• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“HILLARY WINS” መስፍን በዙ

November 10, 2016 10:23 pm by Editor 2 Comments

* የጅብ ችኩል …

መቸም ይህ የአሜሪካ ምርጫ ከቅስቀሳው እስከ ትራምፕ ምርጫ ትዝታው ብዙ ነው፣ በመጨረሻው ቀንና በምርጫው ውጤት ቀን የሆንነው ግን በጣም ያጓጓና ልዩ ትዝታ ይዞ ያለፈ አጋጣሚ ነው፣ ለብዙዎቻችን … የማልረሳውን የእኔን ትዝታ ከትዝብት ጋር ላጋራችሁ …

“እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!” የሚል መርህን ይዘው ከሚንቀሳቀሱት የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ “HILLARY WINS” “ሄለሪ አሸነፈች!” የሚል አንድ አስገራሚ ሰበር መረጃ ከሌሊት 3:34 Am ተሰራጭቶ ደረሰኝ።

HILLARY WINS ከሚለው መረጃ ስር “ቲጂ ቴሌቪዥን ጠዋት ላይ የምርጫ ጣቢያዎቹን ጎብኝቶ ባገኘው መረጃ መሰረት ሄለሪ የአሜሪካ 45ኛ ፕሬዚደንት ሆነው ተመርጠዋል” በሚል የሚያትተው መረጃ አስገራሚ ነበር፣ መረጃው ለሄለሪ ደጋፊ ደስታ፣ ለትራምፕ ደጋፊ ሀዘንም ነበር … መልዕክቱ እንደወረደ እንዲህ ነበር የሚለው:

TG Ethiopian Television did visit some polling stations this morning. Based on what the voters said, TG Ethiopian Television declares that Hillary Clinton will be the 45th President of the United States …  ከጉጉቴ የተነሳ ደስታዬ ወሰን አጣና በሰፊው በመገናኛ ብዙሃን ማልጀ እስክሰማው የአቶ መስፍን መረጃ ነፍስ ዘርቶብኝ እረፍት ማድረጉን መረጥኩ …!

እረፍት አይሉት እረፍት አድርጌ የእንጀራ ነገር ሆኖብኝ ወደ ስራ ልሰማራ ረዥሙን መንገድ ስጀምር ግን “እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!” የሚል መርህን ይዞ ከሚንቀሳቀሰው የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ “HILLARY WINS”  “ሄለሪ አሸነፈች” መረጃ “በሬ ወለደ” መሆኑን ተረዳሁ! አዘንኩ፣ ቢያንስ ጭብጥ ሳይያዝ ለምን መረጃ ይሰራጫል? ችኮላው ባላስፈለገ ብዬ ጋዜጠኛውን ሳማርራቸው አጅሬ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ ከወደ ምሽት ላይ ማስተባበያ አሰራጭተዋል፣ በተሰራጨው ማስተባበያም “የተሰራጨውን መረጃ እኔ በማላውቀው መንገድ፣ ከፍቃዴ ውጭ የተሰራጨ ነው!” ብለው ይቅርታ ጠይቀዋል …

It is true that when we talked to the voters in Virginia, most of them said that they voted for Hillary Clinton. Since we only talked to Virginia voters, please disregard the previous email. It was sent without my approval.

Thank you
Mesfin Bezu

ያለጭብጥ መረጃ የጅብ ችኩል እየተኮነ “እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!” ቢሉት ፋይዳ የለውም! ከመረጃ ቅበላው እሽቅድድም ለመረጃው ተአማኒነት ቅድሚያ መስጠት እንደሚገባ የአቶ መስፍን በዙ ስህተት ካስተማረን መልካም ይመስለኛል!

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 1 ቀን 2009 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. tesfai habte says

    November 11, 2016 02:41 pm at 2:41 pm

    ወያኔዎች ምን ሃሳብ ነበራቸው ይመስላል መሰለኝ!—-ሄለሪ ክሊንተን ወደ ስልጣን ከመጣ፡ የኢትዮጵያ ሰው የማሰር፡ የመጨፍጨፍ፡ ብሱማል እና ሱዳን ጦርነቶች ሽብር ፈጥረህ ዶላር ለማግኘት፡ ግደል፡ እሰር፡ ሽብር ከፈጠርክህ የግሪን ካርድ ስጦጣ ከአመሪካ ለመቀበል ተስፋቸው ሰማይ ላይ ደርሶ ነበር። ግን ሁሉ ነገር እንደ ታሰበ ሳይሆን እንዳለው ነው። በተስፋ ሁሉ ግዜ ኣይኖርም። አምላክ ሰርተህ ብላ እንጂ ዋሽተህ፡ ገድለ፡ ሰርቀህ፡ ብላ ያለው ሰው የለም። ኲናት ናፋቂው ወያኔ እና አንዳ አንድ ብዶላር የተገዙ የኢትዮጵያ ሰዎች ግን ዛሬ በትራምፕ መድሃኒት ሕመሙ ይዘልቃ መስሎ ይተየኛል!—-ትራምፕ ስራ እንጂ የመግደል አዝማምየ ያለው አይመስልም!—ለመሆኑ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ስንት ግዜ ሰውን እየገደሉ፡ እያጋደሉ ለመኖር ይፈልጋሉ?—-ሰዎች እንደ ትራምፕ ዓይነት ይበቃናል የማለት ፍሎጎታቸው በመለጽ ናቸው። ጦርነት የክፉ ሰው ውጤት ነው።

    Reply
  2. Ethiopian says

    November 20, 2016 06:33 am at 6:33 am

    The sad part of this story is that the writer’s choice to tune to TG TV for reliable information.Really are you actually living on this planet ? TG TV for reliable source of news.. You got to be kidding

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule