• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍቱኝ ብዬ አልጠይቃችሁም አብሬያችሁ የሰራሁበትን ጊዜ እንደውለታ ቆጥራችሁ የሞት ፍርዱን ተግባራዊ አድርጉ”

May 29, 2018 08:56 pm by Editor 1 Comment

በሽብርተኝነት የተፈረጀው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ፀሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በልዩ ይቅርታ እንደሚፈቱ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቅዳሜ እለት መግለፁን ተከትሎ ከትንናት ሰኞ ጀምሮ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው መፈታታቸውን ሲጠብቁ ቆይተው ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ተለቀዋል።

በቤተሰባቸው ቤት ከቅዳሜ ጀምረው ሲጠባበቁ ለነበሩት ወዳጆቻቸው ባደረጉት ንግግር አቶ አንዳርጋቸው ”እኔ ተፈትቻለሁ ኢትዮጵያ ግን ያልተፈቱ ብዙ ችግሮች አሉባት” ብለዋል።

ከእስር ተፈተው ቤታቸው ሲደርሱ የተመለከቱት ነገር ያልጠበቁት እንደሆነ የተናገሩት አቶ አንዳርጋቸው። “ምንም መረጃ ባይኖረኝም ኢትዮጵያዊያን እኔን ለማስፈታት ጥረት እንደሚያደርጉ ይሰማኝ ነበር” ብለዋል።

ለዚህ ቀን መምጣት ለደከሙ ለሁሉም ሰዎች ከፍተኛ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ “የኢትዮጵያ ሕዝብ ገብቶበት ካለው አስቸጋሪ ሁኔታ አንፃር፤ እንዲህ አይነት ሃገር ከማየት ፍርድ ቤታችሁ የወሰነውን የሞት ቅጣት ተግባራዊ አድርጉ” በማለት ለመርማሪዎች መናገራቸውን ገልፀዋል።

ከዚህ በፊት በቴሌቪዥን ተቆራርጦ ነው የቀረበው ያሉትን ምስል እንዳዩት የተናገሩት አቶ አንዳርጋቸው “ሰው እየሳቀ መሞት እንደሚችል አሳያችኋለሁ ነበር ያልኳቸው፤ ነገር ግን ቆራርጠው ነው ያቀረቡት።”

ጨምረውም “ፍቱኝ ብዬ አልጠይቃችሁም አብሬያችሁ የሰራሁበትን ጊዜ እንደውለታ ቆጥራችሁ የሞት ፍርዱን ተግባራዊ አድርጉ ብዬ ጠይቄያቸዋለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከእስር እንዲፈቱ ጥረት ሲያደርግ የቆየው ሪፕሪቭ የተሰኘው መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም እንዳለው አቶ አንዳርጋቸው ለንደን ከሚገኙት የህይወት አጋራቸው የሚ ኃይለማሪያም ጋር ከአራት ዓመት በኋላ ለአጭር ጊዜ በስልክ ተነጋግረዋል።

የሪፕራይቭ ዳይሬክተር ማያ ፎአ ስለአንዳርጋቸው መፈታት በሰጡት አስተያየት “ቤተሰቡ፣ ልጆቹና ደጋፊዎቹ የሚደሰቱበት አስደሳች ዜና ነው። በቅርቡም ወደ ለንደን መጥቶ ለረጅም ጊዜ ተለይቷቸው የቆዩትን ልጆቹን ያገኛቸዋል ብዬ ተስፋ አድርጋለሁ” ብለዋል።

ሰኞ ጠዋት የእንግሊዝ ኤምባሲ መኪኖች በማረሚያ ቤት አካባቢ ተገኝተው ነበር፤ የአቶ አንዳርጋቸው እህት በስፍራው ከኤምባሲ ሰዎች ጋር የነበረች ሲሆን ለቤተሰቦቿ ደውላ ማለዳ እንዳገኘችውና ወደቤት እንደሚመጣ ነግራቸው ነበር።

ከሰኞ እለት ጀምሮ አዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ የሚገኘው የቤተሰቦቹ ቤትና አካባቢው በመፈታቱ የተሰማቸውን ደስታ በሚገልጡ መልዕክቶችና በፎቶዎቹ አሸብርቆ ውሏል።

የአንዳርጋቸው ደጋፊዎች የእርሱን ምስል የታተመበት ቲሸርት ለብሰው በአካባቢው ተገኝተው ሲጨፍሩ እና ደስታቸውን ሲገልጡ እንደነበር ተመልክተናል።

በለንደን የምትኖረው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የህይወት አጋር ወ/ሮ የምስራች ኃይለማርያም (የሚ) በባለቤቷ ሊፈታ በመሆኑ እጅግ መደሰቷን እና እስካሁንም የተፈጠረውን እንዳላመነች ለቢቢሲ ተናግራለች።

”ከአንድ ሰው ህይወት 4 አመት የሚሆነውን በእስር ማሳለፍ ምን አይነት ተጽዕኖ ሊፈጥር እንደሚችል መገመት ይከብዳል። ነገር ግን ባለቤቴ ከዚህ በኋላ ወደ ፀሃፊነት ያዘነብላል ብዬ አስባለሁ” ትላለች ወ/ሮ የሚ።

ለልጆቼ ዜናውን ስትነግራቸው በደስታ አልቅሰው ነበር የምትለው የሚ፤ እስካሁን አንዳርጋቸውን ለማነጋገር እየጠበቁ እንደሆነ ገልጻለች።

ባለቤቷ በሽብርተኝነት በተፈረጀው ግንቦት ሰባት ድርጅት ስለነበረው ኃላፊነት እና ስለቤተሰቡ ሁኔታ የተጠየቀችው የሚ፤ እንደዚህ አይነት እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ ሰዎች ከመንግሥት ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት ይታወቃል፤ ስለዚህ ሁሌም ቢሆን የሆነ ነገር ሊፈጠር እንደሚችል እገምት ነበር ብላለች።

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ቀን ጀምሮ እንዲለቀቁ ሲወተውት የነበረው ሪፕራይቭ የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ዋና ኮሚሽን የሆኑት አዳም ስሚዝ እስካሁን ድረስ አለመለቀቃቸውን ገልጾ ዛሬ ብሔራዊ በዓል ስለሆነ ላይለቀቁ ይችላሉ ሲሉ ስጋታቸውን አስቀምጠዋል።

አክለውም የእንግሊዝ ኤምባሲ አስቸኳይ የጉዞ ሰነዶችን ሊያዘጋጅ ይገባል፤ አንዳርጋቸውም አባቱን ማየት ሊፈልግ ይችላል ብለዋል።

የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አንዳርጋቸው፣ በሽብር ወንጀል ሁለት ጊዜ ክስ ተመሥርቶባቸው በዕድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ እንደተፈረደባቸው ይታወሳል።


  • አቶ አንዳርጋቸው የተወለዱትና ያደጉት አዲስ አበባ ነው። የቀለም ትምህርት ከቀመሱበት ተፈሪ መኮንን ሲወጡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኤሌክትሪክ ምህንድስና ማጥናት ጀመሩ። በዩኒቨርስቲ ቆይታቸውም በተማሪዎች ንቅናቄ ንቁ ተሳታፊ ነበሩ።
  • የአፄ ኃይለሥላሴ መንግሥት ወድቆ ደርግ ስልጣኑን ሲይዝ ኢህአፓን ተቀላቀሉ። በወቅቱ የኢህአፓ አባል የነበሩ ወጣቶች እንደሚያደርጉት በፓርቲው በህብዕ አደረጃጀት ውስጥ በመሆን የደርግ መንግሥትን መታገል ጀመሩ።
  • አቶ አንዳርጋቸው የደርግ መንግሥት የቀይ ሽብር አውጆ በርካታ ወጣቶች ላይ እርምጃ ሲወስድ ወንድማቸውን አጥተዋል። ያኔ አንዳርጋቸው ሀገር ጥለው ተሰደዱ። በወቅቱ ከኢህአፓ ጋርም በነበራቸው የርዕዮተ ዓለም ልዩነትም ከፓርቲው ተለይተው በሱዳን በኩል እንግሊዝ በመግባት ጥገኝነት ጠየቁ። በኋላም ዜግነት አግኝተዋል።
  • በ1983 የደርግ ከስልጣን ሲወገድ አዲስ የተመሰረተውን መንግሥት ለማገዝ ወደ ሀገር ተመለሱ። ነገር ግን ብዙም ሳይቆዩ ተመልሰው ወደ እንግሊዝ ሄዱ።
  • በጥር ወር 1997 ዓ.ም እንደገና አንዳርጋቸው ጽጌ አዲስ አበባ ገቡ። የመጡት በምርጫው ቅንጅትን ለመርዳት ነበር፤ ወዲያውኑም የቀስተ ዳመና አባል ኾነው የፓርቲ ሥራ ጀመሩ።
  • 1997 ሰኔ ወር ላይ አቶ አንዳርጋቸው በዝዋይ እስር ቤት በሺህዎች ከሚቆጠሩ ሰዎች ጋር ታስረው ለሁለት ሳምንታት ቆዩ። ከእስር ቤት እንደወጡ ሐምሌ 1997 ወደ እንግሊዝ ተመለሱ።
  • በግንቦት 2000 ዓ.ም ከዶክተር ብርሃኑ ነጋ ጋር በመሆን ግንቦት ሰባት ንቅናቄን መሰረቱ። አንዳርጋቸው የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ሆነው ተመርጠው ነበር።
  • ሚያዚያ 2001 ዓ.ም የኢትዮጵያ መንግሥት “በግንቦት ሰባት የተቀነባበረ መፈንቅለ መንግሥት አከሸፍኩ” ሲል ገለጸ። ግንቦት ሰባትንም አሸባሪ ሲል ፈረጀ። በዛው ዓመት አቶ አንዳርጋአው ጽጌ በሌሉበት የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው።
  • ሰኔ 2006 ዓ.ም አንዳርጋቸው የግንቦት ሰባትን ሥራ ለማካሄድ ዱባይ ገቡ። ከዱባይ ተነስቶ በየመን በኩል ወደ ኤርትራ ሊጓዙ ሲሉ ሰንዓ ላይ በየመን የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው ተሰጡ።
  • በ2007 የእንግሊዝ መንግሥት አንዳርጋቸው ከእስር እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥትን መጠየቅ ጀመረ።

ቢቢሲ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: andargachew, andy, Right Column - Primary Sidebar, tplf, tsige

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    May 30, 2018 07:37 pm at 7:37 pm

    ጨበርባሪ! ኣንዳርጋቸው! ጨበርባሪ
    መሬት ነጥቀህ! እኛን ኣስገባሪ
    ጨበርባሪ!ጨበርባሪ! ኣንት ጨበርባሪ!

    ዕውር ቢሸፍት ጓሮ!
    የጽጌ ልጆች! ከቆጥ ከጓሮ
    ፊውዳል ሁሉ! ቅሪት ፈጣሪ በዘንድሮ
    ኣንዳርጋቸው! ውጣ! እንይህ! እንደገና ለከርም! ተመክሮ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule