• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልጄ አካለ ስንኩል ነው እንጂ አእምሮ ስንኩል አይደለም”

March 12, 2014 08:43 am by Editor Leave a Comment

አካለ ስንኩል የሆነውን ልጁን በትከሻው በመሸከም በየቀኑ 14.4ኪሜ (9ማይል) በእግሩ በመጓዝ ለሚያመላልሰው አባት መንግሥት በአቅራቢያው ቤት እንደሚሰጠው ተነገረ፡፡

በደቡብ ምዕራብ የቻይና ግዛት የሚኖረው የአርባ አመቱ አባት አካለ ስንኩል የሆነውን የ12ዓመት ልጁን ት/ቤት ለማስገባት ካለው የጸና እምነት የተነሳ ልጁ ራሱን ችሎ መራመድ የማችል በመሆኑ ለመጓጓዣ ባዘጋጀው ለየት ያለ ቅርጫት በመሸከም ከመስከረም ወር ጀምሮ እያመላለሰው መሆኑን የቻይናን ዜና ምንጮችን ጠቅሶ ዴይሊ ሜል ዘግቧል፡፡

ልጁ የሦስት ዓመት ህጻን በነበረበት ወቅት ከወላጅ እናቱ ጋር የተለያየው አባት ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ልጁን ብቻውን ያሳደገው ሲሆን እናቱ ብትለይም ልጁን ብቻውን ለማሳደግ በመወሰን መክፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል የዚያኑ ጊዜ መወሰኑን ተናግሯል፡፡ ልጁ እያደገ ሲመጣ ት/ቤት ለማስገባት በአካባቢው ያሉትን ሲጠይቅ አዎንታዊ ምላሽ ባለማግኘቱ ከአካባቢው ርቆ ወደሚገኝ ት/ቤት ለማስገባት ይወስናል፡፡ ሆኖም ት/ቤቱ ከሚኖርበት ገጠር 7.2ኪሜ (4.5ማይል) የሚርቅ በመሆኑ ልጁን ራሱ ተሸክሞ ለማመላለስ በመወሰን ከመስከረም ወር ጀምሮ እያመላለሰው እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡

father 6“ልጄ አካለ ስንኩል ነው እንጂ አእምሮ ስንኩል አይደለም” የሚለው አባት በእርሱ ግምት እስካሁን ከ2500ኪሜ በላይ ተጉዟል፡፡ ዕለታዊ ሁኔታውን ሲገልጽም ጠዋት 11ሠዓት ላይ በመነሳት ለልጁ ቁርስ ያዘጋጃል፡፡ ከዚያም 7.2ኪሜ (4.5ማይል) ልጁን ተሸክሞ ይሄዳል፡፡ ት/ቤት አድርሶ ወዲያው ወደቤቱ በመመለስ ለኑሮው የሚሆነውን ዕለታዊ ሥራውን ሲያከናውን ይቆያል፡፡ ከሰዓት በኋላም የመጣበትን 7.2ኪሜ እንደገና በመመለስ ልጁን ከት/ቤት ያመጣል፡፡ በዚህም በቀን 18ኪሜ ከቤቱ ት/ቤት እንደሚመላለስ ይናገራል፡፡

በሚያደርገው ደስተኛ እንደሆነ የተናገው አባት ልጁ በት/ቤት ውጤቱ ከክፍሉ አንደኛ መሆኑ እንደሚያኮራው ይናገራል፡፡ “ትልቅ ደረጃ እንደሚደርስ አውቃለሁ፤ ሕልሜ ኮሌጅ እንዲገባ ነው” በማለት በልጁ ያለውን ተስፋ ይናገራል፡፡

በአካባቢው የሚገኝ የዜና ዘጋቢ ጉዳዩን ይፋ ካደረገው በኋላ የአካባቢው የመንግሥት መስተዳድር በልጁ ት/ቤት አቅራቢያ ቤት እንደሚከራይለት ለአባትየውና ለልጁ ቃል ገብቷል፡፡ ት/ቤቱም ወደፊት ለእንደነዚህ ዓይነት ልጆች የሚሆን የማደሪያ ቦታ ለማመቻቸት ማሰቡን ገልጾዋል፡፡

father 3 father 4 father 5 father 1


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule