• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የኦሮምያ ልዩ ጥቅም ረቂቅ አዋጅ ላይ የ EDF አቋም መግለጫ

July 3, 2017 07:27 pm by Editor 10 Comments

የኢትዮጵያውያን የውይይትና ምክክር መድረክ (ኢውምመ) (EDF) በአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ምሁራን፣ አክቲቪስቶች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች የተመሰረተ መድረክ ሲሆን በኢትዮጵያ መሰረታዊ የኢኮኖሚ የማህበራዊና የፖለቲካዊ ችግሮች ዙሪያ ምርምሮችን እያካሄደ ለተፈላጊ ለውጦች የሚታገል ድርጅት ነው። የዚህ ድርጅት አመራር አባላት በቅርቡ በሚንስትሮች ምክር ቤት የወጣውን የኦሮሚያን ልዩ ጥቅም የሚተነትነውን ረቂቅ አዋጅ በጥልቀት ተወያይቶበታል።

ተወያይቶ የሚከተለው መደምደሚያ ላይ ደርሷል በEDF እምነት በመጀመሪያ ደረጃ   በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መሰረታዊ ችግር ከብሄር ፖለቲካ የመነጩ አንዳንድ የህገ መንግስቱ አንቀጾች ናቸው። ለዚህ ለአሁኑ የሚንስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ አዋጅ መነሻውም ይሄው ህገ-መንግስቱ ላይ የተቀመጠው አንቀጽ 45 ንኡስ አንቀጽ   5 ነው። ህገ-መንግስቱ ከብሄር ፖለቲካ አስተሳሰብ በመነጨ የተቀረጸ በመሆኑ መግቢያው ላይ ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች አገር መሆኑዋን ሲገልጽ ለዜግነት ቦታ አልሰጠም። በአንጻሩ የብዙ ዴሞክራት ሃገሮች ለምሳሌ የተባበረችውን አሜሪካንን፣ አውስትሬሊያን፣ ህንድን ብንመለከት “እኛ” በሚል ይጀምራል። የአንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ የተባበረ ማህበረሰብ እንደመሰረቱ በቃል ኪዳናቸው ላይ አስፍረዋል። ይህ መሰረታዊ እምነትና ቃል ኪዳን ለአንድ ሃገር ህልውና በጣም ወሳኝ ነገር ነው። ፖሊሲዎችና ህጎች ሁሉ ከዚህ ከህገ መንግስቱ የህግ ምንጮች የሚቀዱ በመሆናቸው ህገ መንግስቱ የአንድን ሃገር ህዝብ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ወጥነት ማረጋገጡ ቁልፍ ነገር ነው።

ህገ መንግስቱ የያዛቸው አንዳንድ አንቀጾች በራሳቸው ችግር መሆናቸው ሳያንስ ከነዚህ አንቀጾች የሚቀዳው ህግ ሲመጣ ደግሞ እንዴት አንድነታችንን እኩልነታችንን እንደሚጎዳ የሚንስትሮች ምክር ቤት መግለጫውን ሲያወጣ ተምረናል። የሚንስትሮች ምክር ቤት መግለጫ የኢትዮጵያውያንን መሰረታዊ መብቶች እንደ ልዩ ጥቅም አይቶ አዋጅ ማውጣቱም ሌላ ችግር ሆኖ አይተነዋል። ከሁሉ በላይ ደግሞ አዲስ አበባ ብቻ ሳትሆን ቡድኖች ተሰባስበው የሚኖሩባቸውን የክልል ከተሞች ማለትም እንደነ አዋሳ፣ አሶሳ፣ ጋምቤላና አንዳንድ ዞኖችም እንዲሁ የልዩ ጥቅም ጥያቄ የሚያስነሳ ሆኖ አግኝተነዋል። ይህ ጉዳይ የሚያመጣው ዋና ችግር የልዩ ጥቅም አስተሳሰብ ሲስተማችንን እስከ ታች ሊያበላሸውና ከእኩልነት ይልቅ በተፈጥሮ ሃብትና ኢኮኖሚ ጉዳዮች የይገባኛል ጥያቄዎችን እየፈጠረ አንድነታችንንና የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄዎቻችንን ያበላሻል። ዛሬ በዚህ በወጣው አዋጅ ዙሪያ ኢትዮጵያውያን የሚያዝኑት አዲስ አበባ ኣካባቢ ያለ ገበሬ አይጠቀም ከሚል ሳይሆን የአዋጁ ስሜት ብሄርን መሰረት ያደረገ በመሆኑ፣ መሰረታዊ የዜጎችን  ጥያቄዎች ከመፍታት  ይልቅ ልዩነትን ለማጉላት  የተጨነቀ ሆኖ ስላዩት ነው።

ዛሬ ኢትዮጵያውያን የቸገራቸው ነገር እንዴት ከድህነት እንደሚወጡ፣ እንዴት ወደ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንደሚያድጉ ነው እንጂ የቀበሌ ስሞች የመቀያየር ጉዳይ አይደለም። የሚንስትሮች ምክር ቤትን ያሳሰበው ጉዳይ በከተሞች መስፋፋት ጊዜ የሚመጣውን ችግር በተመለከ ቢሆን በመላ ሃገሪቱ ወጥነት ባለው ሁኔታ በከተሞች አካባቢ የሚኖሩ ገበሬዎችን ህይወት በሚመለከት አንድ ወጥ አሰራር ሊፈጥር ይችል ነበር። ነገር ግን መንግስትን ያሳሰበው ጉዳይ ይህ ባለመሆኑ በብሄሮች መካከል ያለውን ልዩነት ለማጉላት ሲጥር ይታያል። ወጥነት ያለው ኢትዮጵያውያንን በብሄር በሃይማኖት ሳይነጥል የሚንከባከብ ህግ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሞገስ ያገኛል። የመንግስት ስራ ከዚህ ፍጹም ተጻራሪ በመሆኑ መላው የሃገራችን ህዝብ ለተፈላጊ ለውጥ ትግሉን እንዲቀጥል ጥሪ እያደረግን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የኢትዮጵያ ለጋሽ ሃገራት ሁሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ፖለቲካዊ ለውጥ እንዲመጣ ጥብቅ ርምጃ እንዲወስዱና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ እናደርጋለን።

የኢትዮጵያ የውይይትና መፍትሔ መድረክ
9900 GreenbeltRD.E#343 –  Lanham,MD 20706 (መግለጫውን በእንግሊዝኛ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ተረፈ ታደሰ says

    July 5, 2017 11:38 am at 11:38 am

    አንድ ነን እየተባለ እስከ መቸ እያለቀስን እንኖራለን፡፡ የድሮዎቹ እነምንይልክ እና አጤ ሀይለ ስላሴ መች ከዘረኝነት ፀድተዉ ያዉቃሉና ነዉ ጩሄቱ!! ዛሬ ግን ጊዜዉ ተቀይረዋል፡፡ መሰረታዊዉ ችግር ዛሬ ድረስ ያለዉ የተዛባ አመለካከት ነዉ፡፡ስልጣኔ ያልቀየረዉ፤ ትምህርት ያልቀየረዉ ፤ ባጠቃላይ ጊዜ ያልቄየረዉ አመለካከት!! ስለዚህ ይህን አመለካከታችሁን በማስተካከል ዉይይቱን ብትጀምሩ ትማሩበታላችሁ ባይ ነኝ፡፡

    Reply
  2. ተረፈ ታደሰ says

    July 5, 2017 12:06 pm at 12:06 pm

    For me citizen ship should come after realizing am free or under colony. I personally should not tolerate the concept of citizenship if i am still underneath of someones’ feet in the name of citizenship. I am Wolaitta and Wolaitta first. I don’t care about my citizen ship if I were already lost somewhere my identity. My personal identity should be respected first. Ethiopia (if there is, today) should be a country of tolerance and respect. No tolerance and respect mean no more peace, and security as well as development that prevails. I must respect the rights of minorities as well as diversities. The number or population size should not be a pride of any ethnic group in Ethiopia. A population size that supposed to be large as compared to others that you belongs to should not be your cause of pride. Your pride should be your own personality. You can be of a person of integrity, diligence, compassion, and vision. You can be a person of tolerance, hard working, friendliness, and so on. Paul Kaggame once said “no people compared to others weak, or so but your countries size be”. Thus, size has no significant effect on your personality or on your well being rather your good qualities like integrity, friendliness, communication, compassion, respect and tolerance to diversities. Diversity can’t and won’t be destroyed in any ways and any times. You should respect diversity but tolerate and further equality between you and others. No special person in this globe. No special clan or nationality or nation. All come from the same ancestors. Same family! Democratic and human rights should be judged with justices. Justice must be the center of all governmental functions. Political parties too should not be an exception. Our attitude toward diversity should be corrected soon otherwise no more improvement will be happen.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    July 6, 2017 02:23 am at 2:23 am

    Guys!!! As I understand, the ministers passed a big and historical bill in order to make the country united. The Parliament asked or gave a chance to be discussed and digested. In my part, the discussion should be given to Oromyia Government. The Oromyia Government has right and responsible to manage it. For instance, the Amhara and Tigrai regional Governments made their own state without anyone interference. In this case, this chance should be delivered and encouraged to a very beneficial way to Oromo people. Because, the city is in the middle of the regional Government.

    Reply
  4. Tadesse says

    July 9, 2017 10:39 pm at 10:39 pm

    When people lived in Addis Abeba,all you care was if you speak Amharic,I had friends of Oromo parents,they weren’t ashamed to say or tell this but they were also full of respect to what was going in the city.I am a tigrian who grew up in the 1950s and when I was to Mekelle in 1996,i was shocked how small the grain was/eshet in Amharic and shewit in Tigrigna,who care about the name of a land there while nature is deteriorating,I am an Ethiopian again and again.

    Reply
  5. Tadesse says

    July 9, 2017 10:51 pm at 10:51 pm

    I am sorry for my anger,some moslim Oromos,insult Ethiopia and all about Ethiopia,the amharans and every,the heroic amharans sent lemesmatu yemikef.

    Reply
  6. Tadesse says

    July 9, 2017 10:54 pm at 10:54 pm

    Like Gonder was built by foreigners.

    Reply
  7. Tadesse says

    July 9, 2017 10:55 pm at 10:55 pm

    Egziabher yefaredachew,lela men yebalal.Ye Ethiopia Egziabher.

    Reply
  8. Tadesse says

    July 9, 2017 10:57 pm at 10:57 pm

    Ye Egziabher lijoch slehonu ende teraw sew becha yefetenalu belo maseb yewahnet new/sle Israelawian yetebale.

    Reply
  9. aradw says

    July 10, 2017 08:34 pm at 8:34 pm

    የኦሮሞን ጉዳይ ለኦሮም ተወት ኣርጉት። ለቀቅ ኣርጉት ። የህ ጉዳይ ፊንፊኔን ወዳ ባለበቷ ኦሮሞ የመመለስ ጉዳይ ነው። የህ ደግሞ ማንንም ኣይጎዳም። ጥቅሙ ግን ለቡዙሃን ነዉ። መሁራኖችም አስተምሩ ተመራመሩ ዘፋኞችም ዘምሩ ዝፋኑ ብር ሰብሰቡ ።

    Reply
  10. telala says

    July 22, 2017 09:32 pm at 9:32 pm

    terei yalegizesh new yeteweledeshiw meweled yalebsh be 1800 wochu akabai neber. Gizena alem telosh hedual. neqa bey wolaitawochen atasedbi. wolaitanet yerasesh new betifelegim lalemehon aticheym. selezih wolaita first minamin yemityewen neger tewet argesh wedefit terameji. aemeroshenem kefet arigw gizew yeneged mehonu kertual. yegimel shint athugn.
    Mulei astesasebish lela new gen min yadergal chinqilatesh ayseram yezorebesh nesh beolf propaganda.
    Ardawm endezihu demo manew leoromo teqorqari yaderegeh. kemelekiaw rak bel metet nalahen nektotal

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule