• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አታስፈራሩን….

November 15, 2017 12:30 am by Editor Leave a Comment

የጎርፉ፣ የዝናቡ፣ የምድሩና የሰማዩ ፈጣሪ እያለ የምንፈራው የለም፡፡ ዛሬ ጨዋታው ተቀይሯል፡፡ ላለፉት 25 ዓመታት መንግስት ተጫዋች ሕዝቡ ደግሞ ቲፎዞ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ጨዋታውም ሜዳውም ተቀይሯል፡፡ አሰላለፉም ለየቅል ነው፡፡ በኢትዮጵያ ምድር  ላይ ተጫዋቹ ሕዝቡ እንደሆነ የኢአህዴግ “መንግስት” ልብ ሊለው ይገባል፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው እያልሁ ወደ ትዝብቴ ላምራ፡፡

ሰሞኑን በአማራ ክልል በቢሮ ደረጃ ባሉ የመንግስት መ/ቤቶች በለውጥ ሥራዎች ዙሪያ ለአንድ ሳምንት ያህል ከሠራተኛው ጋር ተሃድሶ አይሉት ሥልጠና አልያም ውይይት በዉል ባልታወቀ ጉዳይ የተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ሥራ ፈተው ሲናቆሩ መሰንበታቸውን ስሰማ መንግስት ማለያውንና አሰላለፉን ቀይሮ ያለደጋፊ የጀመረው ጨዋታ እንደሆነ ከጅምሩ ታዝቤአለሁ፡፡

መሰንበቻውን ለመንግስት መ/ቤት ሠራተኞች በመልካም አስተዳደር፣ በውጤት ተኮር ስርዓት፣ በዜጎች ቻርተር ጽንሰ ሀሳብና አተገባበር፣ በለውጥ ሠራዊት ግንባታ፣ በለውጥ መሳሪያዎች ትስስር፣ በመንግስት ሠራተኞች ሥነ ምግባር ኮድ፣ በስብሰባ አፈጻጸምና ማኑዋል በሚሉ ባረጁና ባፈጁ ሰነዶች ዙሪያ በኃይልና በቡድን መድረክ ሲያላጉ መሰንበታቸው ሳያንስ ዓለም ላይ የሌለውን ገነት መሳይ መልካም አስተዳደርና ለውጥ በማስመዝገብ ላይ ነን እያሉ ሲያደናቁሩ ሰንብተዋል፡፡ መሰንበቻውን ጆሮ ያልሰጣቸው ቢኖርም የየተቋሙ ኃላፊዎች በየተቋማቸው ያለውን ሲቪል ሰርቫንት ከአስቸኳይ ጊዜ ያልተናነሰ ማዕቀብ ሲጡሉበት፣ ሲደነፉበትና በግራሞት ሲቆዝም ሰንብቷል፡፡

የመንግሥት ተቋማት ከልክ ያለፈ ንግድ ውስጥ በገቡበት፣ በማህበራዊ ፕሮግራሞች መቋረጥ ምክንያት በርካታ ዜጎች ለበለጠ ድህነትና ሲቃይ በተዳረጉበት፣ ቢሮክራቶች በኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር በተዘፈቁበት፣ ሲቪል ሰርቫንቱ ባረጁና ባፈጁ ህጎች፣ ደንቦችና የአሰራር ሰርዓቶች ውስጥ በታመሰበት፣ የሰው ሀብትና የፋይናንስ ስራ አመራሩና የቁጥጥር ስርዓቱ ፈር ባልያዘበት፣ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጡ ተገልጋይን መሠረት ያላደረገና ቅልጥፍናና ውጤታማነት በጎደለበት በአጠቃላይ መልካም አስተዳደር ቀርቶ መልካም አስተዳደሪ በሌለበት ክልል መንግስት ከሠራተኛው ጋር ሆድና ጀርባ በሆነበት ወቅት ይህን አጀንዳ ዘርግቶ ተቀበል፣ አትቀበል … እያለ የሚፎላው የበላይ አመራር ሥራውን ዘንግቶት ይሆን ያስብላል፡፡

ዳንኤል ኩፍማን የተባለ የዘርፉ ተመራማሪ መልካም አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ ተጠያቂነት፣ የፖለቲካ መረጋጋት፣ ውጤታማነት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈንና ሙስና በቁጥጥር ሥር ማዋል ሲቻል እንደሆነ ይናገራል፡፡ ይሁን እንጂ በአገሪቱ ሆነ በአማራ ክልል ያለው መልካም አስተዳደር ከተመራማሪው ሐሳብ በተቃራኒው እንደሆነ የግድ ጥናት የሚጠይቅ አይደለም፡፡

በክልሉ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለማንሳት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ባለመፈጠሩ መልካም አስተዳደር ቀርቶ አስተዳደርም በአግባቡ የለም፡፡ ይልቁንም በሁሉም ዘርፍ ክልሉ እያሽቆለቆለና እንደ ሀገር በክልል የመቀጠል ህልውናው አደጋ ላይ ወድቋል፡፡

ሁሌም የምለው መንግስት በየዓመቱ ሲቪል ሰረቫንቱንና ሌላውን ሕዝብ ለማዘናጋት በሚል አጀንዳ እየቀረጸና መሪ ቃል እየፈበረከ  የሚፈጥረው ትርምስ ኢትዮጵያ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንዳለች የሚያመላክት ነው። መንግስት እንደድሮው መግዛት ተስኖታል፡፡
ህዝቡም እንደድሮው መገዛት ታክቶታል፡፡ የመንግስትና የሕዝቡ ቋንቋም እንደባቢሎኖች የተለያየበት ወቅት ላይ ነን፡፡ ከዚያም ብሶ ሚዲያው ታፍኗል። ትግሉን በተደራጀ መልክ ዳር የሚያደርስ ጠርቶ ባልወጣበት ሁኔታ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ በተለያዩ ከተሞችና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ህዝባዊ ዓመጽ ሊፈነዳ ጫፍ ላይ መድረሱን ለማወቅ ሊቅነት የሚጠይቅ አልሆነም። በዚህ ሁኔታ ዐመጽ ከተነሳም የሚከተለው ትርምስና እልቂት ቀላል ስላይደለ ንፁህ ህሊና ያለው ሁሉ በግልፅ አይቶት መፍራት አለበት። ይህ ፍርሃት በጎ ፍርሃት ሊሆን የሚችለው ወደ መፍትሄው መሄድ ካስቻለን ብቻ ነው።

እኔን የሚገርመኝ በእንደዚህ ዓይነት ቀውጢ ወቅት ብቅ የሚሉ የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎች በመንግስት ዳረጎት ስም ሕዝብን የሚያንገላቱ ተቆርቋሪ መሳዮች በድርጅት ስም ሸበጥ አልባ ታጋዮች ደካማነታቸውን መንግስት በለገሳቸው የሥልጣን ካባ በመሸፈን በሚያደርሱት የመልካም አስተዳደር ችግር ሕዝብንና መንግስትን ለማለያየት እንደሚጥሩ ገዥው መንግስት ሊያስተውለው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡

መንግስት በአገሪቱ መልካም አስተዳደር ይሰፈን የሚል ከሆነ በቅድሚያ በድርጅት ስም የተኮለኮሉትን አባላቱን ሊያጠራ ይገባዋል፡፡ የአባልነት መስፈርቱ በውል ሳይታወቅ እንደ ተራ ሻይ ቤት ማንም ልቅምቃሚ ድርጅቱን እየተጠጋ ቁጥር እንጂ ጥራት በሌለው የድርጅት አባል በአደባባይ አጀንዳ እየተቀረጸና ሀሳብ እየተወረወረ በስውር ደግሞ አባላቱ እርስ በርስ ጥላሸት እተቀባባ የድርጅቱን ምስጢር ገሀድ እያወጡ ደርጅቴ ቢሉን የምንሰማበት ጆሮ የለንም፡፡ በድርጅት አባልነት ስም አታስፈራሩን፡፡ መደራጀት ሕዝብን ለማገልገል፣ ድህነት ለማስወገድ፣ … እንጂ ሠራተኛውን ለመጨቆን እንዳልሆነ ልብ ሊባል ይገባል፡፡

የሰሞኑ የአማራ ክልል የሲቪል ሰርቫንቱ ተሃድሶ መድረክ ያሳየን የየተቋማቱ ኃላፊዎች በሠራተኛው ላይ ዛቻ አይሉት ጥላቻ ሲዘባበቱበትና ሲያስፈራሩት እንደሰነበቱ ታዝበናል፡፡ እየታደስን እንሠራለን እየሠራን እንታደሳለን የሚለውን መሪ ቃል ወደ ጎን በመተው እየዛትን እናሰራለን እያሰራን እናስራለን በሚመስል መልኩ መድረኩ መጠናቀቁን አውቀናል፡፡

በዚህም የክልሉ መንግስት ሊያገኝ ያሰበውን ተቀባይነትና አመኔታ በድርጅቱ ደረስጌዎች ዛቻ እንዳጣው በማወቅ ለቀጣዩ በየተቋማቱ ያሉ አመራሮችንና በድርጅቱ ከመሠረታዊ ድርጅት እስከ ሴል የተሰገሰጉትን አባላት ማንነትና የሙያ ብቃት በማጥራት ከድርጅቱ 37 ዓመት የድል በዓል ማግስት ሊያድሰው ይገባል እላለሁ፡፡

ጲላጦስ ከጣና ዳር (ummp4.20@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule