• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌዴሬሽን በአውሮፓ፣ ሮም ላይ ተዘርፏል?

October 17, 2017 01:50 pm by Editor 2 Comments

  • በአምስተርዳም ከተማ የተካሄደው አመታዊው የቦርድ አባላት ስብሰባ ጥያቄውን ይመልሳል

ካለፈው ኦገስት ወር ጀምሮ እጅግ ተጋንኖ ሲወራ የነበረ ጉዳይ ነው። ፌዴሬሽኑ ሮም ላይ ተዘርፏል። ይህንን “ዝርፍያ” ልዩ ያደረገው በቅንብር እና በጥናት የተሰራ ነው የሚሉት ጥቂት አልነበሩም። ከውጭ የሚወራው እና የሚጻፈው ነገር ብዙ ነው። ፌዴሬሽኑ እንዴት እና ለምን ተዘረፈ? የሚለው ጥያቄ ግን ምላሹ ከመላ ምት ያላለፈ አልነበረም። ቅዳሜ፣ 14 ኦክቶበር 2017 በአምስተርዳም ከተማ የተካሄደው አመታዊው የቦርድ አባላት ስብሰባ ይህንን እንቆቅልሽ የፈታው ይመስላል። በእለቱ ከሳሽ እና ተከሳሽ  በተገኙበት፤ ጉዳዩን በግልጽ ለመወያየት ተችሎ ነበር። ካሜራችን ሂደቱን በድምጽና ምስል ይዞታል። (ቪድዮውን ይመልከቱ Part 1)

የኢትዮጵያውያን ስፖርት እና ባህል ፌዴሬሽን በአውሮፓ (ኢ.ስ.ካ.ፌ) ባለፈው ቅዳሜ፣ 14 ኦክቶበር 2017 አመታዊውን የቦርድ ስብሰባ  በአምስተርዳም ከተማ  አድርጎ ነበር። ከ 21 ክለቦች የተውጣጡ 45 አባላት የተሳተፉበት ይህ ስብሰባ አራት አጀንዳዎች ላይ የተወያየ ሲሆን፣ አንድ ቀን ከፈጀው ከዚህ ውይይት በኋላ አዲስ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መርጧል። በ2018 እና 2019 አዘጋጅ ሃገሮችም ታውቀዋል። በዚህም መሰረት በ2018 ስቱትጋርት – በ 2019 ደግሞ ዙሪክ በክለብ ደረጃ ፌስቲቫሉን ከዘጋጁ በኋላ – የማዘጋጀቱን ሃላፊነት ፌዴሬሽኑ መልሶ ይወስዳል። ላለፉት ሁለት አመታት በሆላንድ እና በሮም በፌዴሬሽኑ ሃላፊነት የተካሄዱት ዝግጅቶች እንደተጠበቀው ውጤታማ ባለመሆናቸው ለመጭው ሁለት አመት የአዘጋጅነቱን ሃላፊነት አዘጋጅ ሃገር ክለቦች እንዲወስዱ ጉባኤው ወስኗል። የ2017ቱ የሮማ ዝግጅት ብዙ አወዛጋቢ ነገሮች ነበሩበት።

ከዝግጅቱ በኋላ የተወሰኑ ግለሰቦች የተሰራበትን ገንዘብ ይዘው መጥፋታቸው በስፋት ሲወራ መሰንበቱ ይታወሳል።  የፌዴሬሽኑ አመራር አባላት፣ ዮሃንስ መሰለ፣ ግርማ ሳህሌ፣ ከበደ ሃይሌ እና ኢብራሂም ገንዘቡ እንዴት እንደተወሰደ እና እነሱም ሊደርስ ከነበረው ችግር እንዴት እንዳመለጡ ተናግረዋል። በወቅቱ በዚያ ስፍራ የነበረው ጥሩ ያልሆነ ድባብ እና ወሬ የነበረው አማራጭ ስፍራውን ለቅቆ ማምለጥ እንደነበር ቢገልጹም፣ ያረፉበት ሆቴል ጭምር ያልታሰቡ ክስተቶችን ተጋፍጠዋል። ሆቴል የክፍላቸው በማስተር ቁልፍ  እንደበረበሩባቸውም ተናግረዋል።

የዝግጅቱ አስተባባሪ ከነበሩት ውስጥ አንድነት (ቀዮ) እና ፍራንሲስኮ በአምስተርዳም ተገኝተው በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። የተባለውን ገንዘብ መውሰዱን ቀዮ ያመነ ሲሆን፣ ለዚህ ድርጊትም ምክንያት እንዳለው ይገልጻል።

ጉባኤው በአጀንዳው ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ በፌዴሬሽኑ እና በእነ ፍራንሲስኮ የቀረቡትን የፋይናንስ ዘገባ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ ወስኗል። ከጣልያን ሮቤርቶ፣ ከሆላንድ ክንፉ አሰፋ እና ከኮለን ተስፋዬ ጉዳዩን መርምረው ለአጠቃላይ ጉባኤ እንዲያቀርቡ ተመርጠዋል።

ውድ ግዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ክህሎታቸውን እና ገንዘባቸውን በነጻ ሲያፈስሱ የቆዩ የአመራር አባላት ሃላፊነታቸውን በጨዋነት አስረክበዋል። እጅግ አስቸጋሪ ጉዞ እንደተጓዙ ግልጽ ቢሆንም ትእግስታቸው ግን የሚደነቅ ነበር። ጉባኤውም የቀድሞውን አመራር አባላት በከፍተኛ ምስጋና ካሰናበታቸው በኋላ 9 አባላት ያሉበት አዲስ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መርጧል። አዲሶቹ የአመራር አባላት የሚከተሉት ናቸው።

  • አሳዬ ከኖርዌይ (ሊቀ መንበር)
  • ነቢዩ ሰቆጣው ከፍራንክፈርት
  • ተስፋዬ ከኮለን (ዋና ጸሃፊ)
  • ዳናኤል ከስዊዝ
  • አፈወርቅ አዘበርሊን
  • መስፍን  ከስቱትጋርት
  • ፋሲል ከካታንጋ – ለንደን
  • ሮቤርቶ ከሮማ
  • ቴዲ ከቤልጅየም
  • ብርሃኑ ክስዊድን (ገንዘብ ያዥ)

ቪድዮውን እዚህ ላይ ይመልከቱ

ክንፉ አሰፋ (ፎቶዎች በጸሃፊው የተላኩ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. ጎፋ says

    October 28, 2017 06:56 pm at 6:56 pm

    መቼ ይሆን እኛ ኢትዮጵያውያኖች በሃሳብ ተስማምተን ዓላማችንን የምናሳካው? አገር ቤት በወያኔ እናሳብባለን ውጭሳ በማን ሊሆን ይሆን? ብንተባበር። ወያኔ ክጥፌም አታልፍም ነበር።

    Reply
  2. cute-ehapa says

    November 8, 2017 01:51 am at 1:51 am

    These group of money grabbing ‘worrobelas’ don’t deserve to have their ‘meeting’ reported. Believe you me these are scums that are an embarrassment to diaspora. I know because I live in London!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule