• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጉዲፈቻ ስም የህፃናት የውጭ ንግድ

November 28, 2012 06:56 pm by Editor Leave a Comment

የጉዲፈቻ ታሪክ በኢትዮጵያ በባህላዊ መንገድ ሲደረግ የቆየ ነው መቼ እንደተጀመረ በእርግጠኝነት ለማወቅ ባይቻልም በ18 ክፍለ ዘመን በኦሮሞ ብሔረሰብ እንደተጀመረ ይታሰባል። ጉዲፈቻ የሚለው ቃል የመጣው ከኦሮሚኛ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜውም ተፈጥሮዓዊ የወላጅነትና የልጅነት የሥጋ ዝምድና ሳይኖር ከሌላ ሰው አብራክ የተወለደን ልጅ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ጥቅሙን ጠብቆ እንደ አብራክ ክፋይ ልጅ ማሳደግ ማለት ነው። በኢትዮጵያ የጉዲፈቻ ሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1952 ዓ.ም በወጣው የፍትሐብሔር ሕግ ማዕቀፍ ተሰጥቶታል ይህም ሕግ የሕፃኑን መብት የሚያስጠብቅ ሆኖ የተዘጋጀ ነው።

የጉዲፈቻ ዓላማ ከውርስ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የዘር ሃረግን ለመቀጠል፤ የዝምድና ትስስር ለማጠናከር፤ ፖለቲካዊ ሃይማኖታዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ለማግኝት፤ … ጥቂቶቹ ናቸው። ለምሳሌ በሀገራችንም የተለያዩ ጦርነቶች በጎሳዎች መካከል ሲነሱ የአንዱን ጎሳ ልጅ አንዱ ጉዲፈቻ ያደርጋል በዚህም ሰበብ በጎሳዎቹ መካከል ሰላም ይፈጠራል።

በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶች ምክንያት የድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ እየጨመረ መጥቷል። ሀገሮች ለጉዲፈቻ ልጆች ምንጮች የሚሆኑበት ምክንያት በርካታ ናቸው። በሃገራችን እ. ኤ. አ. በ2004 በተደረገ ጥናት ኢትዮጵያ ከቻይና፣ ጓቲማላ፣ ሩሲያና ሶሪያ ቀጥላ በአምስተኛ ደረጃ የጉዲፈቻ ምንጭ ሀገር ለመሆን መብቃቷ ታውቋል። እ. ኤ. አ. በ2006 ላይ የተለያዩ ሀገሮች እየቀነሱ በመምጣታቸው ኢትዮጵያ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። እ. ኤ. አ. በ2010 ደግሞ አብዛኞቹ ሃገሮች በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሳቸው ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሆናለች።

ኢትዮጵያ ውስጥ የጉዲፈቻ መስፋፋት ምክንያት የጉዲፈቻ ኤጀንሲ ማቋቋም ቀላል በመሆኑ ነው።መንግስት ቁጥጥር ለማድረግ የሚያስችለው አሰራር እንደሌለው እና ድርጅቶቹን በቀላሉ አቋቁሞ በአንድ ህፃን ከ20ሺ ዶላር በላይ እየተቀበሉ ሕፃናትን ከሃገር ማጋዛቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ጉዳይ አስፈጻሚ (Case worker) ተብለው በሚጠሩ ቅጥረኛ ሕፃናት መልማዮች እና ከሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅቶች ከጉዲፈቻ ኤጀንሲዎች ጋር በመመሳጠር ሕፃናትን በመስረቅ ለተለያዩ የውጭና የሃገር ውስጥ የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅቶች የሚሸጡ እንዳሉ በስፋት ይነገራል።

የልጆቹ አካላዊ፣ ስነልቦናዊ ደህንነት፣ የወላጆች ሁኔታ ከግምት ባልገባበት የጉዲፈቻ ሂደት ሕፃናትን ከሃገር በማስውጣት ረገድ በተለይ ህጻናትን የሚያሳድጉና ለውጭ ሃገር በማደጐነት የሚያስተላልፉ ድርጅቶች፣ ሕፃናቱን ከየትና በምን ሁኔታ እንዳገኟቸው ቁጥጥር ስለሌለ ህገወጥ ንግዱ ተስፋፍቷል። ለዚህም ነው ኢትዮጵያ በዓለም የጉዲፈቻ ተመራጭ መድረሻም መሆኗ በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ መገናኛ ብዙሃን በተደጋጋሚ የሚዘገበው። ከጉዲፈቻ ጋር በተየያዘ በመንግስትና በጉዲፈቻ ድርጅቶች በኩል ያሉ የፖሊሲዎችና የአፈፃፀም ክፍተቶች በመኖራቸው አሠራሩ “የኢትዮጵያ ዘመናዊ የህጻናት የውጭ ንግድ” የሚል ስም ተሰጥቶታል። ይህንን የመንግስት ቅሌት Nov. 19 2012 አምስተርዳም በተከፈተው አለም አቀፍ የዶክመንታሪ ፊልም ፌስቲቫል ላይ Mercy Mercy የተሰኝው ፊልም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰራውን ህግ ወጥ የህፃናት ንግድ አጋልጦዋል። እየተካሄደ ያለው ልቅ አሠራር የውጭ ሃገር ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች ሳይቀር በሃገራችን የጉዲፈቻ አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶችን በመክፈት እንደፈለጉ እንዲንቀሳቀሱ አስችሏቸዋል።

 ሕፃናትን የሚመለከቱ ውሳኔዎች በሚሰጡበት ጊዜ በሕፃናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 3 ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የሕፃናት ጥቅምና ደህንነት ከማናቸውም ቅድሚያ እንደሚሰጠው፤ የአፍሪካ የሕፃናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 4 ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት ለሕፃናቱ ደህንነት ቅድሚያ መሰጠት እንዳለበት፤ እንዲሁም የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 36 ንዑስ አንቀጽ (2) መሠረት የሕፃናት ደህንነት በቀደምትነት መታሰብ እንዳለበትም ይደነግጋሉ፡፡

በብዙ ሃገሮች ዘንድ ተቀባይነት ያለውና ብዙዎችንም የሚያስማማው የጉዲፈቻ ዝምድና ዓይነት “በግልጽ የሚደረግ የጉዲፈቻ ልጅነት” (Open Adoption) የምንለው ነው፡፡ የልጁ ወይም የልጅቷ ተፈጥሮዓዊ ወላጆች የልጃቸውን የጉዲፈቻ ወላጅ በመምረጥና በመለየት በጉዲፈቻ ከተሰጠው ልጃቸው ጋር ያለው የወላጅነት ዝምድና ሳይቋረጥ እንደቀጠለ የሚቆይ የጉዲፈቻ ዝምድና ዓይነት ነው፡፡ ሌላውና በብዙ አገሮችም ሆነ በብዙ ሰዎች ተቀባይነት የሌለው የጉዲፈቻ ዓይነት “በግልጽ ያልተደረገ የጉዲፈቻ ልጅነት ማለት” (Closed Adoption) ተፈጥሮዓዊ የሆኑ ወላጆች ራሳቸውን በመደበቅ ወይም ወላጅነታቸውን በመሰወር የጉዲፈቻ አድራጊ ለሆነው ሰው (አሳዳሪ) በጉዲፈቻ የተሰጠውን ልጅ በመልቀቅ የወላጅነት መብታቸውን የሚያጡበት ነው፡፡

ከእነዚህ ሁለት የጉዲፈቻ የዝምድና ዓይነቶች አገራችን የመጀመሪያውን ማለትም “በግልጽ የሚደረግ የጉዲፈቻ የዝምድናን” ዓይነት እንደመረጠች ከቤተሰብ ሕጉ የተለያዩ ድንጋጌዎች እንረዳለን፡፡ በወረቀት ላይ የሠፈረው አካሄድ ይህን የሚመስል ቢሆንም በሃገራችን የሚደረገው የጉዲፈቻ ሂደት የጉዲፈቻ አድራጊውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው፡፡ በመረጃ ደረጃ ከሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ጋር ተመሳጥረው ልጆቹ ሲላኩም ምንም ዓይነት የመገናኛ ዘዴ እንዳይኖር ተደርጎ የሚላኩበት ሁኔታም አለ፡፡ በአብዛኛው ጉዲፈቻ አድራጊ ወላጆቻቸው እያሉ የሞቱ መሆኑን እያስመሰከሩ የሚልኩና ጥቅም እንደሚያገኙ ነው፡፡

መንግሥት የመጨረሻ አማራጫቸው ይሄ ነው ብሎ ከሌላ ሀገር ለመጣ ዜጋ በማሳደጊያ ያሉትን ልጆች በሕጋዊ መንገድ ወስዶ የሚያሳድግበት አካሄድ ነው። ሕፃናቱ በሄዱበት አገር ተመችቷቸዋል ወይስ አልተመቻቸውም የሚለውንና የማንነት ችግር እንዳያጋጥማቸው መንግስት መከታተል ሲገባው ህጻናቱ ለአሳዛኝ ድርጊቶች እየተዳረጉ ይገኛሉ፡፡ በተሰጣቸው የተሳሳተ መረጃ በግልፅ ባልተረዱት አሠራር ልጆቻቸውን በጉዲፈቻ ሰጥተው ስለ ልጆቻቸው አንዳችም ነገር ማወቅ ያቃታቸው ኢትዮጵያውያን ወላጆች በርካታ ናቸው፡፡ በዚህ መልኩ በጨቅላነታቸው ወደ ውጭ ሄደው ከማንነት ጥያቄ ባሻገር ለከባድ ሥነልቦናዊና አካላዊ ጉዳት የተጋለጡ ልጆች ቁጥርም ጥቂት አይደለም፡፡ በፈረንሣውያን ባልና ሚስት የሁለት ዓመትና የአራት ዓመት ወንድ ልጆች ሊያሳድጉ ከኢትዮጵያ በወሰዱ ማግስት ነበር በአሳዳጊያቸው የተደፈሩት፡፡ ኢትዮጵያዊቷ ሀና ዊልያምስን አሜሪካ ውስጥ በምግብ እጥረት ሕይወቷ አልፏል፡፡ አምስት ኢትዮጵያዊያን ሴት ልጆች በአሳዳጊያቸው የመደፈራቸው ዜና መዘገቡም ይታወሳል፡፡ የማንነት ቀውስ ለአንድ ሕፃን ልጅ የመጨረሻው መጥፎ ክስተት ነው።

መንግሥት ጉዲፈቻን እንደማያበረታታ ይናገራል፡፡ የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ሚኒስቴር በጉዲፈቻ የሚሄዱ ሕፃናትን ጉዳይ በተመለከተ በቀን ከሀምሳ በላይ የሚሆኑ ማመልከቻዎችን  እንደሚያስተናግድ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ሆኖም ምዕራባዊ የዜና አውታሮች በማስረጃ እንደሚዘግቡት በአሜሪካ በጉዲፈቻነት ልጅ ከሚደረጉ አምስት ህጻናት መካከል አንዱ ከኢትዮጵያ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ በአሜሪካ ብቻ እ.ኤ.አ. በ2004 በጉዲፈቻነት ከኢትዮጵያ የሚመጡት ህጻናት ቁጥር በ2010ዓም በሦስት እጥፍ ያደገ ሲሆን ይህም አገራችንን ከቻይና ቀጥሎ ሁለተኛ አድርጓታል፡፡

ሔለን ዘውዱ አየለ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule