• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት

April 9, 2014 02:32 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ የ5 እና የ 6ሺ ዘመን ታሪክ ያለት ሀገር ነች። የመንግስት ስርዐትም ፈጥረው ከኖሩ ሀገሮች መካከል በቅድሚያ የምትጠራ ሀገር ናት። ሆኖም ግን አንዳንዶቹ የአሁኑ ድህነታችን፣ በቴክኒኦሎጂ ወደሁዋላ መቅረታችን፣ የቀደመ የኢትዮጵያንና የህዝቡዋን ትልቅነት ለማየት ይቸግራቸዋል። ”ቤት ሲያረጅ ትሁዋን ይፈጥራል” እንደሚባለው ካልሆነ በቀር ከታሪክ እንደምንረዳው፣ አንድ ሀገር ይወድቃል ይነሳል፡ ይደኸያል ይበለጽጋል፡ ይዋረዳል ይከበራል። ሆኖም በህዝቡ የመንፈስ ጽናትና ቆራጥነት፣ የገጠመውን ድህነት፣ ውድቀትና ፈተና ሁሉ ታግሎ አሸንፎ ወደ ነበረበት የክብር ቦታው ይመለሳል። ዛሬ እኛ ደህይተናል፣ ወድቀናል፣ ተዋርደን ህዝባችን በየሀገሩ ተበትኖ የስቃይ ህይወት መኖሩ አልበቃው ብሎ በሀገሩም በሰላም እንዳይኖር በኢትዮጵያ የቅርብና የሩቅ ጠላቶች በሚደጎሙና አለኝታን ባገኙ ከሀዲዎች ሀገራችን በብሄር ተሸንሽና ኢትዮጵያዊነት ላይ ጦር ተሰብቆበታል። በተለይ ኢትዮጵያዊነቱን ጥርጣሬ ውስጥ ያላስገባው የአማራው ህዝብ በጠላትነት ተፈርጆ ይፈናቀላል፣ ይታሰራል፣ ይገደላል።

ዛሬ የኢትዮጵያ ድህነትና ወደ ሁዋላ መቅረት ጭንቅላታችንን ቀና አድርገን በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከማየት ሊጋርደን አይገባም። ወይም በአማራው ህዝብ ላይ በሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ዘመቻ እኔ የለሁበትም ለማለት ምክንያቶችን በመፈብረክ የሁለት ብሄሮች ችግር አድርጎ ማቅረብ፣ ወይም ድርጊቱን የሚፈጽሙትን በጀምላ የአንዱ ወይም የሌላው ብሄር የባህሉ መገለጫ አድርጎ ማቅረብ፣ በተለይ ለሀገርና ለህዝብ መፍትሄ ያፈልቃሉ ተብለው የሚጠበቁ የተማሩ ዜጎች በተቃራኒው የአማራውን ህዝብ ግዳይ በመጣል ስልጣን ከያዙና ጉልበት ካለቸው ጋር ለመተቃቀፍ በጽሁፍ፣ በድምጽና በምስል ቅጅዎች፣ በትብብርና ዝምታን መደበቂያ አድርጎ በመምረጥ የሚያሳዩት ግብራአበርነት ኢትዮጵያዊነትን አይገነባም።

ዛሬ በአንድ የአማራው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው አንድን ሰውና ወገን፤ ከአማራ ወላጆች መወለዱን ብቻ ዋናና አይነተኛ ምክንያት አድርጎ አንድን ሰው ተወልዶ ካረጀበት ቀየው ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማጋዝና መግደል ነገ ሌላውን ተረኛ አያደርግም ብሎ ማሰብ፣ አርቆና አሻግሮ ማየት አለመቻልን ብቻ ሳይሆን፡ አንድነት፣ ሙሉነት፣ ጥራት፣ አይነተኛነት የጎደለው የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት ብቻ መሆኑን ግልጽ አድርጎ የሚያሳይ ይመስለናል።

ኢትዮጵያዊነት መከባበር፣ መተዛዘን፣ መነፋፈቅ፣ መፈቃቀር፣ መተሳሰብ እንጂ አንድ ህዝብ ተለይቶ ሲጋዝ፣ ሲሰደድ፣ ሲፈናቀል፣ በህይወት በገደል ሲጣል፣ ቤት ተዘግቶበት ሲቃጠል፣ ማስተባበያ ምክንያት እየፈጠሩ ከአጥቂው ጋር መወገን፣ ሙሉነቱንና አይነተኛነቱን፣ ሀቀኛነቱንና ጽናቱን የተገፈፈ የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት ከመሆን ያለፈ አይሆንም።

ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን የመንግስት ስርአት መስርታ የኖረች ሀገር በመሆኑዋ የአማራው ህዝብ አሁንም ቢሆን ተወልዶ ከአረጀበት፣ ያያት የቅድመ አያቱ አጽም ካረፈበት፣ አባት አያት ቅድመአያቱ ከውጭ ወራሪ፣ ከውስጥ ከሀዲ የደም ዋጋ ከፍለው ካወረሱት ሀገሩ፣ ”ይህ ያንተ ሀገር  አይደለም” ተብሎ ሲፈናቀል አሁንም ቢሆን ለመንግስት አቤት ይላል። ይህ በረጅም ዘመን የተገነባው በህግና በመንግስት ላይ ያለን እምነት ከስር ከመሰረቱ ከህዝብ ስነልቦና ሰልቦ በምትኩ በህዝብ መካከል አለመተማመንን፣ መጠራጠርንና የጎሪጥ መተያየትን ለመተካት በህዘብና በሀገር  ከሀዲዎች ሳያዛንፍ ከ20  ዓመት በላይ አንድን ህዝብ ለይቶ የማጥፋት ዘመቻ የሚፈጥረው፣ የነፈሰበት፣ የተበላሸ፣ የተመረዘ ኢትዮጵያዊነት እንጂ፣ በእምነቱ የጸና፣ የተከበረና የኮራ ኢትዮጵያዊነትን አይሆንም።

በአንድ አካባቢ፣ ቀበሌና ቀዬ በእድሩ፣ በማህበሩ፣ በቤተ ክርስቲያኑ፣ በመስጊዱና በመሳሰሉት ህብረተሰቡን በሚያገናኙት ነገሮች አንድ ሆኖ በአንድነት የኖረን ህዝብ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ታሪካዊ የቅርብና የሩቅ ጠላቶች በገንዘብ፣ በመሳሪያ፣ በሎጅስቲክና በመሳሰሎ ነገሮች እርዳታና ስልጠና አግኝተው ለስልጣን ከበቁ የሀገርና የህዝብ ከሀዲዎች ኢትዮጵያዊነትን መጠበቅ ከእባብ የእርግብ እንቁላል መጠበቅ ይሆናል።

የአማራው ህዝብ ”ነግ በኔ” የሚል ነገን አሻግሮ የሚያይ አኩሪ ባህል ያለው ህዝብ በመሆኑ፣ ክፉውን ከደጉ ለይቶ፣ በከንቱነት ፈርጇቸው ትግሉን በአንድ ኢትዮጵያዊነትና በአንድ የኢትዮጵያ ህዝብነት ሙሉ እምነት ትግሉን በትእግስትና በጽናት እስካሁን ተቋቁሟል፣ ነገም ይቋቋማል። እህቶቻችን በአምካኝ መድሀኒት ዘር እንዳይተኩ ሆነዋል፡ አባቶቻችን በህይወት በገደል ተጥለዋል፣ ቆዳቸው ተገፎ ተገለዋል፤ ወንድሞቻችን ያባቶቻቸው አጽም ካረፈበት ቀያቸው ሀገራችሁ አይደለም ተብለው ተፈናቅለዋል፡ ታሪካችንን ወደሁዋላ ሄደን እንድንመረምር ተገፍተናል፣ ሀገራችንና ህዝባችን በጣሊያን ወረራ ወቅት ያሳለፉትን ፈተና ከወረቀት አልፎ በአይን አይተናል። አንድን ህዝብ በቋንቋ መክፈል፣ የነፈሰበት፣ የተሳከረ ኢትዮጵያዊነት እንጂ፣ አንድነቱ የጸና እና በኢትዮጵያዊነቱ የኮራ ኢትዮጵያዊነት ይገነባል የሚል ቅዠት የለንም።

ኢትዮጵያ በልጆቿ የመንፈስ ጽናት ተመልሳ በእግሯ ትቆማለች።

ኢትዮጵያ በነጻነቷና በአንድነቷ ለዘላለም ኮርታ ትኑር

ሞረሽ ወገኔ ማህበር በስዊድን

moweswe@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule