• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ፡ ሽምግልና ለምኔ?

September 22, 2016 01:44 am by Editor 2 Comments

ኢትዮጵያ ካለችበት ወቅታዊ ችግሮች ለመውጣት ሽምግልናን እንደ መፍትሄ አድርጋ መውሰድ ትችላለች ወይ? እስቲ ይህንን ሀሳብ በተመለከተ ጉዳዩን ከሁሉም አቅጣጫ ረጋ ብለን እንመልከት።

ከኢህአዴግ አንዳንዶች አንድ ምርጫ ብቻ እንዳለ ሊያስቀምጡ የፈለጉ ይመስላል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሲሆን ፀጥ ለጥ አሰኝቶ መግዛት አሊያም በሃይልም ቢሆን መግዛት እንችላለን ብለው የሚያምኑ እስኪመስል ድረስ ሃይልንም ሲጠቀሙ ይታያል። በተቃዋሚ ጎራ ያሉ አንዳንዶች ደግሞ በተመሳሳይ መልኩ አንድ ምርጫ ብቻ እንዳለ አድርገው ያስቀምጣሉ። ያም የሚያስከትለውን ዋጋ ከፍሎና  በአመፅ አብዮት አካሄዶ መንግስትን መገልበጥ ነው እንጂ መነጋገር የትም አያደርስም ብለው ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ።

እና ምን ይሻላል? ተያይዞ ገደል መግባት ወይስ አውጥቶ አውርዶ፥ ከሁለቱም ተቃራኒ አስተሳስብ ይልቅ ሌላኛ ሶስተኛ አስተሳሰብ አለ ብለን መንግስትንና የተቃዋሚ አካላትን መሞገት?

የኢትዮጵያ ሕዝብ በመቻቻልና በመተሳስብ አብሮ የኖረ ሕዝብ ነው። ያልታደለው እኩልነትን አንግሶ በፍቅር የሚያያይዘውና አንድ የሚያደርገው አስተዳደር እስካሁን አለመገኘቱ ነው። ፈሪሃ ፈጣሪን የተላበሰው ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ በእውነት ላይ የተመሰረተ ጥል ሆነ ጥላቻ አንዱ በሌላው ላይ የለውም። መሪዎች እንደ ሕዝቡ ቅን ሆነው እኩልነትና ፍቅርን ቢዘሩ የሚታጨደው የፍቅር አዝመራ የሚያስጎመጅ በሆነ ነበር።

የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ህብረ ብሔር በሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማንነት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በመሪዎች የስህተት አካሄድ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል። ስለሆነም መንግስት በተቀዳሚነት ለዚህ ስጋት ሃላፊነትን ራሱ መውሰድ ይገባዋል። ራሱንም ተጠያቂ ካደረገ በኋላ፥ ወደዚያ ጥፋት ከሚመራው የሃይል እርምጃ ታቅቦ ኢትዮጵያን ለማዳን ውይይትና መግባባትን እንደ ብቸኛ አማራጭ በመውሰድ አማራጭ ሃይሎችን ለሰላሙ ጉዞ መጋበዝ ይኖርበታል።

አብዮት ላለፉት አራት አስርተ አመታት ያተረፈልንን እያየነው ነው። ችግርን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ለዛሬና ለወደፊቱ ፍቱን መድሃኒት ነው። አብዮት የዛሬን ችግር ፈቶ ሲያበቃ የነገውን ችግር ይወልዳል። መንግስት ጊዜ ሊገዛ ፈልጎ የውሸት ሽምግልና ቢመርጥ ያንን ውድቅ ማድረግ ያባት ነው። አለበለዚያ ግን በጭፍን ሽምግልና ዋጋ የለውም ማለት ከማስተዋል ሃላፊነት መጉደል ይሆንብናል።

ሽምግልና ይሰራል አይሰራም ሳይሆን ጥያቄው፥ የትኛው ሽምግልና ይሰራል ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል። ሁለት አይነት የሽምግልና አካሄድ ሊኖር ይችላል። አንድም አድሏዊ የሆነ ከሃይለኛው ጋር የወገነ የይስሙላ ሽምግልና ሲሆን ሌላኛው ደግሞ፥ አድሏዊ ያልሆነ ከማንም ያልወገነና እውነተኛ ሽምግልና ነው። በርግጥ የይስሙላ ሽምግልና ምንም ፋይዳ ላይሰጥ ይችላል። ነገር ግን ለእውነተኛው ሽምግልና እድል ተሰጥቶት ኢትዮጵያ ካለችበት አጣብቂኝ እንድትወጣ ድልድይ ቢሰራ ሀገራችን ዘላቂ ሰላም ይሰፍንባታል።

የዚህ እውነተኛ ሽምግልና ግብና ዓላማ የሚያዛልቀው ሶስተኛው (ሌላኛው) መንገድ፥ በውይይትና በመግባባት አገሪቱን በሰላማዊ መንገድ ወደ ዘላቂ ዲሞክራሲ ፍትህ እኩልነትና ዕድገት የሚያመራውን ሂደት ለመፍጠር ሁኔታዎችን የሚያመቻች ነው። ዞሮ ዞሮ ይህን ዓላማና ግብ ሁላችንም የምንፈልገው ነው።

እግዚብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Takele says

    September 26, 2016 04:13 pm at 4:13 pm

    Well done brother , that is why peace and justice for Africa is trying to do its best . Let us unite , talk , discuss the problem and come to the table with a clean heart and bright mind . All sides have to restrain from where they were and say byegones be byegones . In order to make this happen the government, opposition parties , elderlies , religious leaders , and concerned fellow Ethiopians like you have to pay serious attention and cooperate with PJA ( Peace and Justice for Africa ) to make it real . The current Ethiopian situation is going from bad to worst and our beloved country is on the sharp edge of the cliff . We all wish if our naturally beautiful country go in the right direction and become one of the best democratic and prosperous country in the world . please , please citizens and friends of Ethiopia let us change this worst atmospher and make our country comfortable for everyone of us to live .

    Reply
  2. Alewa Geremew says

    October 5, 2016 03:42 am at 3:42 am

    Selam Dr. Zelalem,

    It is not time to split hair. The premise that TPLF will participate in a genuine reconciliation is wrong. I know you very well and you are a very intelligent person even when we were in college.
    Over the years, I noticed when your posting shows up. I am not sure it is intentional but most of the time you choose the wrong time.

    Dr. Zelalem, I recall how you were devastated when you lost loved ones. So please do not make a trivial argument when people of Ethiopia is mourning.

    Thousands of Amhara, Oromo, Konso, Benshangul, and many other ethnic groups have been massacred by the regime. The Ethiopian people have to get rid off this terrorist government.
    What you are preaching is exactly what these fascists are looking for to buy time.

    My heart is broken when the woman in Wollega was forced to sit on her son’s dead body and beg for mercy to save her daughter. I am heart broken when millions show up for thanksgiving and massacred! I don’t have to be an Oromo to feel the pain. The genocide in Amhara region is beyond belief.

    Victory to Ethiopian People!

    Take care Brother!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule