• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም” !

July 3, 2015 08:41 am by Editor 1 Comment

ሰሞኑን ኦባማ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው በሚል፤ ከባህር ማዶ ጫጫታ፤ ከወደ አገር ቤት ደግሞ የጆሮ ብራና የሚጠልዝ ከበሮ ድለቃው ተጧጡፏል:: ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ::

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    July 8, 2015 07:43 pm at 7:43 pm

    ***በዘመነ የርዕዮተዓለም ኢምፔሪያሊስት ሶሺያሊስት ጦርነት ህወአት አሸባሪ ነበር። በዘመነ ካፒታሊስት እና አብዮታዊ ዴሞክራሲአዊ የድብልቅ ኢኮኖሚ የቀድሞው አሸባሪ የአሁን የፀረ ሽብር አቀንቃኝ ሆኖ ሲመቸው ነጭ እጄን አይጠመዝዘኝም ሲል ሳይመቸው እጅ እየፈለቀቀ ሲለምንና ሲበደር ጭራሽም ያሳዳሪዎቹን ጥቅም(ኢንቨስትመንት) ለማስከበር የአካባባቢው ቋሚ ተጠሪ ሆኖ የድሃ ልጅ ነፍስ በቀን ሁለት ዶላር ክፍያ በሰው ይግብራል።
    “ለመሆኑ ኦባማ ኢትዮጵያን ጎበኙ አልጎበኙ የኢትዮጵያን ሕዝብ የባርነት ሰንሰለት ከማጥበቅ በቀር ምን የሚያመጣው ለውጥ ይኖራል?
    እነሱ አይደሉም እንዴ ወያኔን ከጫካ ጀምረው መሳሪያና ገንዘብ በማቅረብ፤ በሳተላይት የኢትዮጵያን ሠራዊት አሳላለፍ፤
    የመሳሪያ ብዛትና ዓይነት መረጃ በመስጠት፤ የኢትዮጵያን ሠራዊት እንዲበተን አድርገው አራት ኪሎ ድረስ እጃቸውን ጎትተው ያስገቧቸው?
    አሁንስ እነሱ አይደሉም እንዴ ለወያኔ እርዳታና ብድር እያስታቀፉ የመከራ ዘመናችንን የሚያራዝሙት?”
    *************
    —– ኦቦ ባራክ ሁሴን ሲመረጡ ከትውልድ ከአሜሪካን በበለጠ ኢትዮጵያውያን ጨፍረዋል ቢራ ጠጥተዋል በእርግጥ ለሀገራችን ለውጥ ያመጣሉ ብለው አስበው ወይስ አጋጣሚውን አጝኝተው ለግል እርካታ? በተስረቅራቂ ድምፃቸው ይቻላል እንዳሉ በተሰረቀ ድምፃቸው ተሞክሯል ሲሉ ቢጮሁም አይደመጡም!ያ ሁሉ ጥቅስ፣ ያ ሁሉ መፈክር!አደባባይ በላው የፈረደበት የጥቁር ዘር ከድሮው በበለጠ ዛሬ በቀን አንድ መንገድ ላይ በጥይት ይደፋል….(ኢህአዴግ የሚገለውን በቁጥር ስለማያውቀው በዓላማ አንድ ናቸው) ኦቦ ሁሴን ድሮም ለመመረጥ ያስቻላቸው ከታዋቂና ሀብታም ነጭ መጠጋታቸው… ቤቱ በዕዳ የተዘፈቀ ስለነበር የነጩን ዕዳ ጥቁር ላይ ለመለጠፍ ታሰቦ ነበር ከቻይና ሶስት ትሪሊየን ዕዳ ምን አላት?…የእኛን ቤት ዕዳ ማን ቆጠረው?
    * ኦባማ ከአሜሪካ ዱሞክራሲ በሻንጣ ሸክፎ ይመልኛል ብሎ የሚያንጋጥጥ ካለ፤ አፉን ለአሞራ ኩስ መጸዳጃ እንዳያደርግ አደራ እላለሁ::
    * ላላው ከወደ አሥመራ ዲሞክራሲ በቦይ ኮለል ብሎ ይፈስና ተጠምቄ እድናለሁ ብሎ የሚያስብ ካለ እሱ ሽባ እንደሆነ ይቀራል እንጂ አይድንም:: ምክንያቱም ወያኔና ሻዕቢያ በአንድ ላይ ቆመው የጠጡት ጽዋ ቢኖር ኢትዮጵያን በዘርና በጎሳ የመበታተን ዘመቻ በመሆኑ፤ አስመሳዩ የወያኔና የሻዕቢያ ጥል፤ አገር ወዳድን ዜጎችን ከወዲያና ከወዲህ እየነጠለ ለመምታት የተሸረበ የተንኮል ገመድ ለመሆኑ የእስከዛሬው ውጤት ምስክር ሆኖ ሊያገለግል ይገባል::”…አሜሪካኖች በጥቅሉ ምዕራባውያን ከብዙ ሚሉዮን ኢትዮጵያውያን ሕይወት ይልቅ ጥቅማቸውን ያስቀድማሉ፤ ዕርዳታ ሲሰጡ እንኳን በሁለትና ሦስት እጥፍ እንደሚመልሷት ሳያሰሉ እጃቸውን አይዘረጉም፤ ዱሞክራሲን ለእነሱ(ለጠገቡ) እንጂ ለእኛ (ለድሃና ርሃብተኛ) እንደ ቅንጦት እቃ ነው የሚቆጥሩት፤ ስለዚህ የኛ ጉዳይ ለእነሱ የእንጀራ ልጃቸው ነው ::
    *** ” በእርግጥ ኦቦ ሁሴን ቻይና ከኢህአዴግ ጋር ያላት ውሽምነት ከኢንቨስትመንቱም በበለጠ ያሰጋቸው ራሺያ ኤርትራን ቀድማ ካገባች ቻይና ሙዜ ከሆነ ፈረንሳይ ከጅቡቲ ቢፋታም አብሮ በመኖር ፍቅር ተስማምቷል።ለዚህም አንዳንዴ ኢትዮጵያ ፈረንሳይኛ ሕዝቧን ታስተምር ጅቡቲና ኢትዮጵያ አንድ ናቸው የሚሉ መሽኮርመም ይሰማሉ… እንግሊዝ አውሮፓ ይቅርብኝ የድሮ ባሮቼ (ሱማሌ..ኬንያ.. ሱዳን…ግብፅ ማለቱ አይቀርም!) ለቀጣናውም ለአካባቢውም የተጻፈ ግን ያልተነበበ የተለጠጠ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ሲመጣ ኢትዮጵያ ሻቢያን መውጋትና የራሷን ክልላዊ መንግስት በኤርትራ ፈጥራ አሰብን የመጠቀም ዕቅድ የሰሜን ኡንዱስትሪ መር ዕቅድ ተግባሪ እንዲሆን ገንዘብና የወታደር እርዳታ ከኦቦ ሁሴን ባራክ ያስፈልጋታል ኢህአዴግ ከትውልድ ትውልድ ሥልጣኑን ይቀጥላል አሜሪካ ሰሜንን በነፃ አገኘች ማለት ይህ ነው። ኦባማ ፎቅና የባቡር ሃዲድ፣ የጫት እርሻ፣ የቢራ ፋብሪካ፣ የብሔር ብሄረሰቦች እስታዲየም፣ የቻይናን የአፍሪካ የአንድነት የጉቦ(ሙስና መር)የእድገት አዳራሽ ለመጎብኘት ከመጡ የገባችም ያልገባችሁም ኦባማ የተናገረውን ጥቅስ በ፹፫ ቋንቋ ፅፋችሁ መጽሐፍ ለማተም የተዘጋጃችሁ…ለሚቀጥለው አምስት ዓመት ዕቅድ ሙሉ ይህንን የኦቦ ሁሴን ጉብኝት ምክንያት አድርጋችሁ ካኒቴራ፣ ቲሸርት፣ ባርኔጣ፣ ለማተም የተዘጋጃችሁ አነስተኛና ጥቃቅን ተጠርናፊዎች የግልም የድርጅትም ሚዲያ የዘረጋችሁ የዚህን ድሃ ሕዝብ ገንዘብ ጤናና ሰላሙንም አስቡለት። የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም እንዳለው በኦቦ ባራክ ሁሴን ጥቅስ የሚያጠቃቅስ አድርባይ እንጂ የሚጠግብ ድሃ አሜሪካ ስለሌለ አፍሪካም አይኖርም።* ከእንግዱህ መዳን በሌሎች የለም ! አይኖርምም !! መዳን በእራስ ብቻ ነው ! በእኛነታችን !! በእራሳችን ብቻ!የፈረንጅ ሳይሆን፤ የአገራችን ኮሶ ቢመርም ደፍረን እንዋጠው ውሎ አድሮ ያሽረናል፤ እናም እንድናለን፤ መዳን በአገር ነውና። አራት ነጥብ። ድንቅ ነው በለው!።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule