቡሬ
40. አለበል ዓይናለም 28 ደብረማርቆስ
41. ስሙ ገና የሚጣራ ደካማ እናት ያሉት   ደብረ ማርቆስ ቀበሌ 03
42. ዓይንአዲስ ለዓለም 24 ደብረወርቅ
43. አበጀ ተዘራ 28 ወረታ
44. ደመቀ ዘለቀ 22 ወረታ
45. አለበል ሃይማኖት 24 ወረታ
46. መሣፍንት አማራ 22 እስቴ
47. በለጠ ካሤ 32 ደብረታቦር
48. ይህነው ሽመልስ 30 ደብረታቦር
49.  ማዕረግ ብርሃን   ደብረታቦር ቀበሌ 01
50. መምህር ተስፋዬ ብርሃን   ደብረታቦር ቀበሌ 01
51. ባየሁ   ጎንደር
52. የቻፖራ ወንድም   ጎንደር
53. በለጡ መሐመድ   አዘዞ
54. እንጀራ ባዬ   አዘዞ
55. ግርማቸው ከተማ   ላይ አርማጭሆ
56. አዛናው ደሴ   አርማጭሆ
57. አራጋው መለሰ   አርማጭሆ
58. ሲሣይ ታከለ   አርማጭሆ
59. ሊሻን ከበደ   አይምባ
60. መሌ   አይምባ
61. ሰጠኝ አድማሱ   ደልጊ
62. ታረቀኝ ተሾመ   ደልጊ
63. ኖኖክ አታሎ   ደልጊ
64. ደሴ ደረሰ 53 ሻውራ
65. ግርማቸው ሞገስ   ሻውራ
66. ወርቁ   ሻውራ
67. ማማየ አራጋው   ዳንሻ
68. ፈንታ አህመድ   ዳንሻ
69. ክንፈ ቸኮል   በአከር
70. ፍሥሃ ጥላሁን 25 አዲስ አበባ
71. ቅዱስ ሀብታሙ 16 አዲስ አበባ
72. ይበልጣል ደሴ    

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃል-ኪዳን ነው!

ዐማራው ኅልውናውንና መብቱን በትግሉ ያስከብራል!

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት!

ሰኞ ነሐሴ ፴ ቀን ፪ሺህ፰  ዓ.ም.                

ቅፅ ፬ ፣ ቁጥር ፳፯

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule