• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዞን 9ኞችን አደግፋለሁ!

May 7, 2014 05:33 am by Editor Leave a Comment

ዞን 9ኞችን አከብራቸዋለሁ ፣ እዎዳቸዋለሁ! “የሃገር የህዝባችን ጉዳይ ያገባናል!” በሚል በፖለቲካ ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ህይዎታችን ዙሪያ የሚያቀርቧቸው መጣጥፎች አስተማሪ ለመሆናቸው እማኝ ነኝ! ጦማርያኑ ቀፍድዶ ከያዘን ፍርሃት ወጥተን ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ለመብታችን እንድንተጋ ማነቃቃታቸው ቢያስመሰግን እንጅ የሚያስኮንን፣ የሚያስወግዝ፣ ብሎም ወህኒ የሚያስወርድ ነው አልልም።

ዞን 9 ኞችን የምንወድ የምንደግፍ  እኔና እኔን መሰሎች ጥቂቶች አይደለንም። እልፍ አእላፎች ነን። ቢያንስ እኔ በግል የወጣት ጦማርያኑ እንግልትና ጉዳት የሃገር  ጉዳት ነው ብየ አምናለሁ። እልፍ  አእላፎች ጦማሪዎች “ህገ መንግስቱን አልጣሱም ” ስንል ” ህገ መንግስቱ ይከበር ፣ ዞን 9ኞች ይፈቱ !” ዘንድ ድምጻችን ከፍ አድርገን እናሰማለን!

የዞን 9 ጦማርያን የመጻፍ የመናገር መብታቸውን ተጠቅመው ተደራጅተው በሰለጠነና በዘመነ አካሔድ ፍርሃት ዝምታችን ሰብረውልናል። ስለዚህም የሃገርና የህዝብ ድንቅ ልጆች እንጅ በጠላትነት ሊፈረጁ አይገባም። “የህዝብ የሃገር ጉዳይ ያገባናል!” ብለው ግንባራቸውን ለመስዋዕት የሰጡት ወጣቶች የህግ ከለላ ያስፈልጋቸዋል እንጅ ህግ እየተሸራረፈ መብታቸው መጣስ የለበትም።

ዞን 9 ኞች የማይወዷቸው የማግፈልጓቸው ” ሃገርና ህዝብ በድለዋል ፣ በብዕራቸው ሰላም አደፍርሰዋል!” ካሉ  የተጨበጠ መረጃ ይዘው አይሞግቷቸው አልልም። ጉዳያቸው በህግ ማዕቀፍ ተመርምሮ እና የዋስ መብታቸው ተከብሮ ትክክለኛ ፍትህን ሊያገኙ  ይገባል። ይህ ሳይደረግ የሳሾቻቸው አቤቱታ ብቻ እየተሰማ ፣  ባልረባባ ምክንያት እየወነጀሉ ዞን 9ኞችን ሊያዳክሙና ከአደባባይ መድረኩ ሊያጠፏቸው አይገባም።

በዚህ ረገድ የፍትህ አካላት የሃገርንና የህዝብን ደህንነት ከማስጠበቁ ባልተናነሰ  የታዳጊ ወጣት ጦማሪዎችን መብት የማስጠበቅ ሰው የመሆን የሞራል ግዴታ አለባቸው!

“የህዝበና የሃገር ጉዳይ ያገባናል!” ያልን ፍዳችን በዝቷል። ያም ሆኖ ዝም አንልም፣ ያገባናልና በአደጋ ተከበን እንጦምራለን!  አዎ! ያገባናልና!

ሰላም …

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule