• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ቦርድ፣ ማጭበርበሩን ያቁም!

January 20, 2015 12:45 am by Editor Leave a Comment

በሕወሓት አመራርና አጃቢዎች የተፈበረከው ምርጫ ቦርድ ባለፉት 20 አመታት ለ4 ጊዜ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ምርጫ አካሂዷል። ሁሉም ምርጫዎች ግን የዴሞክራሲ መስፈርትን የሚያሟሉ እንዳልነበሩ ዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ጭምር አረጋግጠዋል።

በ2007 ዓ.ም የምርጫ ውድድርም ሕወሓቶች፣ በዚሁ አመት ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ጭራሹን ላለማሳተፍ፣ ለአመታት ያህል የቤት ስራ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡ ለዚሁ አላማ ግቡን ለመምታት አስቀድመው እጅግ ብዙ ብቁ ምሁራንን እና ወጣት የፖለቲካ አመራሮችን “ለስልጣናችን አስጊ ናቸው” በማላት በሀሰት ወንጅለው አስረው በማሰቃየት ላይ ይገኛሉ። ብዙ የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላት ላይም ስጋት ፈጥረዋል፤ ከትምህርትና ከስራም አፈናቅለዋል። ፓርቲዎችን ለመበታተን ብዙ ሰርጎ-ገቦችን በማስረፅ አለመተማመን በመፍጠር፣ እንዲከፋፈሉ ለማድረግ ብዙ ገንዘብ ረጭተዋል።

ተቃናቃኝ ፓርቲዎች፣ ሰርገው ከገቡ ባንዳዎች ውስጣቸውን ለማጥራት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴም ለማሰናከል፤ ምርጫ ቦርዱ ከባንዳዎች ጋር በማበርና በመወገን ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ስራቸውን እንዳይሰሩ በጭቅጭቅ እየጠመዳቸው ይገኛል።

ለዚሁ ለማስረጃነት የሕወሓት መንግስት የህዝብ ድጋፍ ያላቸው ተቀናቃኝ ፓርቲዎች፤ ህዝብ በስብሰባና በሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡን እንዳያነቁ ከመከልከል አልፎም ብዙ አባላት ተጨፍጭፈው ደማቸው በጎዳና ፈሷል። በአገር ውስጥ ያለውን ሁለ-ገብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ የሚዘግቡ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ፀሃፊዎች፣ አምደኞችና ከያኒያን ታስረዋል ተሰደዋል።

ይሄ ሁሉ አልበቃም ብሎ፣ በዚሁ በምርጫ ዋዜማ አሸንፈው በፓርላማ ከፍተኛ ወንበር ያገኛሉ ያሏቸውን አንድነት እና መኢአድን ከምርጫ ጨዋታው ለማስወጣት፣ ብሎም ለመሰረዝ የተለያዩ ደባዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ፣ ምንም ስህተት ሳይኖርባቸው ትዕዛዙን ለመፈፀምና ምክንያታቸውን ለማስጨረስ ተደጋጋሚ ጉባኤ አድርገዋል፡፡ ምርጫ ቦርድ ጉባኤያቸውን እንዲታዘብ ጠርተውት፣ ሳይመጣ ቀርቶ ፓርቲዎችን ለማባረር ተዘጋጅተዋል ። ይህን ሁሉ ሲል የኢትዮጵያ ህዝብ ገጠር ከተማ ሳይለይ የምርጫ ቦርድን ሴራ ተረድቶት እየተመለከተው ይገኛል። ለውጥ ፈላጊ ነውና።

በሌላ በኩል፣ ምርጫ ቦርድ ህወሓቶች ባዋቀሯቸውና ምንም ተከታይ በሌላቸው፤ ለወደፊትም የህወሓት ተስፈኞች ከመሆን ውጭ ለህዝብና ሀገር ምንም ፋይዳ የሌላቸው ባንዳዎችን ወደፊት በማምጣት ገንዘብ ያገኛል። በሌላ በኩል ግን ጠንካራ ፓርቲዎችን ለማፍረስ ወጥመድ እየፈጠረ ይሰጣል። ምርጫ ቦርድም ሆነ ሕወሓት መረዳት ያለባቸው እነዚህ ፓርቲዎች ከምርጫ ጨዋታ ውጭ ከሆኑ፣ የሕወሓቶች ውድቀት የተቃናቃኝ ፓርቲዎች ድል መሆኑ የማይቀር እንደሆነ መረዳት አለባቸው።

እነዚህ ከምርጫ ጨዋታ ውጭ እንዲወጡ የሚፈለጉ ፓርቲዎች ህወሓት አስቀድሞ የወሰነው ስለሆነ ተደጋጋሚ ጉባኤ ማድረግ አቁመው ህወሓት ከሰራቸው ጥገኛ አጃቢዎቹ (ብቻው ማንጨብጨብ አለበት) የዚህ ኣፈና ውጤት ዳግም ህዝብ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንዲሄድ ተስፋ እንዲቆርጥ ያደርገዋል፤ ለዚህ ተጠያቂ የሚሆኑት ህወሓትና ምርጫ ቦርድ ይሆናሉ።

ለሕወሓት መሪዎች የምለግሳላቸው ምክር ቢኖር፣ የዘንድሮውን ምርጫ የዓለም-አቀፉን ህብረተሰብ ለማታለልና ለተራ የፖለቲካ ፍጆታ ብለው በሸፍጥ ጊዜያቸው ከማባከን እንዲቆጠቡ ነው፡፡ ሕወሓት፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም፣ ነፃነት ፍትህና መልካም አስተዳደር ሲል ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞችን መፍታት ይኖርበታል፡፡ ሁሉም በሰላማዊ መንገድ ከሚታገሉ ፓርቲዎች፣ ነፍጥ አንስተው በረሃ እስከ ገቡ ሃይሎች ድረስ የሰላም መድረክ ከፍቶ የሰላም ድርድር ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በዚህች አገር ሰላም ሰፍኖ ሁሉም ዜጎች በመቻቻል፣ በመፈቃቀር ስለሀገር ጥቅም ሀሳባቸውን በነፃነት አንሸራሽረው በህዝብ የድምፅና ዳኝነት ትመራ ዘንድ ምህዳሩን ቢያሰፉት የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ራሱ ሕወሓት ጭምር እጅጉን ይጠቀማል። ይህ ካልሆነ ግን ይህች ሀገርና ህዝቦቿ፣ ለከፋ ችግር መጋለጣቸው አይቀሬ ነው። አሁንም መፍትሄው በሕወሓት መሪዎችና አጃቢዎቹ እጅ ነው።

ሕወሓት ምርጫ ቦርድን መሳሪያ አድርጎ፣ በተቃናቃኝ ፓርቲዎች ላይ እያካሄደ ያለውን ሴራ ህዝባችንና አለምም ከወዲሁ ጠንቅቆ አውቆታል።

እግዚአብሔር ለሕወሓት መሪዎች ልብ ይስጥልን። (ምንጭ: ፍኖተ ነጻነት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule