• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌዴሬሽን በአውሮፓ፣ ሮም ላይ ተዘርፏል?

October 17, 2017 01:50 pm by Editor 2 Comments

  • በአምስተርዳም ከተማ የተካሄደው አመታዊው የቦርድ አባላት ስብሰባ ጥያቄውን ይመልሳል

ካለፈው ኦገስት ወር ጀምሮ እጅግ ተጋንኖ ሲወራ የነበረ ጉዳይ ነው። ፌዴሬሽኑ ሮም ላይ ተዘርፏል። ይህንን “ዝርፍያ” ልዩ ያደረገው በቅንብር እና በጥናት የተሰራ ነው የሚሉት ጥቂት አልነበሩም። ከውጭ የሚወራው እና የሚጻፈው ነገር ብዙ ነው። ፌዴሬሽኑ እንዴት እና ለምን ተዘረፈ? የሚለው ጥያቄ ግን ምላሹ ከመላ ምት ያላለፈ አልነበረም። ቅዳሜ፣ 14 ኦክቶበር 2017 በአምስተርዳም ከተማ የተካሄደው አመታዊው የቦርድ አባላት ስብሰባ ይህንን እንቆቅልሽ የፈታው ይመስላል። በእለቱ ከሳሽ እና ተከሳሽ  በተገኙበት፤ ጉዳዩን በግልጽ ለመወያየት ተችሎ ነበር። ካሜራችን ሂደቱን በድምጽና ምስል ይዞታል። (ቪድዮውን ይመልከቱ Part 1)

የኢትዮጵያውያን ስፖርት እና ባህል ፌዴሬሽን በአውሮፓ (ኢ.ስ.ካ.ፌ) ባለፈው ቅዳሜ፣ 14 ኦክቶበር 2017 አመታዊውን የቦርድ ስብሰባ  በአምስተርዳም ከተማ  አድርጎ ነበር። ከ 21 ክለቦች የተውጣጡ 45 አባላት የተሳተፉበት ይህ ስብሰባ አራት አጀንዳዎች ላይ የተወያየ ሲሆን፣ አንድ ቀን ከፈጀው ከዚህ ውይይት በኋላ አዲስ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መርጧል። በ2018 እና 2019 አዘጋጅ ሃገሮችም ታውቀዋል። በዚህም መሰረት በ2018 ስቱትጋርት – በ 2019 ደግሞ ዙሪክ በክለብ ደረጃ ፌስቲቫሉን ከዘጋጁ በኋላ – የማዘጋጀቱን ሃላፊነት ፌዴሬሽኑ መልሶ ይወስዳል። ላለፉት ሁለት አመታት በሆላንድ እና በሮም በፌዴሬሽኑ ሃላፊነት የተካሄዱት ዝግጅቶች እንደተጠበቀው ውጤታማ ባለመሆናቸው ለመጭው ሁለት አመት የአዘጋጅነቱን ሃላፊነት አዘጋጅ ሃገር ክለቦች እንዲወስዱ ጉባኤው ወስኗል። የ2017ቱ የሮማ ዝግጅት ብዙ አወዛጋቢ ነገሮች ነበሩበት።

ከዝግጅቱ በኋላ የተወሰኑ ግለሰቦች የተሰራበትን ገንዘብ ይዘው መጥፋታቸው በስፋት ሲወራ መሰንበቱ ይታወሳል።  የፌዴሬሽኑ አመራር አባላት፣ ዮሃንስ መሰለ፣ ግርማ ሳህሌ፣ ከበደ ሃይሌ እና ኢብራሂም ገንዘቡ እንዴት እንደተወሰደ እና እነሱም ሊደርስ ከነበረው ችግር እንዴት እንዳመለጡ ተናግረዋል። በወቅቱ በዚያ ስፍራ የነበረው ጥሩ ያልሆነ ድባብ እና ወሬ የነበረው አማራጭ ስፍራውን ለቅቆ ማምለጥ እንደነበር ቢገልጹም፣ ያረፉበት ሆቴል ጭምር ያልታሰቡ ክስተቶችን ተጋፍጠዋል። ሆቴል የክፍላቸው በማስተር ቁልፍ  እንደበረበሩባቸውም ተናግረዋል።

የዝግጅቱ አስተባባሪ ከነበሩት ውስጥ አንድነት (ቀዮ) እና ፍራንሲስኮ በአምስተርዳም ተገኝተው በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። የተባለውን ገንዘብ መውሰዱን ቀዮ ያመነ ሲሆን፣ ለዚህ ድርጊትም ምክንያት እንዳለው ይገልጻል።

ጉባኤው በአጀንዳው ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ በፌዴሬሽኑ እና በእነ ፍራንሲስኮ የቀረቡትን የፋይናንስ ዘገባ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ወስኗል። ከጣልያን ሮቤርቶ፣ ከሆላንድ ክንፉ አሰፋ እና ከኮለን ተስፋዬ ጉዳዩን መርምረው ለአጠቃላይ ጉባኤ እንዲያቀርቡ ተመርጠዋል።

ውድ ግዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ክህሎታቸውን እና ገንዘባቸውን በነጻ ሲያፈስሱ የቆዩ የአመራር አባላት ሃላፊነታቸውን በጨዋነት አስረክበዋል። እጅግ አስቸጋሪ ጉዞ እንደተጓዙ ግልጽ ቢሆንም ትእግስታቸው ግን የሚደነቅ ነበር። ጉባኤውም የቀድሞውን አመራር አባላት በከፍተኛ ምስጋና ካሰናበታቸው በኋላ 9 አባላት ያሉበት አዲስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መርጧል። አዲሶቹ የአመራር አባላት የሚከተሉት ናቸው።

  • አሳዬ ከኖርዌይ (ሊቀ መንበር)
  • ነቢዩ ሰቆጣው ከፍራንክፈርት
  • ተስፋዬ ከኮለን (ዋና ጸሃፊ)
  • ዳናኤል ከስዊዝ
  • አፈወርቅ አዘበርሊን
  • መስፍን  ከስቱትጋርት
  • ፋሲል ከካታንጋ – ለንደን
  • ሮቤርቶ ከሮማ
  • ቴዲ ከቤልጅየም
  • ብርሃኑ ክስዊድን (ገንዘብ ያዥ)

ቪድዮውን እዚህ ላይ ይመልከቱ

ክንፉ አሰፋ (ፎቶዎች በጸሃፊው የተላኩ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. ጎፋ says

    October 28, 2017 06:56 pm at 6:56 pm

    መቼ ይሆን እኛ ኢትዮጵያውያኖች በሃሳብ ተስማምተን ዓላማችንን የምናሳካው? አገር ቤት በወያኔ እናሳብባለን ውጭሳ በማን ሊሆን ይሆን? ብንተባበር። ወያኔ ክጥፌም አታልፍም ነበር።

    Reply
  2. cute-ehapa says

    November 8, 2017 01:51 am at 1:51 am

    These group of money grabbing ‘worrobelas’ don’t deserve to have their ‘meeting’ reported. Believe you me these are scums that are an embarrassment to diaspora. I know because I live in London!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule