• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምርጫ ቦርድ፣ ማጭበርበሩን ያቁም!

January 20, 2015 12:45 am by Editor Leave a Comment

በሕወሓት አመራርና አጃቢዎች የተፈበረከው ምርጫ ቦርድ ባለፉት 20 አመታት ለ4 ጊዜ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ምርጫ አካሂዷል። ሁሉም ምርጫዎች ግን የዴሞክራሲ መስፈርትን የሚያሟሉ እንዳልነበሩ ዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ጭምር አረጋግጠዋል።

በ2007 ዓ.ም የምርጫ ውድድርም ሕወሓቶች፣ በዚሁ አመት ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ጭራሹን ላለማሳተፍ፣ ለአመታት ያህል የቤት ስራ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡ ለዚሁ አላማ ግቡን ለመምታት አስቀድመው እጅግ ብዙ ብቁ ምሁራንን እና ወጣት የፖለቲካ አመራሮችን “ለስልጣናችን አስጊ ናቸው” በማላት በሀሰት ወንጅለው አስረው በማሰቃየት ላይ ይገኛሉ። ብዙ የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላት ላይም ስጋት ፈጥረዋል፤ ከትምህርትና ከስራም አፈናቅለዋል። ፓርቲዎችን ለመበታተን ብዙ ሰርጎ-ገቦችን በማስረፅ አለመተማመን በመፍጠር፣ እንዲከፋፈሉ ለማድረግ ብዙ ገንዘብ ረጭተዋል።

ተቃናቃኝ ፓርቲዎች፣ ሰርገው ከገቡ ባንዳዎች ውስጣቸውን ለማጥራት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴም ለማሰናከል፤ ምርጫ ቦርዱ ከባንዳዎች ጋር በማበርና በመወገን ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ስራቸውን እንዳይሰሩ በጭቅጭቅ እየጠመዳቸው ይገኛል።

ለዚሁ ለማስረጃነት የሕወሓት መንግስት የህዝብ ድጋፍ ያላቸው ተቀናቃኝ ፓርቲዎች፤ ህዝብ በስብሰባና በሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡን እንዳያነቁ ከመከልከል አልፎም ብዙ አባላት ተጨፍጭፈው ደማቸው በጎዳና ፈሷል። በአገር ውስጥ ያለውን ሁለ-ገብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ የሚዘግቡ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ፀሃፊዎች፣ አምደኞችና ከያኒያን ታስረዋል ተሰደዋል።

ይሄ ሁሉ አልበቃም ብሎ፣ በዚሁ በምርጫ ዋዜማ አሸንፈው በፓርላማ ከፍተኛ ወንበር ያገኛሉ ያሏቸውን አንድነት እና መኢአድን ከምርጫ ጨዋታው ለማስወጣት፣ ብሎም ለመሰረዝ የተለያዩ ደባዎች እየተፈፀሙ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ፣ ምንም ስህተት ሳይኖርባቸው ትዕዛዙን ለመፈፀምና ምክንያታቸውን ለማስጨረስ ተደጋጋሚ ጉባኤ አድርገዋል፡፡ ምርጫ ቦርድ ጉባኤያቸውን እንዲታዘብ ጠርተውት፣ ሳይመጣ ቀርቶ ፓርቲዎችን ለማባረር ተዘጋጅተዋል ። ይህን ሁሉ ሲል የኢትዮጵያ ህዝብ ገጠር ከተማ ሳይለይ የምርጫ ቦርድን ሴራ ተረድቶት እየተመለከተው ይገኛል። ለውጥ ፈላጊ ነውና።

በሌላ በኩል፣ ምርጫ ቦርድ ህወሓቶች ባዋቀሯቸውና ምንም ተከታይ በሌላቸው፤ ለወደፊትም የህወሓት ተስፈኞች ከመሆን ውጭ ለህዝብና ሀገር ምንም ፋይዳ የሌላቸው ባንዳዎችን ወደፊት በማምጣት ገንዘብ ያገኛል። በሌላ በኩል ግን ጠንካራ ፓርቲዎችን ለማፍረስ ወጥመድ እየፈጠረ ይሰጣል። ምርጫ ቦርድም ሆነ ሕወሓት መረዳት ያለባቸው እነዚህ ፓርቲዎች ከምርጫ ጨዋታ ውጭ ከሆኑ፣ የሕወሓቶች ውድቀት የተቃናቃኝ ፓርቲዎች ድል መሆኑ የማይቀር እንደሆነ መረዳት አለባቸው።

እነዚህ ከምርጫ ጨዋታ ውጭ እንዲወጡ የሚፈለጉ ፓርቲዎች ህወሓት አስቀድሞ የወሰነው ስለሆነ ተደጋጋሚ ጉባኤ ማድረግ አቁመው ህወሓት ከሰራቸው ጥገኛ አጃቢዎቹ (ብቻው ማንጨብጨብ አለበት) የዚህ ኣፈና ውጤት ዳግም ህዝብ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንዲሄድ ተስፋ እንዲቆርጥ ያደርገዋል፤ ለዚህ ተጠያቂ የሚሆኑት ህወሓትና ምርጫ ቦርድ ይሆናሉ።

ለሕወሓት መሪዎች የምለግሳላቸው ምክር ቢኖር፣ የዘንድሮውን ምርጫ የዓለም-አቀፉን ህብረተሰብ ለማታለልና ለተራ የፖለቲካ ፍጆታ ብለው በሸፍጥ ጊዜያቸው ከማባከን እንዲቆጠቡ ነው፡፡ ሕወሓት፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም፣ ነፃነት ፍትህና መልካም አስተዳደር ሲል ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞችን መፍታት ይኖርበታል፡፡ ሁሉም በሰላማዊ መንገድ ከሚታገሉ ፓርቲዎች፣ ነፍጥ አንስተው በረሃ እስከ ገቡ ሃይሎች ድረስ የሰላም መድረክ ከፍቶ የሰላም ድርድር ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በዚህች አገር ሰላም ሰፍኖ ሁሉም ዜጎች በመቻቻል፣ በመፈቃቀር ስለሀገር ጥቅም ሀሳባቸውን በነፃነት አንሸራሽረው በህዝብ የድምፅና ዳኝነት ትመራ ዘንድ ምህዳሩን ቢያሰፉት የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ራሱ ሕወሓት ጭምር እጅጉን ይጠቀማል። ይህ ካልሆነ ግን ይህች ሀገርና ህዝቦቿ፣ ለከፋ ችግር መጋለጣቸው አይቀሬ ነው። አሁንም መፍትሄው በሕወሓት መሪዎችና አጃቢዎቹ እጅ ነው።

ሕወሓት ምርጫ ቦርድን መሳሪያ አድርጎ፣ በተቃናቃኝ ፓርቲዎች ላይ እያካሄደ ያለውን ሴራ ህዝባችንና አለምም ከወዲሁ ጠንቅቆ አውቆታል።

እግዚአብሔር ለሕወሓት መሪዎች ልብ ይስጥልን። (ምንጭ: ፍኖተ ነጻነት)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule