• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የኦሮምያ ልዩ ጥቅም ረቂቅ አዋጅ ላይ የ EDF አቋም መግለጫ

July 3, 2017 07:27 pm by Editor 10 Comments

የኢትዮጵያውያን የውይይትና ምክክር መድረክ (ኢውምመ) (EDF) በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ምሁራን፣ አክቲቪስቶች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች የተመሰረተ መድረክ ሲሆን በኢትዮጵያ መሰረታዊ የኢኮኖሚ የማህበራዊና የፖለቲካዊ ችግሮች ዙሪያ ምርምሮችን እያካሄደ ለተፈላጊ ለውጦች የሚታገል ድርጅት ነው። የዚህ ድርጅት አመራር አባላት በቅርቡ በሚንስትሮች ምክር ቤት የወጣውን የኦሮሚያን ልዩ ጥቅም የሚተነትነውን ረቂቅ አዋጅ በጥልቀት ተወያይቶበታል።

ተወያይቶ የሚከተለው መደምደሚያ ላይ ደርሷል በEDF እምነት በመጀመሪያ ደረጃ   በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መሰረታዊ ችግር ከብሄር ፖለቲካ የመነጩ አንዳንድ የህገ መንግስቱ አንቀጾች ናቸው። ለዚህ ለአሁኑ የሚንስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ አዋጅ መነሻውም ይሄው ህገ-መንግስቱ ላይ የተቀመጠው አንቀጽ 45 ንኡስ አንቀጽ   5 ነው። ህገ-መንግስቱ ከብሄር ፖለቲካ አስተሳሰብ በመነጨ የተቀረጸ በመሆኑ መግቢያው ላይ ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች አገር መሆኑዋን ሲገልጽ ለዜግነት ቦታ አልሰጠም። በአንጻሩ የብዙ ዴሞክራት ሃገሮች ለምሳሌ የተባበረችውን አሜሪካንን፣ አውስትሬሊያን፣ ህንድን ብንመለከት “እኛ” በሚል ይጀምራል። የአንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ የተባበረ ማህበረሰብ እንደመሰረቱ በቃል ኪዳናቸው ላይ አስፍረዋል። ይህ መሰረታዊ እምነትና ቃል ኪዳን ለአንድ ሃገር ህልውና በጣም ወሳኝ ነገር ነው። ፖሊሲዎችና ህጎች ሁሉ ከዚህ ከህገ መንግስቱ የህግ ምንጮች የሚቀዱ በመሆናቸው ህገ መንግስቱ የአንድን ሃገር ህዝብ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ወጥነት ማረጋገጡ ቁልፍ ነገር ነው።

ህገ መንግስቱ የያዛቸው አንዳንድ አንቀጾች በራሳቸው ችግር መሆናቸው ሳያንስ ከነዚህ አንቀጾች የሚቀዳው ህግ ሲመጣ ደግሞ እንዴት አንድነታችንን እኩልነታችንን እንደሚጎዳ የሚንስትሮች ምክር ቤት መግለጫውን ሲያወጣ ተምረናል። የሚንስትሮች ምክር ቤት መግለጫ የኢትዮጵያውያንን መሰረታዊ መብቶች እንደ ልዩ ጥቅም አይቶ አዋጅ ማውጣቱም ሌላ ችግር ሆኖ አይተነዋል። ከሁሉ በላይ ደግሞ አዲስ አበባ ብቻ ሳትሆን ቡድኖች ተሰባስበው የሚኖሩባቸውን የክልል ከተሞች ማለትም እንደነ አዋሳ፣ አሶሳ፣ ጋምቤላና አንዳንድ ዞኖችም እንዲሁ የልዩ ጥቅም ጥያቄ የሚያስነሳ ሆኖ አግኝተነዋል። ይህ ጉዳይ የሚያመጣው ዋና ችግር የልዩ ጥቅም አስተሳሰብ ሲስተማችንን እስከ ታች ሊያበላሸውና ከእኩልነት ይልቅ በተፈጥሮ ሃብትና ኢኮኖሚ ጉዳዮች የይገባኛል ጥያቄዎችን እየፈጠረ አንድነታችንንና የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄዎቻችንን ያበላሻል። ዛሬ በዚህ በወጣው አዋጅ ዙሪያ ኢትዮጵያውያን የሚያዝኑት አዲስ አበባ ኣካባቢ ያለ ገበሬ አይጠቀም ከሚል ሳይሆን የአዋጁ ስሜት ብሄርን መሰረት ያደረገ በመሆኑ፣ መሰረታዊ የዜጎችን  ጥያቄዎች ከመፍታት  ይልቅ ልዩነትን ለማጉላት  የተጨነቀ ሆኖ ስላዩት ነው።

ዛሬ ኢትዮጵያውያን የቸገራቸው ነገር እንዴት ከድህነት እንደሚወጡ፣ እንዴት ወደ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንደሚያድጉ ነው እንጂ የቀበሌ ስሞች የመቀያየር ጉዳይ አይደለም። የሚንስትሮች ምክር ቤትን ያሳሰበው ጉዳይ በከተሞች መስፋፋት ጊዜ የሚመጣውን ችግር በተመለከ ቢሆን በመላ ሃገሪቱ ወጥነት ባለው ሁኔታ በከተሞች አካባቢ የሚኖሩ ገበሬዎችን ህይወት በሚመለከት አንድ ወጥ አሰራር ሊፈጥር ይችል ነበር። ነገር ግን መንግስትን ያሳሰበው ጉዳይ ይህ ባለመሆኑ በብሄሮች መካከል ያለውን ልዩነት ለማጉላት ሲጥር ይታያል። ወጥነት ያለው ኢትዮጵያውያንን በብሄር በሃይማኖት ሳይነጥል የሚንከባከብ ህግ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሞገስ ያገኛል። የመንግስት ስራ ከዚህ ፍጹም ተጻራሪ በመሆኑ መላው የሃገራችን ህዝብ ለተፈላጊ ለውጥ ትግሉን እንዲቀጥል ጥሪ እያደረግን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የኢትዮጵያ ለጋሽ ሃገራት ሁሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ፖለቲካዊ ለውጥ እንዲመጣ ጥብቅ ርምጃ እንዲወስዱና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ እናደርጋለን።

የኢትዮጵያ የውይይትና መፍትሔ መድረክ
9900 GreenbeltRD.E#343 –  Lanham,MD 20706 (መግለጫውን በእንግሊዝኛ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ተረፈ ታደሰ says

    July 5, 2017 11:38 am at 11:38 am

    አንድ ነን እየተባለ እስከ መቸ እያለቀስን እንኖራለን፡፡ የድሮዎቹ እነምንይልክ እና አጤ ሀይለ ስላሴ መች ከዘረኝነት ፀድተዉ ያዉቃሉና ነዉ ጩሄቱ!! ዛሬ ግን ጊዜዉ ተቀይረዋል፡፡ መሰረታዊዉ ችግር ዛሬ ድረስ ያለዉ የተዛባ አመለካከት ነዉ፡፡ስልጣኔ ያልቀየረዉ፤ ትምህርት ያልቀየረዉ ፤ ባጠቃላይ ጊዜ ያልቄየረዉ አመለካከት!! ስለዚህ ይህን አመለካከታችሁን በማስተካከል ዉይይቱን ብትጀምሩ ትማሩበታላችሁ ባይ ነኝ፡፡

    Reply
  2. ተረፈ ታደሰ says

    July 5, 2017 12:06 pm at 12:06 pm

    For me citizen ship should come after realizing am free or under colony. I personally should not tolerate the concept of citizenship if i am still underneath of someones’ feet in the name of citizenship. I am Wolaitta and Wolaitta first. I don’t care about my citizen ship if I were already lost somewhere my identity. My personal identity should be respected first. Ethiopia (if there is, today) should be a country of tolerance and respect. No tolerance and respect mean no more peace, and security as well as development that prevails. I must respect the rights of minorities as well as diversities. The number or population size should not be a pride of any ethnic group in Ethiopia. A population size that supposed to be large as compared to others that you belongs to should not be your cause of pride. Your pride should be your own personality. You can be of a person of integrity, diligence, compassion, and vision. You can be a person of tolerance, hard working, friendliness, and so on. Paul Kaggame once said “no people compared to others weak, or so but your countries size be”. Thus, size has no significant effect on your personality or on your well being rather your good qualities like integrity, friendliness, communication, compassion, respect and tolerance to diversities. Diversity can’t and won’t be destroyed in any ways and any times. You should respect diversity but tolerate and further equality between you and others. No special person in this globe. No special clan or nationality or nation. All come from the same ancestors. Same family! Democratic and human rights should be judged with justices. Justice must be the center of all governmental functions. Political parties too should not be an exception. Our attitude toward diversity should be corrected soon otherwise no more improvement will be happen.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    July 6, 2017 02:23 am at 2:23 am

    Guys!!! As I understand, the ministers passed a big and historical bill in order to make the country united. The Parliament asked or gave a chance to be discussed and digested. In my part, the discussion should be given to Oromyia Government. The Oromyia Government has right and responsible to manage it. For instance, the Amhara and Tigrai regional Governments made their own state without anyone interference. In this case, this chance should be delivered and encouraged to a very beneficial way to Oromo people. Because, the city is in the middle of the regional Government.

    Reply
  4. Tadesse says

    July 9, 2017 10:39 pm at 10:39 pm

    When people lived in Addis Abeba,all you care was if you speak Amharic,I had friends of Oromo parents,they weren’t ashamed to say or tell this but they were also full of respect to what was going in the city.I am a tigrian who grew up in the 1950s and when I was to Mekelle in 1996,i was shocked how small the grain was/eshet in Amharic and shewit in Tigrigna,who care about the name of a land there while nature is deteriorating,I am an Ethiopian again and again.

    Reply
  5. Tadesse says

    July 9, 2017 10:51 pm at 10:51 pm

    I am sorry for my anger,some moslim Oromos,insult Ethiopia and all about Ethiopia,the amharans and every,the heroic amharans sent lemesmatu yemikef.

    Reply
  6. Tadesse says

    July 9, 2017 10:54 pm at 10:54 pm

    Like Gonder was built by foreigners.

    Reply
  7. Tadesse says

    July 9, 2017 10:55 pm at 10:55 pm

    Egziabher yefaredachew,lela men yebalal.Ye Ethiopia Egziabher.

    Reply
  8. Tadesse says

    July 9, 2017 10:57 pm at 10:57 pm

    Ye Egziabher lijoch slehonu ende teraw sew becha yefetenalu belo maseb yewahnet new/sle Israelawian yetebale.

    Reply
  9. aradw says

    July 10, 2017 08:34 pm at 8:34 pm

    የኦሮሞን ጉዳይ ለኦሮም ተወት ኣርጉት። ለቀቅ ኣርጉት ። የህ ጉዳይ ፊንፊኔን ወዳ ባለበቷ ኦሮሞ የመመለስ ጉዳይ ነው። የህ ደግሞ ማንንም ኣይጎዳም። ጥቅሙ ግን ለቡዙሃን ነዉ። መሁራኖችም አስተምሩ ተመራመሩ ዘፋኞችም ዘምሩ ዝፋኑ ብር ሰብሰቡ ።

    Reply
  10. telala says

    July 22, 2017 09:32 pm at 9:32 pm

    terei yalegizesh new yeteweledeshiw meweled yalebsh be 1800 wochu akabai neber. Gizena alem telosh hedual. neqa bey wolaitawochen atasedbi. wolaitanet yerasesh new betifelegim lalemehon aticheym. selezih wolaita first minamin yemityewen neger tewet argesh wedefit terameji. aemeroshenem kefet arigw gizew yeneged mehonu kertual. yegimel shint athugn.
    Mulei astesasebish lela new gen min yadergal chinqilatesh ayseram yezorebesh nesh beolf propaganda.
    Ardawm endezihu demo manew leoromo teqorqari yaderegeh. kemelekiaw rak bel metet nalahen nektotal

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule