• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“HILLARY WINS” መስፍን በዙ

November 10, 2016 10:23 pm by Editor 2 Comments

* የጅብ ችኩል …

መቸም ይህ የአሜሪካ ምርጫ ከቅስቀሳው እስከ ትራምፕ ምርጫ ትዝታው ብዙ ነው፣ በመጨረሻው ቀንና በምርጫው ውጤት ቀን የሆንነው ግን በጣም ያጓጓና ልዩ ትዝታ ይዞ ያለፈ አጋጣሚ ነው፣ ለብዙዎቻችን … የማልረሳውን የእኔን ትዝታ ከትዝብት ጋር ላጋራችሁ …

“እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!” የሚል መርህን ይዘው ከሚንቀሳቀሱት የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ “HILLARY WINS” “ሄለሪ አሸነፈች!” የሚል አንድ አስገራሚ ሰበር መረጃ ከሌሊት 3:34 Am ተሰራጭቶ ደረሰኝ።

HILLARY WINS ከሚለው መረጃ ስር “ቲጂ ቴሌቪዥን ጠዋት ላይ የምርጫ ጣቢያዎቹን ጎብኝቶ ባገኘው መረጃ መሰረት ሄለሪ የአሜሪካ 45ኛ ፕሬዚደንት ሆነው ተመርጠዋል” በሚል የሚያትተው መረጃ አስገራሚ ነበር፣ መረጃው ለሄለሪ ደጋፊ ደስታ፣ ለትራምፕ ደጋፊ ሀዘንም ነበር … መልዕክቱ እንደወረደ እንዲህ ነበር የሚለው:

TG Ethiopian Television did visit some polling stations this morning. Based on what the voters said, TG Ethiopian Television declares that Hillary Clinton will be the 45th President of the United States …  ከጉጉቴ የተነሳ ደስታዬ ወሰን አጣና በሰፊው በመገናኛ ብዙሃን ማልጀ እስክሰማው የአቶ መስፍን መረጃ ነፍስ ዘርቶብኝ እረፍት ማድረጉን መረጥኩ …!

እረፍት አይሉት እረፍት አድርጌ የእንጀራ ነገር ሆኖብኝ ወደ ስራ ልሰማራ ረዥሙን መንገድ ስጀምር ግን “እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!” የሚል መርህን ይዞ ከሚንቀሳቀሰው የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ “HILLARY WINS”  “ሄለሪ አሸነፈች” መረጃ “በሬ ወለደ” መሆኑን ተረዳሁ! አዘንኩ፣ ቢያንስ ጭብጥ ሳይያዝ ለምን መረጃ ይሰራጫል? ችኮላው ባላስፈለገ ብዬ ጋዜጠኛውን ሳማርራቸው አጅሬ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ ከወደ ምሽት ላይ ማስተባበያ አሰራጭተዋል፣ በተሰራጨው ማስተባበያም “የተሰራጨውን መረጃ እኔ በማላውቀው መንገድ፣ ከፍቃዴ ውጭ የተሰራጨ ነው!” ብለው ይቅርታ ጠይቀዋል …

It is true that when we talked to the voters in Virginia, most of them said that they voted for Hillary Clinton. Since we only talked to Virginia voters, please disregard the previous email. It was sent without my approval.

Thank you
Mesfin Bezu

ያለጭብጥ መረጃ የጅብ ችኩል እየተኮነ “እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!” ቢሉት ፋይዳ የለውም! ከመረጃ ቅበላው እሽቅድድም ለመረጃው ተአማኒነት ቅድሚያ መስጠት እንደሚገባ የአቶ መስፍን በዙ ስህተት ካስተማረን መልካም ይመስለኛል!

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 1 ቀን 2009 ዓም


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. tesfai habte says

    November 11, 2016 02:41 pm at 2:41 pm

    ወያኔዎች ምን ሃሳብ ነበራቸው ይመስላል መሰለኝ!—-ሄለሪ ክሊንተን ወደ ስልጣን ከመጣ፡ የኢትዮጵያ ሰው የማሰር፡ የመጨፍጨፍ፡ ብሱማል እና ሱዳን ጦርነቶች ሽብር ፈጥረህ ዶላር ለማግኘት፡ ግደል፡ እሰር፡ ሽብር ከፈጠርክህ የግሪን ካርድ ስጦጣ ከአመሪካ ለመቀበል ተስፋቸው ሰማይ ላይ ደርሶ ነበር። ግን ሁሉ ነገር እንደ ታሰበ ሳይሆን እንዳለው ነው። በተስፋ ሁሉ ግዜ ኣይኖርም። አምላክ ሰርተህ ብላ እንጂ ዋሽተህ፡ ገድለ፡ ሰርቀህ፡ ብላ ያለው ሰው የለም። ኲናት ናፋቂው ወያኔ እና አንዳ አንድ ብዶላር የተገዙ የኢትዮጵያ ሰዎች ግን ዛሬ በትራምፕ መድሃኒት ሕመሙ ይዘልቃ መስሎ ይተየኛል!—-ትራምፕ ስራ እንጂ የመግደል አዝማምየ ያለው አይመስልም!—ለመሆኑ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ስንት ግዜ ሰውን እየገደሉ፡ እያጋደሉ ለመኖር ይፈልጋሉ?—-ሰዎች እንደ ትራምፕ ዓይነት ይበቃናል የማለት ፍሎጎታቸው በመለጽ ናቸው። ጦርነት የክፉ ሰው ውጤት ነው።

    Reply
  2. Ethiopian says

    November 20, 2016 06:33 am at 6:33 am

    The sad part of this story is that the writer’s choice to tune to TG TV for reliable information.Really are you actually living on this planet ? TG TV for reliable source of news.. You got to be kidding

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule