• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት

April 9, 2014 02:32 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ የ5 እና የ 6ሺ ዘመን ታሪክ ያለት ሀገር ነች። የመንግስት ስርዐትም ፈጥረው ከኖሩ ሀገሮች መካከል በቅድሚያ የምትጠራ ሀገር ናት። ሆኖም ግን አንዳንዶቹ የአሁኑ ድህነታችን፣ በቴክኒኦሎጂ ወደሁዋላ መቅረታችን፣ የቀደመ የኢትዮጵያንና የህዝቡዋን ትልቅነት ለማየት ይቸግራቸዋል። ”ቤት ሲያረጅ ትሁዋን ይፈጥራል” እንደሚባለው ካልሆነ በቀር ከታሪክ እንደምንረዳው፣ አንድ ሀገር ይወድቃል ይነሳል፡ ይደኸያል ይበለጽጋል፡ ይዋረዳል ይከበራል። ሆኖም በህዝቡ የመንፈስ ጽናትና ቆራጥነት፣ የገጠመውን ድህነት፣ ውድቀትና ፈተና ሁሉ ታግሎ አሸንፎ ወደ ነበረበት የክብር ቦታው ይመለሳል። ዛሬ እኛ ደህይተናል፣ ወድቀናል፣ ተዋርደን ህዝባችን በየሀገሩ ተበትኖ የስቃይ ህይወት መኖሩ አልበቃው ብሎ በሀገሩም በሰላም እንዳይኖር በኢትዮጵያ የቅርብና የሩቅ ጠላቶች በሚደጎሙና አለኝታን ባገኙ ከሀዲዎች ሀገራችን በብሄር ተሸንሽና ኢትዮጵያዊነት ላይ ጦር ተሰብቆበታል። በተለይ ኢትዮጵያዊነቱን ጥርጣሬ ውስጥ ያላስገባው የአማራው ህዝብ በጠላትነት ተፈርጆ ይፈናቀላል፣ ይታሰራል፣ ይገደላል።

ዛሬ የኢትዮጵያ ድህነትና ወደ ሁዋላ መቅረት ጭንቅላታችንን ቀና አድርገን በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከማየት ሊጋርደን አይገባም። ወይም በአማራው ህዝብ ላይ በሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ዘመቻ እኔ የለሁበትም ለማለት ምክንያቶችን በመፈብረክ የሁለት ብሄሮች ችግር አድርጎ ማቅረብ፣ ወይም ድርጊቱን የሚፈጽሙትን በጀምላ የአንዱ ወይም የሌላው ብሄር የባህሉ መገለጫ አድርጎ ማቅረብ፣ በተለይ ለሀገርና ለህዝብ መፍትሄ ያፈልቃሉ ተብለው የሚጠበቁ የተማሩ ዜጎች በተቃራኒው የአማራውን ህዝብ ግዳይ በመጣል ስልጣን ከያዙና ጉልበት ካለቸው ጋር ለመተቃቀፍ በጽሁፍ፣ በድምጽና በምስል ቅጅዎች፣ በትብብርና ዝምታን መደበቂያ አድርጎ በመምረጥ የሚያሳዩት ግብራአበርነት ኢትዮጵያዊነትን አይገነባም።

ዛሬ በአንድ የአማራው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው አንድን ሰውና ወገን፤ ከአማራ ወላጆች መወለዱን ብቻ ዋናና አይነተኛ ምክንያት አድርጎ አንድን ሰው ተወልዶ ካረጀበት ቀየው ማፈናቀል፣ ማሰር፣ ማጋዝና መግደል ነገ ሌላውን ተረኛ አያደርግም ብሎ ማሰብ፣ አርቆና አሻግሮ ማየት አለመቻልን ብቻ ሳይሆን፡ አንድነት፣ ሙሉነት፣ ጥራት፣ አይነተኛነት የጎደለው የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት ብቻ መሆኑን ግልጽ አድርጎ የሚያሳይ ይመስለናል።

ኢትዮጵያዊነት መከባበር፣ መተዛዘን፣ መነፋፈቅ፣ መፈቃቀር፣ መተሳሰብ እንጂ አንድ ህዝብ ተለይቶ ሲጋዝ፣ ሲሰደድ፣ ሲፈናቀል፣ በህይወት በገደል ሲጣል፣ ቤት ተዘግቶበት ሲቃጠል፣ ማስተባበያ ምክንያት እየፈጠሩ ከአጥቂው ጋር መወገን፣ ሙሉነቱንና አይነተኛነቱን፣ ሀቀኛነቱንና ጽናቱን የተገፈፈ የነፈሰበት ኢትዮጵያዊነት ከመሆን ያለፈ አይሆንም።

ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን የመንግስት ስርአት መስርታ የኖረች ሀገር በመሆኑዋ የአማራው ህዝብ አሁንም ቢሆን ተወልዶ ከአረጀበት፣ ያያት የቅድመ አያቱ አጽም ካረፈበት፣ አባት አያት ቅድመአያቱ ከውጭ ወራሪ፣ ከውስጥ ከሀዲ የደም ዋጋ ከፍለው ካወረሱት ሀገሩ፣ ”ይህ ያንተ ሀገር  አይደለም” ተብሎ ሲፈናቀል አሁንም ቢሆን ለመንግስት አቤት ይላል። ይህ በረጅም ዘመን የተገነባው በህግና በመንግስት ላይ ያለን እምነት ከስር ከመሰረቱ ከህዝብ ስነልቦና ሰልቦ በምትኩ በህዝብ መካከል አለመተማመንን፣ መጠራጠርንና የጎሪጥ መተያየትን ለመተካት በህዘብና በሀገር  ከሀዲዎች ሳያዛንፍ ከ20  ዓመት በላይ አንድን ህዝብ ለይቶ የማጥፋት ዘመቻ የሚፈጥረው፣ የነፈሰበት፣ የተበላሸ፣ የተመረዘ ኢትዮጵያዊነት እንጂ፣ በእምነቱ የጸና፣ የተከበረና የኮራ ኢትዮጵያዊነትን አይሆንም።

በአንድ አካባቢ፣ ቀበሌና ቀዬ በእድሩ፣ በማህበሩ፣ በቤተ ክርስቲያኑ፣ በመስጊዱና በመሳሰሉት ህብረተሰቡን በሚያገናኙት ነገሮች አንድ ሆኖ በአንድነት የኖረን ህዝብ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ታሪካዊ የቅርብና የሩቅ ጠላቶች በገንዘብ፣ በመሳሪያ፣ በሎጅስቲክና በመሳሰሎ ነገሮች እርዳታና ስልጠና አግኝተው ለስልጣን ከበቁ የሀገርና የህዝብ ከሀዲዎች ኢትዮጵያዊነትን መጠበቅ ከእባብ የእርግብ እንቁላል መጠበቅ ይሆናል።

የአማራው ህዝብ ”ነግ በኔ” የሚል ነገን አሻግሮ የሚያይ አኩሪ ባህል ያለው ህዝብ በመሆኑ፣ ክፉውን ከደጉ ለይቶ፣ በከንቱነት ፈርጇቸው ትግሉን በአንድ ኢትዮጵያዊነትና በአንድ የኢትዮጵያ ህዝብነት ሙሉ እምነት ትግሉን በትእግስትና በጽናት እስካሁን ተቋቁሟል፣ ነገም ይቋቋማል። እህቶቻችን በአምካኝ መድሀኒት ዘር እንዳይተኩ ሆነዋል፡ አባቶቻችን በህይወት በገደል ተጥለዋል፣ ቆዳቸው ተገፎ ተገለዋል፤ ወንድሞቻችን ያባቶቻቸው አጽም ካረፈበት ቀያቸው ሀገራችሁ አይደለም ተብለው ተፈናቅለዋል፡ ታሪካችንን ወደሁዋላ ሄደን እንድንመረምር ተገፍተናል፣ ሀገራችንና ህዝባችን በጣሊያን ወረራ ወቅት ያሳለፉትን ፈተና ከወረቀት አልፎ በአይን አይተናል። አንድን ህዝብ በቋንቋ መክፈል፣ የነፈሰበት፣ የተሳከረ ኢትዮጵያዊነት እንጂ፣ አንድነቱ የጸና እና በኢትዮጵያዊነቱ የኮራ ኢትዮጵያዊነት ይገነባል የሚል ቅዠት የለንም።

ኢትዮጵያ በልጆቿ የመንፈስ ጽናት ተመልሳ በእግሯ ትቆማለች።

ኢትዮጵያ በነጻነቷና በአንድነቷ ለዘላለም ኮርታ ትኑር

ሞረሽ ወገኔ ማህበር በስዊድን

moweswe@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule