• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጻነትን ለመጎናጸፍ ባሩዷን ማሽተት የግድ ነው !!!

July 18, 2014 09:35 pm by Editor Leave a Comment

የወያኔ የግፍ ስርዓት በህዝብ ትከሻ ላይ ድሩን አድርቶ ፤ የማይጠረግ እስኪመስለን ድረስ ሁለት አስርት አመታቶችን በላያችን ላይ ዘልቋል ።በሰላማዊ መንገድ የግፉ ስርዓት ተቋጭቶ ፍትህና እኩልነት በሀገራችን ይሰፍን ዘንድ ብዙ ተሞክሯል ። ነገር ግን በወያኔ ስልጣን አልጠግብ ባይነት እና የሰላማዊው መንገድ ክርችም ብሎ በመዘጋቱ ባሩዷን ማሽተት ግድ የሆነበት ጊዜ ላይ ከደረስን ከራርመናል ።ትግሉ ከኛ ምን ያህል የአላማ ጽናትን ይፈልጋል ? ምን ያህልስ መስዋእትነትን ያስከፍለናል ? እንዴትስ ብንታገል ካሰብነው የነጻነት ደጃፍ ባጭሩ ያደርሰናል ብለን ብንጠያየቅ ትክክለኛ ጊዜው አሁን ይመስለኛል።

አብዛኛው ኢትዮጵያዊም በተለይም በወጣትነት የእድሜ ክልል ያለው የህብረተሰብ ክፍል ስልጣንን ከህወሃት መዳፍ ውጭ አይቶት ስለማያውቅ ፤ ሀገሪቱን እነሱ ብቻ እንዲመሩ መለኮታዊ የሆነ ፈቃድ ያላቸው እስኪመስለው ድረስ ውስጡ አምኖ ተቀብሎት ነበር ለማለት ይቻላል ።ዳሩ ቢያምንም አይፈረድበትም ፤ ምክንያቱም  እድሜ ሙሉውን በገዢነት የሚያውቀው ወያኔን ብቻ ነውና ።ነገር ግን ከጥቂት አመታት ወዲህ ስንመለከት በሀገር ውስጥም ሆነ በባእድ ሀገራት በሚያስደንቅ ሁኔታ የወጣቱን አዲስ የሆነ የትግል መንፈስ በተለያዩ መድረኮች እየታየ ነው።እንደ እኔ ግምት ፤ የትግል መንፈሱን እንዲህ በከፍተኛ ሁኔታ ካጦዙት አንዱ ስርዐቱ እጅግ ከፋ የሚባልበት ደረጃ ላይ መድረሱና ሌላው የገዥው አምባገነን ቡድን በአፈሙዝ ወደ ስልጣን የመጣ ቡድን በመሆኑ ለሰላማዊ መንገድ ባይተዋርና በር የማይከፍት በመሆኑ ነው።

የወያኔ ስርዓት በርካታ የሆኑ ሰላማዊ ፣ ቡድኑን ከህዝብ የሚያስታርቁ እድሎችን በት እቢትና በተአብዮ በመወጠር ሳይጠቀምበት ቀርቷል።ሳይጠቀምበት ካመለጡት  እድሎች መሃከል የግንቦት 1997 ምርጫ በዋናነት ይጠቀሳል ። በዚያ ወቅት ህዝቡ ሙሉ በሙሉ በህወሃት መሪዎች ያለገደብ የተያዘው ስልጣን ህዝብ እጅ ይገባል ብሎ በጉጉት እየጠበቀ ያለበት ጊዜ ነበር ።በጊዜው ገዥው ፓርቲ በምርጫው ሙሉ በሙሉ የተሸነፈ ቢሆንም ሽንፈቱን መቀበል ተስኖት አፈሙዙን ወደ ህዝብ ሰድሮ ንጹሃንን በግፍ መጨፍጨፉ መቼም ከህሊናችን የሚፋቅ አይደለም ።በዚያ ወቅት በሰላም ስልጣናቸውን ለህዝብ ቢያወርዱት ኖሮ ላሳዩት ቀናኢነትና ህዝቡን በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ የስልጣን ባለቤት በማድረጋቸው ፤ ምናልባትም በ2002 ምርጫ ህዝቡ በድጋሚ እድሉን ሊሰጣቸው ይችል ነበር ብዬ እገምታለው።

በወቅቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹና ህዝቡ እውን ወያኔ ስልጣኑን ወደ ህዝብ ያወርደው ይሆን ? የሚለው ጥያቄ በአብዛኞቻችን አይምሮ ውስጥ የምርጫውን ውጤት እስክናውቅ ድረስ  ልብ ያንጠለጠለ ጉዳይ ነበር ።እንደው ግን ድምጻችን ብቻ ሳይሆን ልባቸውም አሸንፏቸው በጉልበት ከያዙት የሃላፊነት ቦታ በሰላም ገለል ቢሉ ኖሮ፤ ህዝቡም ያሁኑን ያህል የከፋ ቂም በቀል በወያኔ ላይ ይኖረዋል ብዬ አልገምትም ።ምክንያቱም የህዝቡ ሙሉ ትኩረት የስልጣን ባለቤትነቱ መረጋገጡ ላይ ስለነበረ ፤ በስልጣን ላይ በቆዩበት ጊዜያት ላጠፉት ጥፋትም የመጠየቅ አዝማሚያ አይስተዋልም ነበርና።

አሁን ግን ወያኔ መሽቶበታል ። ይቅር ከመባባያው ክልል በጣም እርቆ ተጉዟል ።በአሁኑ ሰዓት በየትኛውም አቅጣጫ የአስከፊውን ስርዓት ገፈት ቀማሽ ያልሆነ ዜጋ ፈልጎ ማግኘት ከክምር ጭድ መሃል የወደቀን መርፌ እንደመፈለግ ይቆጠራል።

ችግር ብልሃትን እንደሚፈጥር ሁሉ አብዝቶ መበደልም የነጻነት ትግልን እውን ያደርገዋል ።የወያኔ ቡድን እንዴት ሊወገድ እንደሚችል በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ የፖለቲካ ምሁሮች ያስኬዳል ያሉትን ስልቶች ጠቁመዋል ።ከዚህም መካከል የትጥቅ ትግል አንዱ ነው ።በትጥቅ ትግል መንግስታቸውን ካወረዱ ሀገራት ልምድ በመነሳት ፤ የእርስ በእርስ ጦርነት ለአንድ ሀገር መጠነ ሰፊ ጉዳቶችን የሚያስከትልና የማይረሳ የታሪክ ጠባሳ አሳርፎ የሚሄድ ስለሆነ በሃገራችን ባይከሰት መልካም ቢሆንም ፤ ነገር ግን እንደ ወያኔ ያለ አስከፊና ጨቋኝ ስርዓት ለረጅም ጊዜያት ስልጣኑን የሙጥኝ ብሎ ህዝብን እየጨቆነ ፣ እያፈነ፣ እያሰረና እየገደለ መዝለቁም ፤ ይበል የሚያሰኝ ስላልሆነ የትጥቅ ትግሉን አስፈላጊነት እርግጥ ያደርገዋል።

እርግጥ ነው ባሩድ ሳናሸት የሚገኝ ነጻነት ቢኖር ማንም አይጠላም ። ነገር ግን በአሁኑ ወቅት በገዥው መደብ በኩል በገሃድ የምናየው እብሪትና ትእቢት ፣ ህዝብን የመናቅና ያለማድመጥ ሁኔታ ትግሉን የግድ ያደርገዋል ። ምናልባት አንድ ቀን የባሩድ ሳይሆን የሽቶ መዐዛ ያሸትቱናል ብለን ለ23 ዓመታት በተስፋ ጠብቀን ነበር ። ግን አልሆነም ከዚህ በኋላም እንደማይሆን የአሁኑ አካሄዳቸው በራሱ እማኝ ነው ። ይህን አስከፊ እና በጥቂት አጉራ ዘለል የስርዓቱ ዋና አንቀሳቃሽ የሚከወነው እልህ ውስጥ የሚያስገባ ሀገራዊ በደል ማስቆም የእኛ ሃላፊነት ነው ።

የህወሃት መንግስት ስልጣን ከያዘበት ጀምሮ በጦር መሳሪያ ግዢ ስራ የተጠመደ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም።ቢሆንም የሚያስፈራንና አላማችንን አንዲት ጋትም ብትሆን ወደኋላ የሚያፈገፍግ መሆን የለበትም። ምክንያቱም ለነጻነት ትግል ለመነሳት ብዙ ሃይል ወይም ብዙ የጦር መሳሪያ አይደለም የሚያስፈልገው የቆረጠ ልብ እንጂ ይሄንን ደግሞ ካሁኖቹ ጨቋኝ ገዥዎቻችን መማር እንችላላን ። የወያኔ ቡድን ለትግል ሲነሳ 11 ሆነው መነሳታቸውን ሁላችንም የምናውቀው ነው ።ቀጥሎ የነሱን ቆርጦ መነሳት የተመለከተው ወገናቸው የመሪዎቹን ፈለግ ተከትሎ ለድል በቃና በተራው ጨቋኝ ሆኖ ቁጭ አለ ። ወገኖቼ ! ታድያ ታግሎ ያታገላቸው የቁጥራቸው መበራከት አሊያም የጦር መሳሪያ ብዛት አልነበረም ትግራይን ነጻ የማውጣት የአላማ ጽናት እንጂ ፤ እኛም ከዚህ ምሳሌ በመነሳት ኢትዮጵያን ካለችበት የጭቆና ቀንበር ለማውጣት ቁርጠኛ ልብ ያስፈልገናል።

እንደ እውነቱ ከሆነ ስርዓቱ ሞቷል  ከኛ የሚጠበቀው ተገቢውን የቀብር ስነስርዓት ማስፈጸም ብቻ ነው!!!!

እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ !!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule