• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተማሪዎች ዓመጽና የየአካባቢው አጫጭር መረጃዎች

December 12, 2017 08:44 pm by Editor Leave a Comment

አክሱም ዩኒቨርሲቲ

አክሱም ዩኒቨርሲቲ በየግማሽ ቀኑ ሲነሳና ሲበርድ ነው የሰነበተው። በካፌ ሰዓት ብዙ ጊዜ ድንጋይ ይወረወራል። ማምሻውን በራት ሰዓት በተፈጠረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠው ወደ ቤተሰቦቻቸው ቢሔዱም እስካሁን መውጣት የሚፈልጉ ከሁለት ሺህ በላይ የዐማራ ተማሪዎች አሉ።


አዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ዛሬ ጠዋት በነበረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በአዲግራት እስካሁን የተረጋገጠ 9 ያክል ተማሪዎች ሕይወት ጠፍቷል፣ በርካቶች ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ወደ 30 የሚጠጉ የአማራ ተወላጆች በአዲግራት የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች ታስረው ቶርች ተደርገዋል፤ እስካሁንም አልተፈቱም። ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሔድ ቢፈልጉም አልተቻለም። ገዳም እንገባለን ብለው የወጡ ተማሪዎችም የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል።


መቀሌ ዩኒቨርሲቲ

በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ግቢ ማምሻው ግጭት እንደተፈጠረ መረጃዎች ቢወጡም ዝርዝር ማግኘት አልተቻለም። ዘግይቶ በመጣ መረጃ ደግሞ ግቢው ውስጥ ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶ መብራት ጠፍቶ የተማሪዎች ጩኸትና ለቅሦ እንደሚሰማ ነው የገለጹልን።

(ተጨማሪ፤ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ግቢ ማምሻውን እንዳልከው ከባድ የፍንዳታ ድምፅ ተሠምቶ መብራት ተማሪዎቹ መጮህ እንደጀመሩና ወዲያው የፌዴራል ፖሊሥ ጊቢው ውስጥ መግባቱን ዶርማቸው ውስጥ ሆነው ያዩ ልጆች ነግረውኛል። ይሄንን ስፅፍ በድጋሚ በሜሴጅ በላኩልኝ መልእክት መብራቱ አልመጣም ግቢው ግን መረጋጋቱን ነግረውኛል ። Abate Azagae)


ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

ትናንት በማራኪ ካምፓስ ተማሪዎች ሰላማዊ ተቃውሞ ጀምረው ነበር፤ “አዲግራት ያሉ ወንድሞቻችን ላይ የሚደርሰው ጭፍጨፋ ይቁም!” “የዐማራ ደም መፍሰስ ይቁም!” ወዘተ የሚሉ ተቃውሞዎች በማራኪና ቴዎድሮስ ካምፓሶች ቀጥለው ከሕዝብ ጋር ሊደባለቁ ሲል በአጋዚ ከግቢ እንዳይወጡ ተደርገዋል። ዛሬም ከሆስፒታሉ ውጭ በሁሉም ካምፓሶች ተቃውሞዎች ቀጥለው ነበር፤ ነገር ግን የጠዳው ግቢ የአጋዚ ወታደሮች ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል። በጥይት የተገደሉ ተማሪዎች ሁሉ እንዳሉ ነው የተገለጸው።


ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ

ትናንት ሌሊት በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የነበረውን የዐማራ ጭፍጨፋ በማውገዝ የተጀመረው ተቃውሞ የትምህርት መማር ማስተማር ሒደቱን ሙሉ በሙሉ አቋርጦታል። ከአዲግራት የተገደለ አንድ ልጅ አስከሬን የሚመጣ አለ መባሉ የበለጠ ችግሩን አባብሶታል። አጋዚ ወደ ግቢው መግባቱንም ሰምተናል።


ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

ጠዋት ዘንዘሊማ ኮሌጅ የጀመረው ተቃውሞ ግማሽ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፖሊን፣ ፔዳንና ይባብ ኮሌጆችን ጭምር አዳርሷል። የትግራይ ተማሪዎች አዲስ ዓምባ የተባለ ባለሦስት ኮከብ ሆቴል ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገላቸው ሲሆን የፌደራል ፖሊስና አጋዚ ቀሪ ተማሪዎችን እያሰረ ነው። ምሽት ላይ ፖሊ ግቢ መጠነኛ ቃጠሎ ደርሶ ወዲያውኑ ጠፍቷል።


ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

በደብረ ማርቆስ ማምሻውን ነው የተማሪዎች ተቃውሞ የጀመረው። ሆኖም በዝግጅት ሲጠባበቅ የነበረው የፌደራል ፖሊስና አጋዚ በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል ተብሏል።


ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ

በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው ተቃውሞ እስካሁን አልበረደም። የትግራይ ተማሪዎች በወልዲያ ስታዲየም ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው፤ ከዩኒቨርሲቲው በመከላከያና ፌደራል ፖሊስ ነው ተመርጠው የወጡት። ሌሊት አንድ ሕንጻ በእሳት ጉዳት ደርሶበታል። በወልዲያ ትምህርት ቤቶችም ዝግ ሆነው ውለዋል።

ዛሬ ደግሞ በዩኒቨርሲቲው መርሣ ካምፓስ አዲስ ተቃውሞ ጀምሯል።


ውጫሌ ውርጌሳ

በውጫሌና ውርጌሳ የተጀመረው ተቃውሞ ትናንት ነው። “ልጆቻችን ሳይመለሱ ወደ መሀል አገር ወይም ከመሀል አገር ወደ ትግራይ የሚሔድ መኪና መኖር የለበትም” በሚል ነው ተቃውሞው የተነሳው። አንድ ልጅ ከአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተገደለ አለ መባሉ የበለጠ ጉዳዩን አወሳስቦታል። ጥቂት መኪናዎች ተቃጥለዋል። የሰላም ባስ ተሰባብሯል።

ትምህርት ቤቶች ዝግ ሆነው ውለዋል።

ሙሉቀን ተስፋው (Muluken Tesfaw)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule