• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለዲያስፖራ ኗሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

August 3, 2014 06:28 am by Editor Leave a Comment

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) ለስድብና ለማዋረድ ሥራ በክፍያ ያሰማራቸው ቅጥረኛ ባንዳዎችን እንዋጋ!!

ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ግለሰብ ኢትዮጵያውያንን፤ ድርጅትና፤ ተቋማትን እያሳደዱ እንዲሰድቡና እንዲያዋርዱ ወያኔ አሰልጥኖ ያሰማራቸው ቅጥረኞች ሕዝብን ስይፈሩና ሳያፍሩ የባንዳነት ተግባራቸውን ቀጥለውበት ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ መንግሥት የሚል ስያሜን የያዘው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) እነዚህን ተሳዳቢ ቅጥረኞች ያሰማራው የቻይና መንግሥት የኮሚንስት ፓርቲውን አመራር የሚቃወሙና የሚተቹ ግለሰብና ተቋማትን ለማሸማቀቅ ሲል አቋቁሞት የነበረውን የ50 ሳንቲም ፓርቲ (50 Pence Party) ዘዴን በመውረስ ሲሆን ዓላማውም ለወያኔ የማይመችን ኢትዮጵያዊ ግለሰብ፤ ማህበረሰብንና ተቋምን ሁሉ በመስደብ በማዋረድና በሃሰት ክስ በማሸማቀቅ ቅስሙን ሰብሮ ተገዢ ለማድረግ ነው።

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) ይህንን ከቻይና አገዛዝ የወረሰውን የአዋርደህ ግዛ ዘዴ ሥራ ላይ ለማዋል ያፈለገበትም፤ በሃገር ውስጥ የአገዛዝ ሥርዓቱን የሚቃወሙ፤ ለሥርዓቱ የማይገዙና የማያጎበድዱ ሃገርና ሕዝብ ወዳድ ግለሰቦችና ቡድኖችን  ሁሉ በፌደራል ፖሊስና በደህንነት ኃይል እያነቀ መግረፍ፤ ማሰቃየት፤ ማሰርና ከዛም ካለፈ በመግደል ፀጥ የማድረግ እርምጃው በተጨማሪ ይህንን ለማድረግ በማይችልበት ወቅትና አካባቢ በተለይም ደግሞ በውጪ ሃገር በሚኖረው ኢትዮጵያዊ ላይ ተፈጻሚነት እንዲኖረው በማሰብ ለመሆኑ በየጊዜው የአገዛዝ ሥርዓቱን እየከዱ የሚኮበልሉ ባለሥልጣናት ጭምር ያረጋገጡት ጉዳይ ነው።

በዚህ የአዋርደህና አሸማቀህ ግዛ ዘዴ መሠረትም የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) በተለይ በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ላይ ያነጣጠሩ ዌብ ሳይቶችን፤ ብሎግ እና አያሌ የሶሻል ሚዲያ መድረኮችን በመክፈት አገዛዙ በጠላትነት የፈረጃቸው ግለሰቦች፤ ቡድን እና ተቋማት ላይ የተለያዩ ስብዕናን የሚያረክሱ ስድቦችን፤ የሃሰት ውንጀላዎችንና ክሶችን በማዥጎድጎድ ግለሰብና ተቋማቱ ቅስማቸው ተሰብሮ ፈርተውና ተሸማቀው እንዲኖሩ ለማድረግ  የስድብ ቅጥረኞቹን አስልጥኖ በሕብረተ ሰቡ ውስጥ በማሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ እየከፈላቸው በሙሉ ሰዓት ሰራተኝነት ይህንኑ የስድብና የማዋረድ ተግባራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

እነዚህም በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ውስጥ በመሰግሰግ በኮሚኒቲም ይሁን፤ በፓሊቲካና በሲቪክ ድርጅቶች፤ እንዲሁም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሳይቀር ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ሃቀኛ ኢትዮጵያውያንን ስም በማብጠልጠል የሚሰድቡና የሚያዋርዱ የወያኔ ቅጥረኛ ባንዳዎች በስራቸው እየተጋለጡ ይገኛሉ።

በዚህ መሠረት በአሁኑ ወቅት ሥራቸውም ሆነ ማንነታቸው በግልጽ ከታወቁት የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) የሙሉ ሰዓት ቅጥረኛ ተሳዳቢ ሰራተኞች ውስጥ በ1ኛ ደረጃ የሚጠቀሰው ኗሪነቱ በእንግሊዝ ሃገር በለንደን ከተማ የሆነው አቶ እንዳለ ወንዳፍራሽ ወይም ራሱን (Endex) እያለ የሚጠራ ግለሰብ ነው። እንዳለ ወንዳፍራሽ ከታች በፎቶው ላይ እንደሚታየው የቅጥረኛ ባንዳነት ሥራውን ለመሸፈን ሲል ሁሌም ኮፊያ፤ ከራሱ ላይ ጥቁር መነጽር ደግሞ ከዓይኑ ላይ አይለይም። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)።

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule