• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አታስፈራሩን….

November 15, 2017 12:30 am by Editor Leave a Comment

የጎርፉ፣ የዝናቡ፣ የምድሩና የሰማዩ ፈጣሪ እያለ የምንፈራው የለም፡፡ ዛሬ ጨዋታው ተቀይሯል፡፡ ላለፉት 25 ዓመታት መንግስት ተጫዋች ሕዝቡ ደግሞ ቲፎዞ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ጨዋታውም ሜዳውም ተቀይሯል፡፡ አሰላለፉም ለየቅል ነው፡፡ በኢትዮጵያ ምድር  ላይ ተጫዋቹ ሕዝቡ እንደሆነ የኢአህዴግ “መንግስት” ልብ ሊለው ይገባል፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው እያልሁ ወደ ትዝብቴ ላምራ፡፡

ሰሞኑን በአማራ ክልል በቢሮ ደረጃ ባሉ የመንግስት መ/ቤቶች በለውጥ ሥራዎች ዙሪያ ለአንድ ሳምንት ያህል ከሠራተኛው ጋር ተሃድሶ አይሉት ሥልጠና አልያም ውይይት በዉል ባልታወቀ ጉዳይ የተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ሥራ ፈተው ሲናቆሩ መሰንበታቸውን ስሰማ መንግስት ማለያውንና አሰላለፉን ቀይሮ ያለደጋፊ የጀመረው ጨዋታ እንደሆነ ከጅምሩ ታዝቤአለሁ፡፡

መሰንበቻውን ለመንግስት መ/ቤት ሠራተኞች በመልካም አስተዳደር፣ በውጤት ተኮር ስርዓት፣ በዜጎች ቻርተር ጽንሰ ሀሳብና አተገባበር፣ በለውጥ ሠራዊት ግንባታ፣ በለውጥ መሳሪያዎች ትስስር፣ በመንግስት ሠራተኞች ሥነ ምግባር ኮድ፣ በስብሰባ አፈጻጸምና ማኑዋል በሚሉ ባረጁና ባፈጁ ሰነዶች ዙሪያ በኃይልና በቡድን መድረክ ሲያላጉ መሰንበታቸው ሳያንስ ዓለም ላይ የሌለውን ገነት መሳይ መልካም አስተዳደርና ለውጥ በማስመዝገብ ላይ ነን እያሉ ሲያደናቁሩ ሰንብተዋል፡፡ መሰንበቻውን ጆሮ ያልሰጣቸው ቢኖርም የየተቋሙ ኃላፊዎች በየተቋማቸው ያለውን ሲቪል ሰርቫንት ከአስቸኳይ ጊዜ ያልተናነሰ ማዕቀብ ሲጡሉበት፣ ሲደነፉበትና በግራሞት ሲቆዝም ሰንብቷል፡፡

የመንግሥት ተቋማት ከልክ ያለፈ ንግድ ውስጥ በገቡበት፣ በማህበራዊ ፕሮግራሞች መቋረጥ ምክንያት በርካታ ዜጎች ለበለጠ ድህነትና ሲቃይ በተዳረጉበት፣ ቢሮክራቶች በኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር በተዘፈቁበት፣ ሲቪል ሰርቫንቱ ባረጁና ባፈጁ ህጎች፣ ደንቦችና የአሰራር ሰርዓቶች ውስጥ በታመሰበት፣ የሰው ሀብትና የፋይናንስ ስራ አመራሩና የቁጥጥር ስርዓቱ ፈር ባልያዘበት፣ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጡ ተገልጋይን መሠረት ያላደረገና ቅልጥፍናና ውጤታማነት በጎደለበት በአጠቃላይ መልካም አስተዳደር ቀርቶ መልካም አስተዳደሪ በሌለበት ክልል መንግስት ከሠራተኛው ጋር ሆድና ጀርባ በሆነበት ወቅት ይህን አጀንዳ ዘርግቶ ተቀበል፣ አትቀበል … እያለ የሚፎላው የበላይ አመራር ሥራውን ዘንግቶት ይሆን ያስብላል፡፡

ዳንኤል ኩፍማን የተባለ የዘርፉ ተመራማሪ መልካም አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ ተጠያቂነት፣ የፖለቲካ መረጋጋት፣ ውጤታማነት፣ የህግ የበላይነትን ማስፈንና ሙስና በቁጥጥር ሥር ማዋል ሲቻል እንደሆነ ይናገራል፡፡ ይሁን እንጂ በአገሪቱ ሆነ በአማራ ክልል ያለው መልካም አስተዳደር ከተመራማሪው ሐሳብ በተቃራኒው እንደሆነ የግድ ጥናት የሚጠይቅ አይደለም፡፡

በክልሉ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለማንሳት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ባለመፈጠሩ መልካም አስተዳደር ቀርቶ አስተዳደርም በአግባቡ የለም፡፡ ይልቁንም በሁሉም ዘርፍ ክልሉ እያሽቆለቆለና እንደ ሀገር በክልል የመቀጠል ህልውናው አደጋ ላይ ወድቋል፡፡

ሁሌም የምለው መንግስት በየዓመቱ ሲቪል ሰረቫንቱንና ሌላውን ሕዝብ ለማዘናጋት በሚል አጀንዳ እየቀረጸና መሪ ቃል እየፈበረከ  የሚፈጥረው ትርምስ ኢትዮጵያ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንዳለች የሚያመላክት ነው። መንግስት እንደድሮው መግዛት ተስኖታል፡፡
ህዝቡም እንደድሮው መገዛት ታክቶታል፡፡ የመንግስትና የሕዝቡ ቋንቋም እንደባቢሎኖች የተለያየበት ወቅት ላይ ነን፡፡ ከዚያም ብሶ ሚዲያው ታፍኗል። ትግሉን በተደራጀ መልክ ዳር የሚያደርስ ጠርቶ ባልወጣበት ሁኔታ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ በተለያዩ ከተሞችና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ህዝባዊ ዓመጽ ሊፈነዳ ጫፍ ላይ መድረሱን ለማወቅ ሊቅነት የሚጠይቅ አልሆነም። በዚህ ሁኔታ ዐመጽ ከተነሳም የሚከተለው ትርምስና እልቂት ቀላል ስላይደለ ንፁህ ህሊና ያለው ሁሉ በግልፅ አይቶት መፍራት አለበት። ይህ ፍርሃት በጎ ፍርሃት ሊሆን የሚችለው ወደ መፍትሄው መሄድ ካስቻለን ብቻ ነው።

እኔን የሚገርመኝ በእንደዚህ ዓይነት ቀውጢ ወቅት ብቅ የሚሉ የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎች በመንግስት ዳረጎት ስም ሕዝብን የሚያንገላቱ ተቆርቋሪ መሳዮች በድርጅት ስም ሸበጥ አልባ ታጋዮች ደካማነታቸውን መንግስት በለገሳቸው የሥልጣን ካባ በመሸፈን በሚያደርሱት የመልካም አስተዳደር ችግር ሕዝብንና መንግስትን ለማለያየት እንደሚጥሩ ገዥው መንግስት ሊያስተውለው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡

መንግስት በአገሪቱ መልካም አስተዳደር ይሰፈን የሚል ከሆነ በቅድሚያ በድርጅት ስም የተኮለኮሉትን አባላቱን ሊያጠራ ይገባዋል፡፡ የአባልነት መስፈርቱ በውል ሳይታወቅ እንደ ተራ ሻይ ቤት ማንም ልቅምቃሚ ድርጅቱን እየተጠጋ ቁጥር እንጂ ጥራት በሌለው የድርጅት አባል በአደባባይ አጀንዳ እየተቀረጸና ሀሳብ እየተወረወረ በስውር ደግሞ አባላቱ እርስ በርስ ጥላሸት እተቀባባ የድርጅቱን ምስጢር ገሀድ እያወጡ ደርጅቴ ቢሉን የምንሰማበት ጆሮ የለንም፡፡ በድርጅት አባልነት ስም አታስፈራሩን፡፡ መደራጀት ሕዝብን ለማገልገል፣ ድህነት ለማስወገድ፣ … እንጂ ሠራተኛውን ለመጨቆን እንዳልሆነ ልብ ሊባል ይገባል፡፡

የሰሞኑ የአማራ ክልል የሲቪል ሰርቫንቱ ተሃድሶ መድረክ ያሳየን የየተቋማቱ ኃላፊዎች በሠራተኛው ላይ ዛቻ አይሉት ጥላቻ ሲዘባበቱበትና ሲያስፈራሩት እንደሰነበቱ ታዝበናል፡፡ እየታደስን እንሠራለን እየሠራን እንታደሳለን የሚለውን መሪ ቃል ወደ ጎን በመተው እየዛትን እናሰራለን እያሰራን እናስራለን በሚመስል መልኩ መድረኩ መጠናቀቁን አውቀናል፡፡

በዚህም የክልሉ መንግስት ሊያገኝ ያሰበውን ተቀባይነትና አመኔታ በድርጅቱ ደረስጌዎች ዛቻ እንዳጣው በማወቅ ለቀጣዩ በየተቋማቱ ያሉ አመራሮችንና በድርጅቱ ከመሠረታዊ ድርጅት እስከ ሴል የተሰገሰጉትን አባላት ማንነትና የሙያ ብቃት በማጥራት ከድርጅቱ 37 ዓመት የድል በዓል ማግስት ሊያድሰው ይገባል እላለሁ፡፡

ጲላጦስ ከጣና ዳር (ummp4.20@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule