• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ቦርድ፣ ማጭበርበሩን ያቁም!

January 20, 2015 12:45 am by Editor Leave a Comment

በሕወሓት አመራርና አጃቢዎች የተፈበረከው ምርጫ ቦርድ ባለፉት 20 አመታት ለ4 ጊዜ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ምርጫ አካሂዷል። ሁሉም ምርጫዎች ግን የዴሞክራሲ መስፈርትን የሚያሟሉ እንዳልነበሩ ዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ጭምር አረጋግጠዋል።

በ2007 ዓ.ም የምርጫ ውድድርም ሕወሓቶች፣ በዚሁ አመት ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ጭራሹን ላለማሳተፍ፣ ለአመታት ያህል የቤት ስራ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡ ለዚሁ አላማ ግቡን ለመምታት አስቀድመው እጅግ ብዙ ብቁ ምሁራንን እና ወጣት የፖለቲካ አመራሮችን “ለስልጣናችን አስጊ ናቸው” በማላት በሀሰት ወንጅለው አስረው በማሰቃየት ላይ ይገኛሉ። ብዙ የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላት ላይም ስጋት ፈጥረዋል፤ ከትምህርትና ከስራም አፈናቅለዋል። ፓርቲዎችን ለመበታተን ብዙ ሰርጎ-ገቦችን በማስረፅ አለመተማመን በመፍጠር፣ እንዲከፋፈሉ ለማድረግ ብዙ ገንዘብ ረጭተዋል።

ተቃናቃኝ ፓርቲዎች፣ ሰርገው ከገቡ ባንዳዎች ውስጣቸውን ለማጥራት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴም ለማሰናከል፤ ምርጫ ቦርዱ ከባንዳዎች ጋር በማበርና በመወገን ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ስራቸውን እንዳይሰሩ በጭቅጭቅ እየጠመዳቸው ይገኛል።

ለዚሁ ለማስረጃነት የሕወሓት መንግስት የህዝብ ድጋፍ ያላቸው ተቀናቃኝ ፓርቲዎች፤ ህዝብ በስብሰባና በሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡን እንዳያነቁ ከመከልከል አልፎም ብዙ አባላት ተጨፍጭፈው ደማቸው በጎዳና ፈሷል። በአገር ውስጥ ያለውን ሁለ-ገብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ የሚዘግቡ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ፀሃፊዎች፣ አምደኞችና ከያኒያን ታስረዋል ተሰደዋል።

ይሄ ሁሉ አልበቃም ብሎ፣ በዚሁ በምርጫ ዋዜማ አሸንፈው በፓርላማ ከፍተኛ ወንበር ያገኛሉ ያሏቸውን አንድነት እና መኢአድን ከምርጫ ጨዋታው ለማስወጣት፣ ብሎም ለመሰረዝ የተለያዩ ደባዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ፣ ምንም ስህተት ሳይኖርባቸው ትዕዛዙን ለመፈፀምና ምክንያታቸውን ለማስጨረስ ተደጋጋሚ ጉባኤ አድርገዋል፡፡ ምርጫ ቦርድ ጉባኤያቸውን እንዲታዘብ ጠርተውት፣ ሳይመጣ ቀርቶ ፓርቲዎችን ለማባረር ተዘጋጅተዋል ። ይህን ሁሉ ሲል የኢትዮጵያ ህዝብ ገጠር ከተማ ሳይለይ የምርጫ ቦርድን ሴራ ተረድቶት እየተመለከተው ይገኛል። ለውጥ ፈላጊ ነውና።

በሌላ በኩል፣ ምርጫ ቦርድ ህወሓቶች ባዋቀሯቸውና ምንም ተከታይ በሌላቸው፤ ለወደፊትም የህወሓት ተስፈኞች ከመሆን ውጭ ለህዝብና ሀገር ምንም ፋይዳ የሌላቸው ባንዳዎችን ወደፊት በማምጣት ገንዘብ ያገኛል። በሌላ በኩል ግን ጠንካራ ፓርቲዎችን ለማፍረስ ወጥመድ እየፈጠረ ይሰጣል። ምርጫ ቦርድም ሆነ ሕወሓት መረዳት ያለባቸው እነዚህ ፓርቲዎች ከምርጫ ጨዋታ ውጭ ከሆኑ፣ የሕወሓቶች ውድቀት የተቃናቃኝ ፓርቲዎች ድል መሆኑ የማይቀር እንደሆነ መረዳት አለባቸው።

እነዚህ ከምርጫ ጨዋታ ውጭ እንዲወጡ የሚፈለጉ ፓርቲዎች ህወሓት አስቀድሞ የወሰነው ስለሆነ ተደጋጋሚ ጉባኤ ማድረግ አቁመው ህወሓት ከሰራቸው ጥገኛ አጃቢዎቹ (ብቻው ማንጨብጨብ አለበት) የዚህ ኣፈና ውጤት ዳግም ህዝብ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንዲሄድ ተስፋ እንዲቆርጥ ያደርገዋል፤ ለዚህ ተጠያቂ የሚሆኑት ህወሓትና ምርጫ ቦርድ ይሆናሉ።

ለሕወሓት መሪዎች የምለግሳላቸው ምክር ቢኖር፣ የዘንድሮውን ምርጫ የዓለም-አቀፉን ህብረተሰብ ለማታለልና ለተራ የፖለቲካ ፍጆታ ብለው በሸፍጥ ጊዜያቸው ከማባከን እንዲቆጠቡ ነው፡፡ ሕወሓት፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም፣ ነፃነት ፍትህና መልካም አስተዳደር ሲል ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞችን መፍታት ይኖርበታል፡፡ ሁሉም በሰላማዊ መንገድ ከሚታገሉ ፓርቲዎች፣ ነፍጥ አንስተው በረሃ እስከ ገቡ ሃይሎች ድረስ የሰላም መድረክ ከፍቶ የሰላም ድርድር ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በዚህች አገር ሰላም ሰፍኖ ሁሉም ዜጎች በመቻቻል፣ በመፈቃቀር ስለሀገር ጥቅም ሀሳባቸውን በነፃነት አንሸራሽረው በህዝብ የድምፅና ዳኝነት ትመራ ዘንድ ምህዳሩን ቢያሰፉት የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ራሱ ሕወሓት ጭምር እጅጉን ይጠቀማል። ይህ ካልሆነ ግን ይህች ሀገርና ህዝቦቿ፣ ለከፋ ችግር መጋለጣቸው አይቀሬ ነው። አሁንም መፍትሄው በሕወሓት መሪዎችና አጃቢዎቹ እጅ ነው።

ሕወሓት ምርጫ ቦርድን መሳሪያ አድርጎ፣ በተቃናቃኝ ፓርቲዎች ላይ እያካሄደ ያለውን ሴራ ህዝባችንና አለምም ከወዲሁ ጠንቅቆ አውቆታል።

እግዚአብሔር ለሕወሓት መሪዎች ልብ ይስጥልን። (ምንጭ: ፍኖተ ነጻነት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule