• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት

April 9, 2014 02:32 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ የ5 እና የ 6ሺ ዘመን ታሪክ ያለት ሀገር ነች። የመንግስት ስርዐትም ፈጥረው ከኖሩ ሀገሮች መካከል በቅድሚያ የምትጠራ ሀገር ናት። ሆኖም ግን አንዳንዶቹ የአሁኑ ድህነታችን፣ በቴክኒኦሎጂ ወደሁዋላ መቅረታችን፣ የቀደመ የኢትዮጵያንና የህዝቡዋን ትልቅነት ለማየት ይቸግራቸዋል። ”ቤት ሲያረጅ ትሁዋን ይፈጥራል” እንደሚባለው ካልሆነ በቀር ከታሪክ እንደምንረዳው፣ አንድ ሀገር ይወድቃል ይነሳል፡ ይደኸያል ይበለጽጋል፡ ይዋረዳል ይከበራል። ሆኖም በህዝቡ የመንፈስ ጽናትና ቆራጥነት፣ የገጠመውን ድህነት፣ ውድቀትና ፈተና ሁሉ ታግሎ አሸንፎ ወደ ነበረበት የክብር ቦታው ይመለሳል። ዛሬ እኛ ደህይተናል፣ ወድቀናል፣ ተዋርደን ህዝባችን በየሀገሩ ተበትኖ የስቃይ ህይወት መኖሩ አልበቃው ብሎ በሀገሩም በሰላም እንዳይኖር በኢትዮጵያ የቅርብና የሩቅ ጠላቶች በሚደጎሙና አለኝታን ባገኙ ከሀዲዎች ሀገራችን በብሄር ተሸንሽና ኢትዮጵያዊነት ላይ ጦር ተሰብቆበታል። በተለይ ኢትዮጵያዊነቱን ጥርጣሬ ውስጥ ያላስገባው የአማራው ህዝብ በጠላትነት ተፈርጆ ይፈናቀላል፣ ይታሰራል፣ ይገደላል።

ዛሬ የኢትዮጵያ ድህነትና ወደ ሁዋላ መቅረት ጭንቅላታችንን ቀና አድርገን በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከማየት ሊጋርደን አይገባም። ወይም በአማራው ህዝብ ላይ በሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ዘመቻ እኔ የለሁበትም ለማለት ምክንያቶችን በመፈብረክ የሁለት ብሄሮች ችግር አድርጎ ማቅረብ፣ ወይም ድርጊቱን የሚፈጽሙትን በጀምላ የአንዱ ወይም የሌላው ብሄር የባህሉ መገለጫ አድርጎ ማቅረብ፣ በተለይ ለሀገርና ለህዝብ መፍትሄ ያፈልቃሉ ተብለው የሚጠበቁ የተማሩ ዜጎች በተቃራኒው የአማራውን ህዝብ ግዳይ በመጣል ስልጣን ከያዙና ጉልበት ካለቸው ጋር ለመተቃቀፍ በጽሁፍ፣ በድምጽና በምስል ቅጅዎች፣ በትብብርና ዝምታን መደበቂያ አድርጎ በመምረጥ የሚያሳዩት ግብራአበርነት ኢትዮጵያዊነትን አይገነባም።

ዛሬ በአንድ የአማራው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው አንድን ሰውና ወገን፤ ከአማራ ወላጆች መወለዱን ብቻ ዋናና አይነተኛ ምክንያት አድርጎ አንድን ሰው ተወልዶ ካረጀበት ቀየው ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማጋዝና መግደል ነገ ሌላውን ተረኛ አያደርግም ብሎ ማሰብ፣ አርቆና አሻግሮ ማየት አለመቻልን ብቻ ሳይሆን፡ አንድነት፣ ሙሉነት፣ ጥራት፣ አይነተኛነት የጎደለው የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት ብቻ መሆኑን ግልጽ አድርጎ የሚያሳይ ይመስለናል።

ኢትዮጵያዊነት መከባበር፣ መተዛዘን፣ መነፋፈቅ፣ መፈቃቀር፣ መተሳሰብ እንጂ አንድ ህዝብ ተለይቶ ሲጋዝ፣ ሲሰደድ፣ ሲፈናቀል፣ በህይወት በገደል ሲጣል፣ ቤት ተዘግቶበት ሲቃጠል፣ ማስተባበያ ምክንያት እየፈጠሩ ከአጥቂው ጋር መወገን፣ ሙሉነቱንና አይነተኛነቱን፣ ሀቀኛነቱንና ጽናቱን የተገፈፈ የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት ከመሆን ያለፈ አይሆንም።

ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን የመንግስት ስርአት መስርታ የኖረች ሀገር በመሆኑዋ የአማራው ህዝብ አሁንም ቢሆን ተወልዶ ከአረጀበት፣ ያያት የቅድመ አያቱ አጽም ካረፈበት፣ አባት አያት ቅድመአያቱ ከውጭ ወራሪ፣ ከውስጥ ከሀዲ የደም ዋጋ ከፍለው ካወረሱት ሀገሩ፣ ”ይህ ያንተ ሀገር  አይደለም” ተብሎ ሲፈናቀል አሁንም ቢሆን ለመንግስት አቤት ይላል። ይህ በረጅም ዘመን የተገነባው በህግና በመንግስት ላይ ያለን እምነት ከስር ከመሰረቱ ከህዝብ ስነልቦና ሰልቦ በምትኩ በህዝብ መካከል አለመተማመንን፣ መጠራጠርንና የጎሪጥ መተያየትን ለመተካት በህዘብና በሀገር  ከሀዲዎች ሳያዛንፍ ከ20  ዓመት በላይ አንድን ህዝብ ለይቶ የማጥፋት ዘመቻ የሚፈጥረው፣ የነፈሰበት፣ የተበላሸ፣ የተመረዘ ኢትዮጵያዊነት እንጂ፣ በእምነቱ የጸና፣ የተከበረና የኮራ ኢትዮጵያዊነትን አይሆንም።

በአንድ አካባቢ፣ ቀበሌና ቀዬ በእድሩ፣ በማህበሩ፣ በቤተ ክርስቲያኑ፣ በመስጊዱና በመሳሰሉት ህብረተሰቡን በሚያገናኙት ነገሮች አንድ ሆኖ በአንድነት የኖረን ህዝብ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ታሪካዊ የቅርብና የሩቅ ጠላቶች በገንዘብ፣ በመሳሪያ፣ በሎጅስቲክና በመሳሰሎ ነገሮች እርዳታና ስልጠና አግኝተው ለስልጣን ከበቁ የሀገርና የህዝብ ከሀዲዎች ኢትዮጵያዊነትን መጠበቅ ከእባብ የእርግብ እንቁላል መጠበቅ ይሆናል።

የአማራው ህዝብ ”ነግ በኔ” የሚል ነገን አሻግሮ የሚያይ አኩሪ ባህል ያለው ህዝብ በመሆኑ፣ ክፉውን ከደጉ ለይቶ፣ በከንቱነት ፈርጇቸው ትግሉን በአንድ ኢትዮጵያዊነትና በአንድ የኢትዮጵያ ህዝብነት ሙሉ እምነት ትግሉን በትእግስትና በጽናት እስካሁን ተቋቁሟል፣ ነገም ይቋቋማል። እህቶቻችን በአምካኝ መድሀኒት ዘር እንዳይተኩ ሆነዋል፡ አባቶቻችን በህይወት በገደል ተጥለዋል፣ ቆዳቸው ተገፎ ተገለዋል፤ ወንድሞቻችን ያባቶቻቸው አጽም ካረፈበት ቀያቸው ሀገራችሁ አይደለም ተብለው ተፈናቅለዋል፡ ታሪካችንን ወደሁዋላ ሄደን እንድንመረምር ተገፍተናል፣ ሀገራችንና ህዝባችን በጣሊያን ወረራ ወቅት ያሳለፉትን ፈተና ከወረቀት አልፎ በአይን አይተናል። አንድን ህዝብ በቋንቋ መክፈል፣ የነፈሰበት፣ የተሳከረ ኢትዮጵያዊነት እንጂ፣ አንድነቱ የጸና እና በኢትዮጵያዊነቱ የኮራ ኢትዮጵያዊነት ይገነባል የሚል ቅዠት የለንም።

ኢትዮጵያ በልጆቿ የመንፈስ ጽናት ተመልሳ በእግሯ ትቆማለች።

ኢትዮጵያ በነጻነቷና በአንድነቷ ለዘላለም ኮርታ ትኑር

ሞረሽ ወገኔ ማህበር በስዊድን

moweswe@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule