• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተማሪዎች ዓመጽና የየአካባቢው አጫጭር መረጃዎች

December 12, 2017 08:44 pm by Editor Leave a Comment

አክሱም ዩኒቨርሲቲ

አክሱም ዩኒቨርሲቲ በየግማሽ ቀኑ ሲነሳና ሲበርድ ነው የሰነበተው። በካፌ ሰዓት ብዙ ጊዜ ድንጋይ ይወረወራል። ማምሻውን በራት ሰዓት በተፈጠረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠው ወደ ቤተሰቦቻቸው ቢሔዱም እስካሁን መውጣት የሚፈልጉ ከሁለት ሺህ በላይ የዐማራ ተማሪዎች አሉ።


አዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ዛሬ ጠዋት በነበረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በአዲግራት እስካሁን የተረጋገጠ 9 ያክል ተማሪዎች ሕይወት ጠፍቷል፣ በርካቶች ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ወደ 30 የሚጠጉ የአማራ ተወላጆች በአዲግራት የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች ታስረው ቶርች ተደርገዋል፤ እስካሁንም አልተፈቱም። ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሔድ ቢፈልጉም አልተቻለም። ገዳም እንገባለን ብለው የወጡ ተማሪዎችም የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል።


መቀሌ ዩኒቨርሲቲ

በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ግቢ ማምሻው ግጭት እንደተፈጠረ መረጃዎች ቢወጡም ዝርዝር ማግኘት አልተቻለም። ዘግይቶ በመጣ መረጃ ደግሞ ግቢው ውስጥ ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶ መብራት ጠፍቶ የተማሪዎች ጩኸትና ለቅሦ እንደሚሰማ ነው የገለጹልን።

(ተጨማሪ፤ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ግቢ ማምሻውን እንዳልከው ከባድ የፍንዳታ ድምፅ ተሠምቶ መብራት ተማሪዎቹ መጮህ እንደጀመሩና ወዲያው የፌዴራል ፖሊሥ ጊቢው ውስጥ መግባቱን ዶርማቸው ውስጥ ሆነው ያዩ ልጆች ነግረውኛል። ይሄንን ስፅፍ በድጋሚ በሜሴጅ በላኩልኝ መልእክት መብራቱ አልመጣም ግቢው ግን መረጋጋቱን ነግረውኛል ። Abate Azagae)


ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

ትናንት በማራኪ ካምፓስ ተማሪዎች ሰላማዊ ተቃውሞ ጀምረው ነበር፤ “አዲግራት ያሉ ወንድሞቻችን ላይ የሚደርሰው ጭፍጨፋ ይቁም!” “የዐማራ ደም መፍሰስ ይቁም!” ወዘተ የሚሉ ተቃውሞዎች በማራኪና ቴዎድሮስ ካምፓሶች ቀጥለው ከሕዝብ ጋር ሊደባለቁ ሲል በአጋዚ ከግቢ እንዳይወጡ ተደርገዋል። ዛሬም ከሆስፒታሉ ውጭ በሁሉም ካምፓሶች ተቃውሞዎች ቀጥለው ነበር፤ ነገር ግን የጠዳው ግቢ የአጋዚ ወታደሮች ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል። በጥይት የተገደሉ ተማሪዎች ሁሉ እንዳሉ ነው የተገለጸው።


ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ

ትናንት ሌሊት በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የነበረውን የዐማራ ጭፍጨፋ በማውገዝ የተጀመረው ተቃውሞ የትምህርት መማር ማስተማር ሒደቱን ሙሉ በሙሉ አቋርጦታል። ከአዲግራት የተገደለ አንድ ልጅ አስከሬን የሚመጣ አለ መባሉ የበለጠ ችግሩን አባብሶታል። አጋዚ ወደ ግቢው መግባቱንም ሰምተናል።


ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

ጠዋት ዘንዘሊማ ኮሌጅ የጀመረው ተቃውሞ ግማሽ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፖሊን፣ ፔዳንና ይባብ ኮሌጆችን ጭምር አዳርሷል። የትግራይ ተማሪዎች አዲስ ዓምባ የተባለ ባለሦስት ኮከብ ሆቴል ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገላቸው ሲሆን የፌደራል ፖሊስና አጋዚ ቀሪ ተማሪዎችን እያሰረ ነው። ምሽት ላይ ፖሊ ግቢ መጠነኛ ቃጠሎ ደርሶ ወዲያውኑ ጠፍቷል።


ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

በደብረ ማርቆስ ማምሻውን ነው የተማሪዎች ተቃውሞ የጀመረው። ሆኖም በዝግጅት ሲጠባበቅ የነበረው የፌደራል ፖሊስና አጋዚ በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል ተብሏል።


ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ

በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው ተቃውሞ እስካሁን አልበረደም። የትግራይ ተማሪዎች በወልዲያ ስታዲየም ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው፤ ከዩኒቨርሲቲው በመከላከያና ፌደራል ፖሊስ ነው ተመርጠው የወጡት። ሌሊት አንድ ሕንጻ በእሳት ጉዳት ደርሶበታል። በወልዲያ ትምህርት ቤቶችም ዝግ ሆነው ውለዋል።

ዛሬ ደግሞ በዩኒቨርሲቲው መርሣ ካምፓስ አዲስ ተቃውሞ ጀምሯል።


ውጫሌ ውርጌሳ

በውጫሌና ውርጌሳ የተጀመረው ተቃውሞ ትናንት ነው። “ልጆቻችን ሳይመለሱ ወደ መሀል አገር ወይም ከመሀል አገር ወደ ትግራይ የሚሔድ መኪና መኖር የለበትም” በሚል ነው ተቃውሞው የተነሳው። አንድ ልጅ ከአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተገደለ አለ መባሉ የበለጠ ጉዳዩን አወሳስቦታል። ጥቂት መኪናዎች ተቃጥለዋል። የሰላም ባስ ተሰባብሯል።

ትምህርት ቤቶች ዝግ ሆነው ውለዋል።

ሙሉቀን ተስፋው (Muluken Tesfaw)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule