• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በብላቴናው ላይ የዘገየው ፍትህ!

June 12, 2015 08:40 am by Editor Leave a Comment

* የእናት 9 ዓመት ሰሚ ያጣ ጩኸት

የ4 ዓመት ደልዳላ እያለ ድክ ድክ እያለ ሮጦ ለቀላል ህክምና ከጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት አፍንጫ ስር በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ገባ። ብዙም ሳይቆይ ከሰመመን መንቃት አልችል አለ፣ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከሰመመን አልነቃም፣ በሃኪሞች ስህተት ብላቴናው መሀመድ ህይዎቱ ተሰናክሎ ላለፉት 9 ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሆነል። ትናንትም ሆነ ከትናንት በስቲያም መሀመድና ቤተሰቦቹ ፍትህ ርትዕ ያገኙ ዘንድ ደጋግሜ ጠይቄያለሁ፣ ዛሬም እጠይቃለሁ! ላለፉት በዘጠኝ አመታት ከጅዳ ቆንስል ኃላፊዎች ጀምሮ ሳይኖር “አለሁ” እስከሚለን  የሴቶች ማህበር ተወካዮች ፍትህን ለመሀመድ ያስገኙ ዘንድ ተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቦ ፍትህ ማስገኘት ገዷቸዋል፣ ተበዳዮች ፍትህ  ርቋቸዋል. . .!

ክልትሙ ተንከባሎ ዛሬ ላይ ሲደርስ . . .

ታሪኩን ከመሀመድ እናት ቃል በቃል ስሙት፣ ከዚህ ሁሉ አመት በኋላ የብላቴናው መሀመድ አብድልአዚዝ ቤተሰቦች ደጋግመው ያደረጉት ውትወታ በቀደም የጅዳ ቆንስል ኃላፊዎች ተቀባይነት አግኝቶ አያውቅም።  ለአዲሱ አምባሳደር የቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት አገኘና በጉዳዩ ላይ ክትትል መጀመሩን ተመለከትን።

ቆንስል መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን በያዘው ማግስት ደግሞ ለ9 ዓመት የዋለለው የፍትህ ጥያቄ መልስ አገኘ! አዎ …  በአሳር በመከራ ለመሃመድ ቤተሰቦች ያለማሰለስ ባደረጉት ጉትጎታ 2.5 ሚሊዮን የሳውዲ ሪያል ካሳ እንደሚሰጥ በሳውዲ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር አንድ አጣሪ ኮሚቴ ውሳኔ ተላለፈ። ውሳኔው ባይከፋም ለሰዓታት ከመተንፈሻ መሳሪያ ውጭ መንቀሳቀስ የማይችለው ብላቴና ቤተሰቦች የተወሰነውን ካሳ ተቀብለው ከሀኪም ቤቱ እንዲለቁ የተላለፈውን ፍርደ ገምድል የወላጅ ቤተሰቦች ተቃወሙት! በውሳኔ አሰጣጡ ሂደት የተገኙት የጅዳ ቆንስል ተወካይም የወላጆችን ውሳኔ በመደገፍ የውሳኔውን ፍትሃዊ አለመሆን ሳይቀበሉ ቀረ! ውሳኔ ያሳለፈው ኮሚቴ በህክምና ስህተት መሀመድ በደል የደረሰበት መሆኑን የሚያረጋግጠው ሰነድና ሙሉ ውሳኔ በአስር ቀናት ውስጥ ለወላጅና ለቆንስል መስሪያ ቤቱ እንደሚሰጥ፣ አስፈላጊ ነው ካሉ  ወደ ፍርድ ቤት መውሰድ እንደሚቻል  ተገልጾ ጉዳዩ በተያዘው ቀጠሮ ተዘጋ … ይህ የሆነው ከወራት በፊት ነበር!

ህግ አስከባሪ የማጣት እንቆቅልሽ!

ዛሬስ?  ዛሬ የተገባው ቃል የማይጨበጥ፣ የማይዳሰስ ጉም ሆኗል፣ ቆንስል መስሪያ ቤቱ በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኩል አቀርብኩት ያለው አቤቱታ መልስ አላገኘም፣ ወላጆች ላፍታ ከመድሃኒትና ከህክምና ውጭ መቆየት የማይችለውን መሀመድን ይዘው እንዲዎጡ እየተወተወቱ ነው! እናት ልጃቸውን በቅርብ እንዲያስታምሙ ከተሰጣቸው ማደሪያ በኃይል እንዲለቁ ተገደዋል፣ መጠለያውን በጸጥታ አስከባሪዎች እንዲለቁ ሲደረግ ለቆንስል መስሪያ ቤቱ  ቢያመለክቱም መጠለያውን ከመልቀቅ አልታደጓቸውም! የሳውዲ መንግስት የጤና ጥበቃ መስሪያ ቤት አጣሪ ቡድን  ያረጋገጡት ግፍ ተፈጽሞ የመሀመድ ቤተሰቦች በተለይም ብርቱዋ እናት  ዛሬም ድረሱልኝ እያሉ ነው! ቆንስል መስሪያ ቤቱም፣ የተላለፈውን የውሳኔ ሰነድ ተረክቦ ጉዳዩን ወደ ፍትህ አካላት ማቅረብ ተስኖታል! የጎደለባቸው ፍትህ እንዲሰፍን ዛሬም ተገፊዋ ይጮሃሉ … “ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም!” የሆነበት እንቆቅልሽ ግን አልገባን ብሏል!mo

እንኳንስ ይህም መሰል ግፍ ተሰርቶ በአደባባይ ተፈጽሞባቸው፣ በከባድ የሳውዲ መንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች የተፈጸመ የህግ ጥሰት የሚሸፋፍን የህግ ስርአት ሳላለመኖሩ ብዙ መረጃ ማቅረብ ይቻላል።  የቀደመውን ትተን ዛሬ የወጣውን የሳውዲ ጋዜጥ ብንመለከት ያን ሰሞን በሳውዲ አየር መንገድ ተጓዠ የነበሩ ሁለት ታዳጊዎችን ደፍረው የተመሰከረባቸው ሁለት የአየር መንገዱ የጸጥታ ሰራተኞች የአራት አመት እስራትና 1000 ጅራፍ ተፈርዶባቸዋል! የእኛ ብላቴና መሀመድ ስቃይና የወላጆቹ አቤቱታ ጉዳይ ግን ጠያቂ አጧቷልና ህግ ፊት እንኳ የሚያቀርበው ጠፍቷል! ስለሆነም የዜጎች መብት የሚያገባቸው አካላት የት አሉ? ብለን እንጠይቅ ዘንድ እንገደዳለን!

ስለ ጎደለብን ፍትህ መከበር  እንናገር!

ለሰብዕናና ለፍትህ ቀናኢ አይደለንም፣ በሳውዲ አረቢያ የከተመው ነዋሪ ከኮሚኒቲ አባልነት ሸሸቷል፣ የጅዳና የሪያድ ኮሚኒቲዎች የአባላት ድርቅ የመመታታቸው ሚስጥር ተአማኒነት ማጣት እንጅ “ቡዳ” በልቷቸው አይደለም፣ ባሳለፍናቸው በርካታ አመታት ተወካዬዮቻችን ማህበራት ምስረታ አድርተው ትልቁን ኮሚኒቲ  አኮላሸተውታል፣ እናም እላችኋለሁ፣ ለሰው መብት መቆምን ፈነጋግላችሁ የልማት ማህበራት እንደ እንጉይ የመፈልፈሉ የመጠመዳችሁን አደጋ ዛሬም በውል ያልታያችሁ ጉዳይ ፈጻሚ የመንግስት አካልት አካሄዳችሁን ልትገመግሙ ግድ ይላል። ከምንም በላይ ዘንድሮ በተሃድሶ ላይ ነው የምንለው ቆንስል መስሪያ ቤት መመሪያ ወርዶ እያስፈጸመ ቢሆንም መልሶ ከዳጡ ወደ ማጡ እንዳይወድቅ እሰጋለሁ! ለተገፊው መሀመድ ፍትህ ማግኘት ሁላችን ልንተጋ ግድ ይለናል፣ ቢያንስ ጉዳዩን ወደ ፍትህ አካል ይቀርብ ዘንድ ሁላችንም የቻልነውን ከማድረግ ጎን ለጎን መሀመድን በጸሎት እናስበው!

ተወካዮቻችን የግፉአንን እንባ በመጥረጉና መብትታቸውን በማስከበሩ ሰናይ ምግባር ቆመው አለማየታችን የምስኪኗ የመሀመድ አብድልአዚዝ እናት እንባ የሚነግረን እውነታ አይጠፋም! “ስለ እውነት እንመስክርና የመጣው ይምጣ!” ማለትን ለደፈረ ባለፉት በርካታ አመታት በዋነኛነት የዜጎች መብት የቆሙት ተወካዮቻችንም ሆነ የሚያደራጇቸው ማህበራት  ድግስ እየደገሱ በስሙ ገንዘብ ከመሰብሰብ ያለፈ ስራ ሰሩ ቢባል ለህዳሴውን ግድብ አደረጉ የሚባለውን ድጋድ ብቻ ነው የምናገኘው! ለሀገር ግንባታ፣ ለልማትና ድንበሩ ተደፈረ ሲባል ለሀገሩ ቀናኢነት የሚያሳየው ዜጋ ፍትህ እጦት ግን ዛሬም ተዘንግቷል . . .! ይህ በጣሙን የሚያም፣ ሲነገሩት እንኳ መስዋዕትነትን የሚያስለፍል እውነታ ቢሆንም ነግ በኔ ነውና እኔ የምፈራው መከፈል ያለበት መስዋዕትነት የለም!

በእሱ ስራ አንገባም፣ የዘገየው ፍትህ ይሰፍን ዘንድ ለፈጣሪ አቤት እንላለን፣ መልስም እናገኛለን! ምድራዊ ነንና የተወካዮቻችን ጀሮ የጠፊዎችን ድምጽ ይሰማ ዘንድ ከመማለዱ ጎን እንደ ፍጡር የፍትህ ማስከበር ጥሪያችን ትሰሙ ዘንድ እንማለዳችኋለን!

የየራስ ፍርዳችሁን ስጡ፣ እኔ እንዳገባኝ እናንተም ያገባኛል ካላችሁ፣ የማቀርበውን ጭብጥ መረጃ፣ ስለ ሰብአዊ መብት መከበርና ስለ ፍትህ መረጃውን እየተቀባበላችሁ ጩኹት… የተነፈግነውን ፍትህ ማግኘት እስክንችል የእናት ፍቅርን የምታውቁትም ሆነ የማታውቁ፣ የእናት አንጀትን መላወስ ህመም ጠልቆ የሚሰማችሁትም ሆነ ስሜቱን የማይገባችሁ፣ የምትወዱትን ነገር በግፍ ስለመነጠቃችሁ እያሰባችሁ ስለ መሀመድና ስለ ግፉአን ቤተሰቡ ፍትህ ማግኘት አቤት ትሉ ዘንድ አደራ እላችኃለሁ. . .!

በሳውዲ መንግስት ጤና ጥበቃ ሚኒስትር አጣሪ ኮሚቴ በህክምና መሰናከሉ የተረጋገጠው የብላቴናው  ጉዳት ዛሬ ላይ ሲደርስ ፍትህ እጦቱ አንገሽግሾናል፣ ብላቴናውና ቤተሰቦቹ ፍትህ ይሻሉ፣ እኛ የወገናችን ጉዳይ ያገባናልና ፍትህ፣ እንሻለን፣ ፍትህ ናፍቆናል! ጉዳዩን ወደ ፍትህ አቅርቡልን!

ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ
ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓም

(ሙሉ የመሀመድን እናት ቪዲዮ ከፊስ ቡክ ገጼ ማግኘት ትችላላችሁ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule