• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብሔር ወይስ ሰው-ነት?

November 11, 2015 12:53 am by Editor Leave a Comment

መኃኑን ታሪክ ለማዋለድ በሚደረገዉ “ጥረት” አብዝቼ ባዝንም፣ የቀደመዉን የሃገሬን ጠመዝማዛ የታሪክ መንገድ ግን ከነእንከኑ እቀበለዋለሁ፡፡ የታሪክ ክህደትም ሆነ የታሪክ ብዜትን ሊጭኑብኝ ለሚሞክሩ ሰንባችም ሆኑ አርፋጂ ብሄረተኞች ጆሮዬንም ሆነ አዕምሮዬን የምሰጥ ሰዉ አይደለሁም፡፡

ትላንትን በዛሬ መነጽር ባላየዉ እንኳን የቀደመዉን ዘመን በሰብዓዊነትና በማህበረሰባዊ ዉል ሚዛን ላይ አስቀምጬ እንድመለከተዉ ሰው-ነቴ ያስገድደኛል። ሰው ነኝና። ሰው።. . . .

በገባኝ መጠን የዛሬዋን ቁርጭምጭሚት ኢትዮጵያ ወደ ቀደመ ከፍታዋ ለማውጣትና ገጽታዋን ለማደስ ሲሚንቶው ሰብዓዊነት ሊሆን ይገባል። ከብሔር አጥር ባሻገር ዜግነት የሚባል ሰፊ ሜዳ እንዳለ ልብ እንበል። ኢትዮጵያችንን ከሁለንተናዊ ውድቀት ለመታደግም ሆነ ዳግም ለመገንባት የቀጥታ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ብቻ መፍትሄ አይደለም። ይልቁንስ በሁለንተናዊ . . . መስክ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ባህላዊ መዋቅሮችን (ድርጅቶችን) መደገፍ ሃገሪቱን ከገባችበት ማጥ ለመታደግ አማራጭ መንገድ ይመስለኛል። ጋኑ በጠጠር ሊደገፍ እንደሚችለው ሁሉ የዚህኛው መንገድ አብርክቶም ጋኑን ከደገፈው ጠጠር አያንስም፤ እንዳውም ባይበልጥ።

. . . ለቀይ-መስቀል ደማችን ስንለግስ “ብሔር”ን ታሳቢ ያደረገ ነው ወይስ ሰው-ነትን፣ ሰብዓዊ እርዳታን ግምት ውስጥ ያስገባ? መንገድ ላይ ምጽዋት ለሚጠይቀን ሰው እጃችን የምንዘረጋለት በምን መለኪያ ነው? ከ”ብሔር”ወይስ ከሰብዓዊነት አኳያ? ድንቡሼ ህጻናትን መንገድ ላይ ስናገኝ ጎንበስ ብለን የምንስማቸው በ”ብሔር” ስበት ተገፍተን ነው ወይስ ሰዋዊ የፍቅር ስሜት መርቶን?

. . . እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው . . . ኢትዮጵያን ከውድቀት ለመታደግም ሆነ ከፍታዋን በጋራ ተሳትፎ ለመገንባት ሲሚንቶው ሰብዓዊነት ነው። ከሁሉም ነገር በፊት ሰው መሆን ይቀድማል። ሰው።

smne banner1

ሙሉአለም ገ.መድህን

(“ከጎሣ ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ እንስጥ” የሚለው ንዑስ ርዕስ እና ፎቶው የተወሰደው አቶ ኦባንግ ሜቶ ከሚመሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ድረገጽ ነው፡፡ ይህ ጦማር ጸሃፊው ለዝግጅት ክፍላችን ልከውት የታተመ ነው)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule