• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በብላቴናው ላይ የዘገየው ፍትህ!

June 12, 2015 08:40 am by Editor Leave a Comment

* የእናት 9 ዓመት ሰሚ ያጣ ጩኸት

የ4 ዓመት ደልዳላ እያለ ድክ ድክ እያለ ሮጦ ለቀላል ህክምና ከጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት አፍንጫ ስር በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ገባ። ብዙም ሳይቆይ ከሰመመን መንቃት አልችል አለ፣ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከሰመመን አልነቃም፣ በሃኪሞች ስህተት ብላቴናው መሀመድ ህይዎቱ ተሰናክሎ ላለፉት 9 ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሆነል። ትናንትም ሆነ ከትናንት በስቲያም መሀመድና ቤተሰቦቹ ፍትህ ርትዕ ያገኙ ዘንድ ደጋግሜ ጠይቄያለሁ፣ ዛሬም እጠይቃለሁ! ላለፉት በዘጠኝ አመታት ከጅዳ ቆንስል ኃላፊዎች ጀምሮ ሳይኖር “አለሁ” እስከሚለን  የሴቶች ማህበር ተወካዮች ፍትህን ለመሀመድ ያስገኙ ዘንድ ተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቦ ፍትህ ማስገኘት ገዷቸዋል፣ ተበዳዮች ፍትህ  ርቋቸዋል. . .!

ክልትሙ ተንከባሎ ዛሬ ላይ ሲደርስ . . .

ታሪኩን ከመሀመድ እናት ቃል በቃል ስሙት፣ ከዚህ ሁሉ አመት በኋላ የብላቴናው መሀመድ አብድልአዚዝ ቤተሰቦች ደጋግመው ያደረጉት ውትወታ በቀደም የጅዳ ቆንስል ኃላፊዎች ተቀባይነት አግኝቶ አያውቅም።  ለአዲሱ አምባሳደር የቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት አገኘና በጉዳዩ ላይ ክትትል መጀመሩን ተመለከትን።

ቆንስል መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን በያዘው ማግስት ደግሞ ለ9 ዓመት የዋለለው የፍትህ ጥያቄ መልስ አገኘ! አዎ …  በአሳር በመከራ ለመሃመድ ቤተሰቦች ያለማሰለስ ባደረጉት ጉትጎታ 2.5 ሚሊዮን የሳውዲ ሪያል ካሳ እንደሚሰጥ በሳውዲ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር አንድ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ ተላለፈ። ውሳኔው ባይከፋም ለሰዓታት ከመተንፈሻ መሳሪያ ውጭ መንቀሳቀስ የማይችለው ብላቴና ቤተሰቦች የተወሰነውን ካሳ ተቀብለው ከሀኪም ቤቱ እንዲለቁ የተላለፈውን ፍርደ ገምድል የወላጅ ቤተሰቦች ተቃወሙት! በውሳኔ አሰጣጡ ሂደት የተገኙት የጅዳ ቆንስል ተወካይም የወላጆችን ውሳኔ በመደገፍ የውሳኔውን ፍትሃዊ አለመሆን ሳይቀበሉ ቀረ! ውሳኔ ያሳለፈው ኮሚቴ በህክምና ስህተት መሀመድ በደል የደረሰበት መሆኑን የሚያረጋግጠው ሰነድና ሙሉ ውሳኔ በአስር ቀናት ውስጥ ለወላጅና ለቆንስል መስሪያ ቤቱ እንደሚሰጥ፣ አስፈላጊ ነው ካሉ  ወደ ፍርድ ቤት መውሰድ እንደሚቻል  ተገልጾ ጉዳዩ በተያዘው ቀጠሮ ተዘጋ … ይህ የሆነው ከወራት በፊት ነበር!

ህግ አስከባሪ የማጣት እንቆቅልሽ!

ዛሬስ?  ዛሬ የተገባው ቃል የማይጨበጥ፣ የማይዳሰስ ጉም ሆኗል፣ ቆንስል መስሪያ ቤቱ በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኩል አቀርብኩት ያለው አቤቱታ መልስ አላገኘም፣ ወላጆች ላፍታ ከመድሃኒትና ከህክምና ውጭ መቆየት የማይችለውን መሀመድን ይዘው እንዲዎጡ እየተወተወቱ ነው! እናት ልጃቸውን በቅርብ እንዲያስታምሙ ከተሰጣቸው ማደሪያ በኃይል እንዲለቁ ተገደዋል፣ መጠለያውን በጸጥታ አስከባሪዎች እንዲለቁ ሲደረግ ለቆንስል መስሪያ ቤቱ  ቢያመለክቱም መጠለያውን ከመልቀቅ አልታደጓቸውም! የሳውዲ መንግስት የጤና ጥበቃ መስሪያ ቤት አጣሪ ቡድን  ያረጋገጡት ግፍ ተፈጽሞ የመሀመድ ቤተሰቦች በተለይም ብርቱዋ እናት  ዛሬም ድረሱልኝ እያሉ ነው! ቆንስል መስሪያ ቤቱም፣ የተላለፈውን የውሳኔ ሰነድ ተረክቦ ጉዳዩን ወደ ፍትህ አካላት ማቅረብ ተስኖታል! የጎደለባቸው ፍትህ እንዲሰፍን ዛሬም ተገፊዋ ይጮሃሉ … “ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም!” የሆነበት እንቆቅልሽ ግን አልገባን ብሏል!mo

እንኳንስ ይህም መሰል ግፍ ተሰርቶ በአደባባይ ተፈጽሞባቸው፣ በከባድ የሳውዲ መንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች የተፈጸመ የህግ ጥሰት የሚሸፋፍን የህግ ስርአት ሳላለመኖሩ ብዙ መረጃ ማቅረብ ይቻላል።  የቀደመውን ትተን ዛሬ የወጣውን የሳውዲ ጋዜጥ ብንመለከት ያን ሰሞን በሳውዲ አየር መንገድ ተጓዠ የነበሩ ሁለት ታዳጊዎችን ደፍረው የተመሰከረባቸው ሁለት የአየር መንገዱ የጸጥታ ሰራተኞች የአራት አመት እስራትና 1000 ጅራፍ ተፈርዶባቸዋል! የእኛ ብላቴና መሀመድ ስቃይና የወላጆቹ አቤቱታ ጉዳይ ግን ጠያቂ አጧቷልና ህግ ፊት እንኳ የሚያቀርበው ጠፍቷል! ስለሆነም የዜጎች መብት የሚያገባቸው አካላት የት አሉ? ብለን እንጠይቅ ዘንድ እንገደዳለን!

ስለ ጎደለብን ፍትህ መከበር  እንናገር!

ለሰብዕናና ለፍትህ ቀናኢ አይደለንም፣ በሳውዲ አረቢያ የከተመው ነዋሪ ከኮሚኒቲ አባልነት ሸሸቷል፣ የጅዳና የሪያድ ኮሚኒቲዎች የአባላት ድርቅ የመመታታቸው ሚስጥር ተአማኒነት ማጣት እንጅ “ቡዳ” በልቷቸው አይደለም፣ ባሳለፍናቸው በርካታ አመታት ተወካዬዮቻችን ማህበራት ምስረታ አድርተው ትልቁን ኮሚኒቲ  አኮላሸተውታል፣ እናም እላችኋለሁ፣ ለሰው መብት መቆምን ፈነጋግላችሁ የልማት ማህበራት እንደ እንጉይ የመፈልፈሉ የመጠመዳችሁን አደጋ ዛሬም በውል ያልታያችሁ ጉዳይ ፈጻሚ የመንግስት አካልት አካሄዳችሁን ልትገመግሙ ግድ ይላል። ከምንም በላይ ዘንድሮ በተሃድሶ ላይ ነው የምንለው ቆንስል መስሪያ ቤት መመሪያ ወርዶ እያስፈጸመ ቢሆንም መልሶ ከዳጡ ወደ ማጡ እንዳይወድቅ እሰጋለሁ! ለተገፊው መሀመድ ፍትህ ማግኘት ሁላችን ልንተጋ ግድ ይለናል፣ ቢያንስ ጉዳዩን ወደ ፍትህ አካል ይቀርብ ዘንድ ሁላችንም የቻልነውን ከማድረግ ጎን ለጎን መሀመድን በጸሎት እናስበው!

ተወካዮቻችን የግፉአንን እንባ በመጥረጉና መብትታቸውን በማስከበሩ ሰናይ ምግባር ቆመው አለማየታችን የምስኪኗ የመሀመድ አብድልአዚዝ እናት እንባ የሚነግረን እውነታ አይጠፋም! “ስለ እውነት እንመስክርና የመጣው ይምጣ!” ማለትን ለደፈረ ባለፉት በርካታ አመታት በዋነኛነት የዜጎች መብት የቆሙት ተወካዮቻችንም ሆነ የሚያደራጇቸው ማህበራት  ድግስ እየደገሱ በስሙ ገንዘብ ከመሰብሰብ ያለፈ ስራ ሰሩ ቢባል ለህዳሴውን ግድብ አደረጉ የሚባለውን ድጋድ ብቻ ነው የምናገኘው! ለሀገር ግንባታ፣ ለልማትና ድንበሩ ተደፈረ ሲባል ለሀገሩ ቀናኢነት የሚያሳየው ዜጋ ፍትህ እጦት ግን ዛሬም ተዘንግቷል . . .! ይህ በጣሙን የሚያም፣ ሲነገሩት እንኳ መስዋዕትነትን የሚያስለፍል እውነታ ቢሆንም ነግ በኔ ነውና እኔ የምፈራው መከፈል ያለበት መስዋዕትነት የለም!

በእሱ ስራ አንገባም፣ የዘገየው ፍትህ ይሰፍን ዘንድ ለፈጣሪ አቤት እንላለን፣ መልስም እናገኛለን! ምድራዊ ነንና የተወካዮቻችን ጀሮ የጠፊዎችን ድምጽ ይሰማ ዘንድ ከመማለዱ ጎን እንደ ፍጡር የፍትህ ማስከበር ጥሪያችን ትሰሙ ዘንድ እንማለዳችኋለን!

የየራስ ፍርዳችሁን ስጡ፣ እኔ እንዳገባኝ እናንተም ያገባኛል ካላችሁ፣ የማቀርበውን ጭብጥ መረጃ፣ ስለ ሰብአዊ መብት መከበርና ስለ ፍትህ መረጃውን እየተቀባበላችሁ ጩኹት… የተነፈግነውን ፍትህ ማግኘት እስክንችል የእናት ፍቅርን የምታውቁትም ሆነ የማታውቁ፣ የእናት አንጀትን መላወስ ህመም ጠልቆ የሚሰማችሁትም ሆነ ስሜቱን የማይገባችሁ፣ የምትወዱትን ነገር በግፍ ስለመነጠቃችሁ እያሰባችሁ ስለ መሀመድና ስለ ግፉአን ቤተሰቡ ፍትህ ማግኘት አቤት ትሉ ዘንድ አደራ እላችኃለሁ. . .!

በሳውዲ መንግስት ጤና ጥበቃ ሚኒስትር አጣሪ ኮሚቴ በህክምና መሰናከሉ የተረጋገጠው የብላቴናው  ጉዳት ዛሬ ላይ ሲደርስ ፍትህ እጦቱ አንገሽግሾናል፣ ብላቴናውና ቤተሰቦቹ ፍትህ ይሻሉ፣ እኛ የወገናችን ጉዳይ ያገባናልና ፍትህ፣ እንሻለን፣ ፍትህ ናፍቆናል! ጉዳዩን ወደ ፍትህ አቅርቡልን!

ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ
ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓም

(ሙሉ የመሀመድን እናት ቪዲዮ ከፊስ ቡክ ገጼ ማግኘት ትችላላችሁ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule