• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለዲያስፖራ ኗሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

August 3, 2014 06:28 am by Editor Leave a Comment

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) ለስድብና ለማዋረድ ሥራ በክፍያ ያሰማራቸው ቅጥረኛ ባንዳዎችን እንዋጋ!!

ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ግለሰብ ኢትዮጵያውያንን፤ ድርጅትና፤ ተቋማትን እያሳደዱ እንዲሰድቡና እንዲያዋርዱ ወያኔ አሰልጥኖ ያሰማራቸው ቅጥረኞች ሕዝብን ስይፈሩና ሳያፍሩ የባንዳነት ተግባራቸውን ቀጥለውበት ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ መንግሥት የሚል ስያሜን የያዘው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) እነዚህን ተሳዳቢ ቅጥረኞች ያሰማራው የቻይና መንግሥት የኮሚንስት ፓርቲውን አመራር የሚቃወሙና የሚተቹ ግለሰብና ተቋማትን ለማሸማቀቅ ሲል አቋቁሞት የነበረውን የ50 ሳንቲም ፓርቲ (50 Pence Party) ዘዴን በመውረስ ሲሆን ዓላማውም ለወያኔ የማይመችን ኢትዮጵያዊ ግለሰብ፤ ማህበረሰብንና ተቋምን ሁሉ በመስደብ በማዋረድና በሃሰት ክስ በማሸማቀቅ ቅስሙን ሰብሮ ተገዢ ለማድረግ ነው።

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) ይህንን ከቻይና አገዛዝ የወረሰውን የአዋርደህ ግዛ ዘዴ ሥራ ላይ ለማዋል ያፈለገበትም፤ በሃገር ውስጥ የአገዛዝ ሥርዓቱን የሚቃወሙ፤ ለሥርዓቱ የማይገዙና የማያጎበድዱ ሃገርና ሕዝብ ወዳድ ግለሰቦችና ቡድኖችን  ሁሉ በፌደራል ፖሊስና በደህንነት ኃይል እያነቀ መግረፍ፤ ማሰቃየት፤ ማሰርና ከዛም ካለፈ በመግደል ፀጥ የማድረግ እርምጃው በተጨማሪ ይህንን ለማድረግ በማይችልበት ወቅትና አካባቢ በተለይም ደግሞ በውጪ ሃገር በሚኖረው ኢትዮጵያዊ ላይ ተፈጻሚነት እንዲኖረው በማሰብ ለመሆኑ በየጊዜው የአገዛዝ ሥርዓቱን እየከዱ የሚኮበልሉ ባለሥልጣናት ጭምር ያረጋገጡት ጉዳይ ነው።

በዚህ የአዋርደህና አሸማቀህ ግዛ ዘዴ መሠረትም የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) በተለይ በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ላይ ያነጣጠሩ ዌብ ሳይቶችን፤ ብሎግ እና አያሌ የሶሻል ሚዲያ መድረኮችን በመክፈት አገዛዙ በጠላትነት የፈረጃቸው ግለሰቦች፤ ቡድን እና ተቋማት ላይ የተለያዩ ስብዕናን የሚያረክሱ ስድቦችን፤ የሃሰት ውንጀላዎችንና ክሶችን በማዥጎድጎድ ግለሰብና ተቋማቱ ቅስማቸው ተሰብሮ ፈርተውና ተሸማቀው እንዲኖሩ ለማድረግ  የስድብ ቅጥረኞቹን አስልጥኖ በሕብረተ ሰቡ ውስጥ በማሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ እየከፈላቸው በሙሉ ሰዓት ሰራተኝነት ይህንኑ የስድብና የማዋረድ ተግባራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

እነዚህም በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ውስጥ በመሰግሰግ በኮሚኒቲም ይሁን፤ በፓሊቲካና በሲቪክ ድርጅቶች፤ እንዲሁም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሳይቀር ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ሃቀኛ ኢትዮጵያውያንን ስም በማብጠልጠል የሚሰድቡና የሚያዋርዱ የወያኔ ቅጥረኛ ባንዳዎች በስራቸው እየተጋለጡ ይገኛሉ።

በዚህ መሠረት በአሁኑ ወቅት ሥራቸውም ሆነ ማንነታቸው በግልጽ ከታወቁት የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) የሙሉ ሰዓት ቅጥረኛ ተሳዳቢ ሰራተኞች ውስጥ በ1ኛ ደረጃ የሚጠቀሰው ኗሪነቱ በእንግሊዝ ሃገር በለንደን ከተማ የሆነው አቶ እንዳለ ወንዳፍራሽ ወይም ራሱን (Endex) እያለ የሚጠራ ግለሰብ ነው። እንዳለ ወንዳፍራሽ ከታች በፎቶው ላይ እንደሚታየው የቅጥረኛ ባንዳነት ሥራውን ለመሸፈን ሲል ሁሌም ኮፊያ፤ ከራሱ ላይ ጥቁር መነጽር ደግሞ ከዓይኑ ላይ አይለይም። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule