• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እምዬ ምኒልክ፡ የጥቁር ሕዝብ ኩራት!

December 12, 2013 12:42 pm by Editor 6 Comments

ዛሬ ታህሳስ 3ቀን የሚከበረው የዳግማዊ አጼ ምኒልክ 100ኛ የዕረፍት ዓመት “እምዬ ምኒልክ ምን ዓይነት ውርስ ትተውልን ሄዱ?” ብለን እንድንጠይቅ የሚያደርገን ነው፡፡ በመሆኑም ወደ ጦርነት ለመግባት ሳይፈልጉ “በግድ” ወደሄዱበት የጣሊያን ጦርነት መለስ ብለን የሆነውን እንድናስብ ወደድን፡፡

ክተት፡-

“እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላትን አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፡፡ እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር menelik IIቸርነት ገዛሁ፡፡ እንግዲህ ብሞትም ሞት ለሁሉ ነውና ስለ እኔ ሞት አላዝንም፤ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፤ እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን የባሕር በር አልፎ መጥቷልና እኔም ያገሬ ከብት ማለቁንና የሰዉን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም፤ አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ፡፡ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለምሽትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በሐዘን እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፡፡ አልተውህም ማርያምን፤ ለዚህ አማላጅ የለኝም፡፡ ዘመቻዬ በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረኢሉ ከትተህ ላግኝህ፡፡”

ከድል በኋላ፡-

“(ጥልያኖች) በጥጋባቸው አድዋ ላይ ተዋግተው ድል ሆኑ፡፡ እኔ በድንቁርናቸው ብዛት የእነዚያን ሁሉ ክርስቲን ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ “ድል አደረኩዋቸው” ብዬ ደስ አይለኝም” መጋቢት 23፤ 1888 ምኒልክ ለአውሮጳዊው ዲፕሎማት ሙሴ ሸፍኔ ከላኩት፡፡

ምርኮኞችን ሲመልሱ፡-

“… በእጄ ጨብጫቸው፤ በእግሬ ረግጫቸው የነበሩትን እኒህን ምርኮኞች ሳልነካቸው የሰደድኩልህ … በሞኝነት አይደለም፡፡ … ብትታረቁ ድንቅ፤ ጦርነትም ከከጀላችሁ እነዚህንም ጨምራችሁ ኑ፡፡”

ስለዚህ የምኒልክን ውርስ እያስታወስን እንዲህ እንላለን:-

ምኒልክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ።
በሠራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ
ተፈጠመ ጣሊያን አበሻ እንዳይደርስ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. JINKA says

    December 19, 2013 10:29 pm at 10:29 pm

    Emperror Minelik is a man who signs with out thinking 2 times he signed 12 times en evry corner of Ethiopia he is well known in selling Dijubti, Eritrea to colonizers and he was a murderrer of Oromoo and Southern ethiopan people specially and Over all Ethiopians generally

    Reply
  2. JINKA says

    December 19, 2013 10:30 pm at 10:30 pm

    MENELIK ANTI OROOMOO

    Reply
  3. Abegaz says

    December 29, 2013 04:04 am at 4:04 am

    Emperor Menilik a great leader Ethiopia has had in centuries. He was bright, ahead of his generation in modernizing Ethiopia, keeping his country safe from colonizers. He has deep natural talent for laws. He kept Ethiopia from the jaws of colonizers by giving small, and maintaining the greater part. Everything he signed has a clause that says, territories taken (such as Eritrea and Djibouti) shall be returned to Ethiopia when the occupation period is finished. It is our failure to get back our rightful property. Haile Selassie did great (got back Eritrea). Mengstu failed to claim Djibouti because he was a communist and did not claim Djibouti knowing USA will oppose it. He failed where Haile Selassie succeeded in diplomacy. Meles is the greatest loser and street damn. He wrote a letter to UN secretary to break away Eritrea. What Haile Selassie labored for, was given away by the idiot Meles in a silver plat. What a shame!!

    Reply
  4. Gonfa says

    December 31, 2013 01:56 pm at 1:56 pm

    I’m an Oromo Ethiopian that admires what Menilik has achieved. He had many Oromo speaking soldiers and leaders of the army. Oromos are partakers of the victory Menilik achieved over European colonisers making the entire black people proud. The reason we still have our Oromo and other ethnic languages and cultures intact is because of Menilik’s stance against Italian invaders. Oromo forefathers have shaded their blood at Adwa and all other battle fields just like any other Ethiopians. It’s sad to see a handful of Oromo speaking traitors trying to rewrite history by fabricating lies. Menilik is the pride of all black people.

    Reply
    • Gonfa says

      December 31, 2013 07:32 pm at 7:32 pm

      You Used my name and act as an oromo. you are bare faced lair( fake gonfa above)

      Reply
  5. በዛወርቅ መንገሻ says

    March 11, 2019 01:55 pm at 1:55 pm

    እምዬ ሚኒሊክ ደፋር፡አሰተዋይ ፡ሩህሩህ፡ብልህ መሪ ናቸው፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule