• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለዲያስፖራ ኗሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

August 3, 2014 06:28 am by Editor Leave a Comment

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) ለስድብና ለማዋረድ ሥራ በክፍያ ያሰማራቸው ቅጥረኛ ባንዳዎችን እንዋጋ!!

ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ግለሰብ ኢትዮጵያውያንን፤ ድርጅትና፤ ተቋማትን እያሳደዱ እንዲሰድቡና እንዲያዋርዱ ወያኔ አሰልጥኖ ያሰማራቸው ቅጥረኞች ሕዝብን ስይፈሩና ሳያፍሩ የባንዳነት ተግባራቸውን ቀጥለውበት ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ መንግሥት የሚል ስያሜን የያዘው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) እነዚህን ተሳዳቢ ቅጥረኞች ያሰማራው የቻይና መንግሥት የኮሚንስት ፓርቲውን አመራር የሚቃወሙና የሚተቹ ግለሰብና ተቋማትን ለማሸማቀቅ ሲል አቋቁሞት የነበረውን የ50 ሳንቲም ፓርቲ (50 Pence Party) ዘዴን በመውረስ ሲሆን ዓላማውም ለወያኔ የማይመችን ኢትዮጵያዊ ግለሰብ፤ ማህበረሰብንና ተቋምን ሁሉ በመስደብ በማዋረድና በሃሰት ክስ በማሸማቀቅ ቅስሙን ሰብሮ ተገዢ ለማድረግ ነው።

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) ይህንን ከቻይና አገዛዝ የወረሰውን የአዋርደህ ግዛ ዘዴ ሥራ ላይ ለማዋል ያፈለገበትም፤ በሃገር ውስጥ የአገዛዝ ሥርዓቱን የሚቃወሙ፤ ለሥርዓቱ የማይገዙና የማያጎበድዱ ሃገርና ሕዝብ ወዳድ ግለሰቦችና ቡድኖችን  ሁሉ በፌደራል ፖሊስና በደህንነት ኃይል እያነቀ መግረፍ፤ ማሰቃየት፤ ማሰርና ከዛም ካለፈ በመግደል ፀጥ የማድረግ እርምጃው በተጨማሪ ይህንን ለማድረግ በማይችልበት ወቅትና አካባቢ በተለይም ደግሞ በውጪ ሃገር በሚኖረው ኢትዮጵያዊ ላይ ተፈጻሚነት እንዲኖረው በማሰብ ለመሆኑ በየጊዜው የአገዛዝ ሥርዓቱን እየከዱ የሚኮበልሉ ባለሥልጣናት ጭምር ያረጋገጡት ጉዳይ ነው።

በዚህ የአዋርደህና አሸማቀህ ግዛ ዘዴ መሠረትም የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) በተለይ በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ላይ ያነጣጠሩ ዌብ ሳይቶችን፤ ብሎግ እና አያሌ የሶሻል ሚዲያ መድረኮችን በመክፈት አገዛዙ በጠላትነት የፈረጃቸው ግለሰቦች፤ ቡድን እና ተቋማት ላይ የተለያዩ ስብዕናን የሚያረክሱ ስድቦችን፤ የሃሰት ውንጀላዎችንና ክሶችን በማዥጎድጎድ ግለሰብና ተቋማቱ ቅስማቸው ተሰብሮ ፈርተውና ተሸማቀው እንዲኖሩ ለማድረግ  የስድብ ቅጥረኞቹን አስልጥኖ በሕብረተ ሰቡ ውስጥ በማሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ እየከፈላቸው በሙሉ ሰዓት ሰራተኝነት ይህንኑ የስድብና የማዋረድ ተግባራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

እነዚህም በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ውስጥ በመሰግሰግ በኮሚኒቲም ይሁን፤ በፓሊቲካና በሲቪክ ድርጅቶች፤ እንዲሁም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሳይቀር ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ሃቀኛ ኢትዮጵያውያንን ስም በማብጠልጠል የሚሰድቡና የሚያዋርዱ የወያኔ ቅጥረኛ ባንዳዎች በስራቸው እየተጋለጡ ይገኛሉ።

በዚህ መሠረት በአሁኑ ወቅት ሥራቸውም ሆነ ማንነታቸው በግልጽ ከታወቁት የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) የሙሉ ሰዓት ቅጥረኛ ተሳዳቢ ሰራተኞች ውስጥ በ1ኛ ደረጃ የሚጠቀሰው ኗሪነቱ በእንግሊዝ ሃገር በለንደን ከተማ የሆነው አቶ እንዳለ ወንዳፍራሽ ወይም ራሱን (Endex) እያለ የሚጠራ ግለሰብ ነው። እንዳለ ወንዳፍራሽ ከታች በፎቶው ላይ እንደሚታየው የቅጥረኛ ባንዳነት ሥራውን ለመሸፈን ሲል ሁሌም ኮፊያ፤ ከራሱ ላይ ጥቁር መነጽር ደግሞ ከዓይኑ ላይ አይለይም። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule