• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌዴሬሽን በአውሮፓ፣ ሮም ላይ ተዘርፏል?

October 17, 2017 01:50 pm by Editor 2 Comments

  • በአምስተርዳም ከተማ የተካሄደው አመታዊው የቦርድ አባላት ስብሰባ ጥያቄውን ይመልሳል

ካለፈው ኦገስት ወር ጀምሮ እጅግ ተጋንኖ ሲወራ የነበረ ጉዳይ ነው። ፌዴሬሽኑ ሮም ላይ ተዘርፏል። ይህንን “ዝርፍያ” ልዩ ያደረገው በቅንብር እና በጥናት የተሰራ ነው የሚሉት ጥቂት አልነበሩም። ከውጭ የሚወራው እና የሚጻፈው ነገር ብዙ ነው። ፌዴሬሽኑ እንዴት እና ለምን ተዘረፈ? የሚለው ጥያቄ ግን ምላሹ ከመላ ምት ያላለፈ አልነበረም። ቅዳሜ፣ 14 ኦክቶበር 2017 በአምስተርዳም ከተማ የተካሄደው አመታዊው የቦርድ አባላት ስብሰባ ይህንን እንቆቅልሽ የፈታው ይመስላል። በእለቱ ከሳሽ እና ተከሳሽ  በተገኙበት፤ ጉዳዩን በግልጽ ለመወያየት ተችሎ ነበር። ካሜራችን ሂደቱን በድምጽና ምስል ይዞታል። (ቪድዮውን ይመልከቱ Part 1)

የኢትዮጵያውያን ስፖርት እና ባህል ፌዴሬሽን በአውሮፓ (ኢ.ስ.ካ.ፌ) ባለፈው ቅዳሜ፣ 14 ኦክቶበር 2017 አመታዊውን የቦርድ ስብሰባ  በአምስተርዳም ከተማ  አድርጎ ነበር። ከ 21 ክለቦች የተውጣጡ 45 አባላት የተሳተፉበት ይህ ስብሰባ አራት አጀንዳዎች ላይ የተወያየ ሲሆን፣ አንድ ቀን ከፈጀው ከዚህ ውይይት በኋላ አዲስ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መርጧል። በ2018 እና 2019 አዘጋጅ ሃገሮችም ታውቀዋል። በዚህም መሰረት በ2018 ስቱትጋርት – በ 2019 ደግሞ ዙሪክ በክለብ ደረጃ ፌስቲቫሉን ከዘጋጁ በኋላ – የማዘጋጀቱን ሃላፊነት ፌዴሬሽኑ መልሶ ይወስዳል። ላለፉት ሁለት አመታት በሆላንድ እና በሮም በፌዴሬሽኑ ሃላፊነት የተካሄዱት ዝግጅቶች እንደተጠበቀው ውጤታማ ባለመሆናቸው ለመጭው ሁለት አመት የአዘጋጅነቱን ሃላፊነት አዘጋጅ ሃገር ክለቦች እንዲወስዱ ጉባኤው ወስኗል። የ2017ቱ የሮማ ዝግጅት ብዙ አወዛጋቢ ነገሮች ነበሩበት።

ከዝግጅቱ በኋላ የተወሰኑ ግለሰቦች የተሰራበትን ገንዘብ ይዘው መጥፋታቸው በስፋት ሲወራ መሰንበቱ ይታወሳል።  የፌዴሬሽኑ አመራር አባላት፣ ዮሃንስ መሰለ፣ ግርማ ሳህሌ፣ ከበደ ሃይሌ እና ኢብራሂም ገንዘቡ እንዴት እንደተወሰደ እና እነሱም ሊደርስ ከነበረው ችግር እንዴት እንዳመለጡ ተናግረዋል። በወቅቱ በዚያ ስፍራ የነበረው ጥሩ ያልሆነ ድባብ እና ወሬ የነበረው አማራጭ ስፍራውን ለቅቆ ማምለጥ እንደነበር ቢገልጹም፣ ያረፉበት ሆቴል ጭምር ያልታሰቡ ክስተቶችን ተጋፍጠዋል። ሆቴል የክፍላቸው በማስተር ቁልፍ  እንደበረበሩባቸውም ተናግረዋል።

የዝግጅቱ አስተባባሪ ከነበሩት ውስጥ አንድነት (ቀዮ) እና ፍራንሲስኮ በአምስተርዳም ተገኝተው በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። የተባለውን ገንዘብ መውሰዱን ቀዮ ያመነ ሲሆን፣ ለዚህ ድርጊትም ምክንያት እንዳለው ይገልጻል።

ጉባኤው በአጀንዳው ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ በፌዴሬሽኑ እና በእነ ፍራንሲስኮ የቀረቡትን የፋይናንስ ዘገባ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ወስኗል። ከጣልያን ሮቤርቶ፣ ከሆላንድ ክንፉ አሰፋ እና ከኮለን ተስፋዬ ጉዳዩን መርምረው ለአጠቃላይ ጉባኤ እንዲያቀርቡ ተመርጠዋል።

ውድ ግዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ክህሎታቸውን እና ገንዘባቸውን በነጻ ሲያፈስሱ የቆዩ የአመራር አባላት ሃላፊነታቸውን በጨዋነት አስረክበዋል። እጅግ አስቸጋሪ ጉዞ እንደተጓዙ ግልጽ ቢሆንም ትእግስታቸው ግን የሚደነቅ ነበር። ጉባኤውም የቀድሞውን አመራር አባላት በከፍተኛ ምስጋና ካሰናበታቸው በኋላ 9 አባላት ያሉበት አዲስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መርጧል። አዲሶቹ የአመራር አባላት የሚከተሉት ናቸው።

  • አሳዬ ከኖርዌይ (ሊቀ መንበር)
  • ነቢዩ ሰቆጣው ከፍራንክፈርት
  • ተስፋዬ ከኮለን (ዋና ጸሃፊ)
  • ዳናኤል ከስዊዝ
  • አፈወርቅ አዘበርሊን
  • መስፍን  ከስቱትጋርት
  • ፋሲል ከካታንጋ – ለንደን
  • ሮቤርቶ ከሮማ
  • ቴዲ ከቤልጅየም
  • ብርሃኑ ክስዊድን (ገንዘብ ያዥ)

ቪድዮውን እዚህ ላይ ይመልከቱ

ክንፉ አሰፋ (ፎቶዎች በጸሃፊው የተላኩ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. ጎፋ says

    October 28, 2017 06:56 pm at 6:56 pm

    መቼ ይሆን እኛ ኢትዮጵያውያኖች በሃሳብ ተስማምተን ዓላማችንን የምናሳካው? አገር ቤት በወያኔ እናሳብባለን ውጭሳ በማን ሊሆን ይሆን? ብንተባበር። ወያኔ ክጥፌም አታልፍም ነበር።

    Reply
  2. cute-ehapa says

    November 8, 2017 01:51 am at 1:51 am

    These group of money grabbing ‘worrobelas’ don’t deserve to have their ‘meeting’ reported. Believe you me these are scums that are an embarrassment to diaspora. I know because I live in London!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule