• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕያው ቤተ መዘክር

June 3, 2016 03:12 am by Editor Leave a Comment

ደራሲ፣ ተዋናይና አዘጋጅ ጌታቸው ደባልቄ በኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ደማቅ አሻራቸውን ካኖሩ አንጋፋ አርቲስቶች አንዱ ናቸው፡፡ በብዙዎች ዘንድ ‹‹ሕያው ቤተ መዘክር›› በሚል ስያሜ ይታወቃሉ፡፡ መረጃ በመሰብሰብ፣ ጠንቅቆ በመያዝና ለጠየቃቸው ሁሉ በማካፈል የሚወዳደራቸው የለም ለማለት ይቻላል፡፡ በተለይም በኪነ ጥበቡ ስለተከናወኑ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች ጥልቅ መረጃ ለማግኘት የሳቸውን በር ማንኳኳት የብዙዎች ቀዳሚ ምርጫ ሲሆን ይስተዋላል፡፡ ተማሪዎች፣ ተመራማሪዎችና ሌሎችም ግለሰቦች ለሚፈልጓቸው መረጃዎች በማስረጃ የተደረገፈ ማብራሪያ ከጌታቸው ያገኛሉ፡፡

እኚህ አርቲስት በኢትዮጵያ ቴአትርና ሙዚቃ ታሪክ ጉልህ ሚና ተጫውተዋል፡፡ ተወዳጅነትን ካተረፉ ቴአትሮቻቸውና ብዙዎችን ካስደመመ የትወና ብቃታቸው በተጨማሪ ግሩም የቴአትር አዘጋጅም ናቸው፡፡ እሳቸው ግጥም የጻፉላቸው ዘፈኖች ዘመን ተሻግረው ዛሬም ይደመጣሉ፡፡ አርቲስቱ 80ኛ ዓመታቸው ላይ ቢገኙም፣ ዛሬም ከዓመታት የሙያ ቤታቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቅጥር ግቢ አይጠፉም፡፡

በ1928 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ በ50 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው አዲስ ዓለም ከተማ ነው የተወለዱት፡፡ የጥበብን ዓለም የተቀላቀሉትም በወጣትነታቸው ነው፡፡ በ1944 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የቴአትርና ሙዚቃ ማስፋፊያ ክፍልን ተቀላቅለው በሙዚቃና ቴአትር ሥልጠና መውሰድ ጀመሩ፡፡ ከ1946 ዓ.ም. በኋላ ደግሞ ቴአትሮች እየጻፉ በቴአትር ቤቱ ያሳዩ ጀመር፡፡

1947 ዓ.ም. የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ 25ኛ ዓመት የዘውድ የብር ኢዮቤልዩ በዓልን ለማክበር መሰናዶ የተጀመረበት ዓመት ነበር፡፡ የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር ቤት የአሁኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ግንባታ የተጀመረውም በወቅቱ ነበር፡፡ ባለሙያዎች ለቴአትር ቤቱ መክፈቻ የሚሆኑ የቴአትርና የሙዚቃ ሥራዎች በማዘጋጀት ሥራ ተጠመዱ፡፡ ጌታቸውም የመሰናዶው አካል ነበሩ፡፡

getachewመስከረም 3 ቀን 1948 ዓ.ም. ቴአትር ቤቱ ሲመረቅ ከአገር ውስጥና ከውጪ የመጡም ከዋንያን ሥራዎቻቸውን አቀረቡ፡፡ የነጌታቸው ተራ ደርሶ ‹‹ዳዊትና ኦርዮን›› ከተሰኘው ቴአትር ቀንጭበው አቀረቡ፡፡ ከዚያን ወቅት ጀምሮ በጡረታ ምክንያት እስከሚወጡ ድረስ በብሔራዊ ቴአትር ከተሙ፡፡

ከወቅቱ ‹‹ዳዊትና ኦርዮን››ን ጨምሮ ‹‹ቴዎድሮስ››፣ ‹‹ሀኒባል››፣ ‹‹አስቴር›› እና  ‹‹ጎንደሬው ገብረ ማርያም›› ታዋቂ ቴአትሮች ነበሩ፡፡ ጌታቸው በበርካታ ቴአትሮች ከመሳተፋቸው ጎን ለጎን ተወዳጅነት ያተረፉ ሙዚቃዎች ጽፈዋል፡፡ ‹‹የኔ ሐሳብ››፣ ‹‹ምነው ተለየሽኝ››፣ ‹‹እንገናኛለን››፣ ‹‹በል ተነስ ልቤ›› እና ‹‹ዓለም እንዴት ሰነበተች›› ጥቂቱ ናቸው፡፡ አስናቀች ወርቁ፣ ምኒልክ ወስናቸው፣ ግርማ ነጋሽ፣ ተስፋዬ ሳህሉና ጠለላ ከበደ ግጥም ከሰጧቸው ዕውቅ ድምፃውያን መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

በ1960ዎቹ መገባደጃ የኪነ ጥበብ ሥራዎች ለፖለቲካዊ ቅስቀሳና ለፕሮፖጋንዳ መዋል የጀመሩበት ወቅት ነው፡፡ ባለሙያዎች ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ሥራዎችን ለቅስቀሳ በሚገለገሉበት ጊዜ ጌታቸውና የሙያ አጋሮቻቸው እንደ ‹‹ሀሁ በስድስት ወር›› ያሉ ሥራዎችን በአገሪቱ እየተዘዋወሩ ያሳዩ ነበር፡፡ ከኢትዮጵያ ውጪ ከአጎራባች የአፍሪካ አገሮች ጀምሮ በተለያዩ አገሮች በመዘዋወር በርካታ ቴአትሮች አሳይተዋል፡፡ በቴአትር ቤቱ የቴአትር ክፍል ኃላፊና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ በመሆንና በሌሎችም ኃላፊነቶችም  አገልግለዋል፡፡

በቀጣይ በነበሩት ዓመታት ቅድመ ምርመራ ባለሙያዎችን በእጅጉ ይፈታተን ነበር፡፡ ጌታቸው በወቅቱ ታስረው ነበር፡፡ ከሙዚቃ ግጥሞቻቸው መካከል ‹‹ሎሚ ተራ ተራ›› የሚለው ዘፈን ፖለቲካዊ ትርጓሜ ተሰጥቶት ብዙ ጥያቄዎች አስነስቶባቸውም ነበር፡፡ ከእስር ቤት ከወጡ በኋላ ‹‹ደንቆሮ በር›› የሚል መጽሐፍ ያሳተሙ ሲሆን፣ በታሰሩበት ወቅት ስላለፉበት ሁኔታና ስለተመለከቷቸው ነገሮች ያትታል፡፡ የዝነኛዋን ድምፃዊትና ተዋናይት አስናቀች ወርቁ የሕይወት ታሪክ ጽፏል፡፡ ጌታቸው በ1994 ዓ.ም. የሕይወት ዘመን የቴአትር ዘርፍ ተሸላሚ በመሆን የወርቅ ሜዳልያ አግኝተዋል፡፡ በቅርቡ የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበርም በሙዚቃው ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሸልሟቸዋል፡፡

የእኚህ አርቲስት 80ኛ ዓመት የልደት በዓል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ግንቦት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ ተከብሯል፡፡ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው የተገኙ ሲሆን፣ ለዓመታት አብረዋቸው የሠሩ የሙያ አጋሮቻቸው ትውስታቸውን አውስተዋል፡፡ ከቅርብ ጓደኞቻቸው አንዱ ከጥቂት ወራት በፊት 80ኛ ዓመታቸውን ያከበሩት አርቲስት መርዓዊ ስጦታ፣ ጌታቸው ለዓመታት ያለመታከት በቴአትር ቤቱ መሥራታቸውን ተናግረዋል፡፡

መርዓዊ ‹‹ጌታቸው፣ ሀብቱና ንብረቱ ከብሔራዊ ቴአትር ጋር የተቆራኘ የጥበብ አባት ነው፤›› በማለት ነበር የገለጹት፡፡ ሌላው አስተያየት ሰጪ አርቲስት ተስፋዬ አበበ በበኩላቸው ጌታቸው ብዙ ወጣቶች ወደ ሙያው እንዲገቡ መነሻ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ጌታቸው በሙያው ለሁላችንም ዓርአያ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ኢ/ር ታደለ ብጡል ስለጌታቸው መረጃ አያያዝና በእጃቸው ያሉ ሰነዶች ብዙዎችን መጥቀማቸውን ታናግረዋል፡፡ ውብሸት ወርቃለማሁ፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሠሠና ተስፋዬ ገብረሃናና ንግግር ካደረጉ ባለሙያዎች መካከል ይገኙበታል፡፡ ከጌታቸው ጋር በተለያየ ወቅት ያሳለፏቸውን ትውስታዎች ተናግረዋል፡፡ ‹‹መስታወት ማለት አንተ›› የተሰኘ ግጥም የጻፈው ጌትነት እንየው፣ ጌታቸውን የገለጸው እንዲህ በማለት ነበር፡፡

‹‹. . . ምንም እንኳ ከመሠረቱ

ዕድሜ መስታወት ነው ሁሉንም ያሳያል ቢልም ተረቱ

ለሀገሬ ቴአትር ግና ከዕድሜም የላቀ ማሳያ

አንተ ሰው ነህ መስታወቱ

አዎ አንተ ነህ

ገና ከጮርቃ ዕድሜ አንስተህ

አካል ሆነ በመንፈስህ ከቤተ ተውኔት ሳትነጠቅ

በማያረጅ በማያፈጅ በማያልቅ ፍቅር ተጣብቀህ

ግጥም ለዜማ ቀምረህ

ተውኔት ጽፈሕ ተውነህ መድረክ መርተህ

ውስብስቡን የጥበብ ሕይወት ጭንቅ ሸክም ሁሉ ተሸክመህ

ቤተ ተውኔትን ቤት ቤተ መድረክን መቅደስ አድርገህ

በሦስት የሥርዓት ቅይርይር አንተ ላገር ለኪነት ታምነህ

እየመጣ የሚሄደውን ስንቱን የጥበብ ሹም ሹመት ተቋቁመህ

ስንቱን ቢሮክራሲ ግንባር ለግንባር ተላትመህ

ስንቱን የሳንሱር ስለት ቁስል ሕመሙን ችለህ ታመህ

የስንቱን አድርባይ ጥበብ ከልካይ ቅስም ስብራት መክተህ

የግሌ ኑሮህን ተወት አድርገህ

ሕይወትህን ለጥበብ ሰጥተህ

ቴአትርን ያቆየህ አንተ ራስህ እየሞትክ

የሀሬን የተውኔት ሕይወት ያየሁብህ

ከዕድሜም የጠራህ የነጣህ

የሀገሬ ጥበብ ማስረጃ መስታወት ማለት አንተ ነህ . . .››

(ምንጭ: ዓለማየሁ ላቀው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule