• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብሔር ወይስ ሰው-ነት?

November 11, 2015 12:53 am by Editor Leave a Comment

መኃኑን ታሪክ ለማዋለድ በሚደረገዉ “ጥረት” አብዝቼ ባዝንም፣ የቀደመዉን የሃገሬን ጠመዝማዛ የታሪክ መንገድ ግን ከነእንከኑ እቀበለዋለሁ፡፡ የታሪክ ክህደትም ሆነ የታሪክ ብዜትን ሊጭኑብኝ ለሚሞክሩ ሰንባችም ሆኑ አርፋጂ ብሄረተኞች ጆሮዬንም ሆነ አዕምሮዬን የምሰጥ ሰዉ አይደለሁም፡፡

ትላንትን በዛሬ መነጽር ባላየዉ እንኳን የቀደመዉን ዘመን በሰብዓዊነትና በማህበረሰባዊ ዉል ሚዛን ላይ አስቀምጬ እንድመለከተዉ ሰው-ነቴ ያስገድደኛል። ሰው ነኝና። ሰው።. . . .

በገባኝ መጠን የዛሬዋን ቁርጭምጭሚት ኢትዮጵያ ወደ ቀደመ ከፍታዋ ለማውጣትና ገጽታዋን ለማደስ ሲሚንቶው ሰብዓዊነት ሊሆን ይገባል። ከብሔር አጥር ባሻገር ዜግነት የሚባል ሰፊ ሜዳ እንዳለ ልብ እንበል። ኢትዮጵያችንን ከሁለንተናዊ ውድቀት ለመታደግም ሆነ ዳግም ለመገንባት የቀጥታ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ብቻ መፍትሄ አይደለም። ይልቁንስ በሁለንተናዊ . . . መስክ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ባህላዊ መዋቅሮችን (ድርጅቶችን) መደገፍ ሃገሪቱን ከገባችበት ማጥ ለመታደግ አማራጭ መንገድ ይመስለኛል። ጋኑ በጠጠር ሊደገፍ እንደሚችለው ሁሉ የዚህኛው መንገድ አብርክቶም ጋኑን ከደገፈው ጠጠር አያንስም፤ እንዳውም ባይበልጥ።

. . . ለቀይ-መስቀል ደማችን ስንለግስ “ብሔር”ን ታሳቢ ያደረገ ነው ወይስ ሰው-ነትን፣ ሰብዓዊ እርዳታን ግምት ውስጥ ያስገባ? መንገድ ላይ ምጽዋት ለሚጠይቀን ሰው እጃችን የምንዘረጋለት በምን መለኪያ ነው? ከ”ብሔር”ወይስ ከሰብዓዊነት አኳያ? ድንቡሼ ህጻናትን መንገድ ላይ ስናገኝ ጎንበስ ብለን የምንስማቸው በ”ብሔር” ስበት ተገፍተን ነው ወይስ ሰዋዊ የፍቅር ስሜት መርቶን?

. . . እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው . . . ኢትዮጵያን ከውድቀት ለመታደግም ሆነ ከፍታዋን በጋራ ተሳትፎ ለመገንባት ሲሚንቶው ሰብዓዊነት ነው። ከሁሉም ነገር በፊት ሰው መሆን ይቀድማል። ሰው።

smne banner1

ሙሉአለም ገ.መድህን

(“ከጎሣ ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ እንስጥ” የሚለው ንዑስ ርዕስ እና ፎቶው የተወሰደው አቶ ኦባንግ ሜቶ ከሚመሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ድረገጽ ነው፡፡ ይህ ጦማር ጸሃፊው ለዝግጅት ክፍላችን ልከውት የታተመ ነው)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule