• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልጄ አካለ ስንኩል ነው እንጂ አእምሮ ስንኩል አይደለም”

March 12, 2014 08:43 am by Editor Leave a Comment

አካለ ስንኩል የሆነውን ልጁን በትከሻው በመሸከም በየቀኑ 14.4ኪሜ (9ማይል) በእግሩ በመጓዝ ለሚያመላልሰው አባት መንግሥት በአቅራቢያው ቤት እንደሚሰጠው ተነገረ፡፡

በደቡብ ምዕራብ የቻይና ግዛት የሚኖረው የአርባ አመቱ አባት አካለ ስንኩል የሆነውን የ12ዓመት ልጁን ት/ቤት ለማስገባት ካለው የጸና እምነት የተነሳ ልጁ ራሱን ችሎ መራመድ የማችል በመሆኑ ለመጓጓዣ ባዘጋጀው ለየት ያለ ቅርጫት በመሸከም ከመስከረም ወር ጀምሮ እያመላለሰው መሆኑን የቻይናን ዜና ምንጮችን ጠቅሶ ዴይሊ ሜል ዘግቧል፡፡

ልጁ የሦስት ዓመት ህጻን በነበረበት ወቅት ከወላጅ እናቱ ጋር የተለያየው አባት ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ልጁን ብቻውን ያሳደገው ሲሆን እናቱ ብትለይም ልጁን ብቻውን ለማሳደግ በመወሰን መክፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል የዚያኑ ጊዜ መወሰኑን ተናግሯል፡፡ ልጁ እያደገ ሲመጣ ት/ቤት ለማስገባት በአካባቢው ያሉትን ሲጠይቅ አዎንታዊ ምላሽ ባለማግኘቱ ከአካባቢው ርቆ ወደሚገኝ ት/ቤት ለማስገባት ይወስናል፡፡ ሆኖም ት/ቤቱ ከሚኖርበት ገጠር 7.2ኪሜ (4.5ማይል) የሚርቅ በመሆኑ ልጁን ራሱ ተሸክሞ ለማመላለስ በመወሰን ከመስከረም ወር ጀምሮ እያመላለሰው እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡

father 6“ልጄ አካለ ስንኩል ነው እንጂ አእምሮ ስንኩል አይደለም” የሚለው አባት በእርሱ ግምት እስካሁን ከ2500ኪሜ በላይ ተጉዟል፡፡ ዕለታዊ ሁኔታውን ሲገልጽም ጠዋት 11ሠዓት ላይ በመነሳት ለልጁ ቁርስ ያዘጋጃል፡፡ ከዚያም 7.2ኪሜ (4.5ማይል) ልጁን ተሸክሞ ይሄዳል፡፡ ት/ቤት አድርሶ ወዲያው ወደቤቱ በመመለስ ለኑሮው የሚሆነውን ዕለታዊ ሥራውን ሲያከናውን ይቆያል፡፡ ከሰዓት በኋላም የመጣበትን 7.2ኪሜ እንደገና በመመለስ ልጁን ከት/ቤት ያመጣል፡፡ በዚህም በቀን 18ኪሜ ከቤቱ ት/ቤት እንደሚመላለስ ይናገራል፡፡

በሚያደርገው ደስተኛ እንደሆነ የተናገው አባት ልጁ በት/ቤት ውጤቱ ከክፍሉ አንደኛ መሆኑ እንደሚያኮራው ይናገራል፡፡ “ትልቅ ደረጃ እንደሚደርስ አውቃለሁ፤ ሕልሜ ኮሌጅ እንዲገባ ነው” በማለት በልጁ ያለውን ተስፋ ይናገራል፡፡

በአካባቢው የሚገኝ የዜና ዘጋቢ ጉዳዩን ይፋ ካደረገው በኋላ የአካባቢው የመንግሥት መስተዳድር በልጁ ት/ቤት አቅራቢያ ቤት እንደሚከራይለት ለአባትየውና ለልጁ ቃል ገብቷል፡፡ ት/ቤቱም ወደፊት ለእንደነዚህ ዓይነት ልጆች የሚሆን የማደሪያ ቦታ ለማመቻቸት ማሰቡን ገልጾዋል፡፡

father 3 father 4 father 5 father 1


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule