• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክብሩ የተነካው የክብር ዶክትሬት

July 12, 2015 07:16 am by Editor Leave a Comment

እንደብዙዎቹ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ዩኒቨርሲቲው በየጊዜው የምርቃት ሥነ ሥርዓቱን በንግግር እንዲከፍቱ ለመረጣቸው ታላላቅ ሰዎች የክብር ዶክትሬት ይሰጣል፡፡ እ.ኤ.አ. 2009 ላይ ግን የአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ የምርቃት ሥነ ሥርዓቱን በንግግር ለከፈቱት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የክብር ዶክትሬት ላለመስጠት መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የፕሬዚዳንቱ ልምድና የሥራ ውጤት ለክብር ዶክትሬት ጣሪያ አልደረሰም የሚል ነበር፡፡ በወቅቱ ጉዳዩ በተወሰነ መልኩ ውዝግብ አስነስቶ የነበረ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው የመክፈቻ ንግግር አድራጊዎችንና የክብር ዶክትሬት የሚሰጣቸውን ግለሰቦች የሚመርጥበት የራሱ ነፃ የሆነ ሒደት እንዳለው፤ የክብር ዶክትሬቱ የሚሰጠውም ለትልቅ ስኬት መሆኑን አስታውቆ ነበር፡፡ በወቅቱ ዲግሪው የክብር ከመሆኑ አንፃር ዩኒቨርሲቲው አሠራሩን መሠረት በማድረግ በውሳኔው መጽናቱ የብዙዎችን ይሁንታ አግኝቷል፡፡ ምንም እንኳ በብዙ ነገሮች አልፎ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት መሆን በራሱ እንደ አንድ ትልቅ ስኬት መታየት አለበት የሚል ክርክር ያነሱ ቢኖሩም፡፡

ይህ የተለየ አጋጣሚ ላይሆን ይችላል፡፡ የክብር ዶክትሬት ብዙዎች ትልቅ ዋጋና ቦታ የሚሰጡት በመሆኑ ሰዎች ሁልጊዜም ለእገሌ የክብር ዶክትሬት ተሰጠ ሲባል ዲግሪው ለተሰጠው ሰው ይገባል አይገባም የሚል የራሳቸውን ምዘና ያካሂዳሉ፡፡ ከዚህ ሲያልፍም ሁለት ሦስት ሆነው ነገሩን ይነጋገሩበታል ይገመግሙታልም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአገራችን ዩኒቨርሲቲዎችም ለተለያዩ ሰዎች የክብር ዶክትሬት እየሰጡ ነው፡፡ ወቅቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን የሚያስመርቁበት እንደመሆኑ ካለፉት ሁለት ወይም ሦስት ሳምንታት ወዲህ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክትሬት ይገባቸዋል ላሏቸው እያበረከቱ ያሉበት ጊዜ ነው፡፡ ከእነዚህ መካከል መቐለ ዩኒቨርሲቲ ባለፈው ሳምንት ለድምፃዊ ኪሮስ ዓለማየሁ፣ ለሰር ቦብጊልዶፍና መቐለ ከተማ የሚገኘው ኒኮላስ ሮቢንሰን ትምህርት ቤት መሥራች ለሆኑት ጥንዶች ማክስና ካትሪና ሮቢንሰን ሲሰጥ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለሶል ሬብልሷ ቤተልሔም ጥላሁንና ለለማ ጉያ መስጠታቸው ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለቢል ጌትስና ለቱርኩ ፕሬዚዳንት ጣይብ ኤርዶጋን የክብር ዶክትሬት መስጠቱም ይታወሳል፡፡

ባለፈው ዓመት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት የሰጣቸው አርቲስት ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) የክብር ዶክትሬት ሊያገኙ ሲገባቸው የተረሱ፤ ዕውቅናው ሲሰጣቸውም ዘግይቶ የተሰጣቸው እንዳሉ ይናገራሉ፡፡ ለምሳሌ እሳቸው ይህን ዕውቅና ቀደም ሲል ማግኘት ይገባቸው እንደነበር አስተያየት የሰጧቸው ጥቂት እንዳልሆኑ ይናገራሉ፡፡

እሳቸው እንደሚሉት በየዘርፉ የሚመለከታቸው አካላት የመንግሥት ተቋማትና የሙያ ማኅበራት ዕውቅናው ይገባቸዋል የሚሏቸውን ፈልገው የማውጣትና ዕውቅና ለሚሰጠው አካል የማመልከት አሠራር ሊኖር ይገባል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የሚገባቸው ዕውቅናውን ለማግኘት ሊዘገዩ ከናካቴውም ሳያገኙ ሊቀሩ ይችላሉ፡፡ ‹‹አንገታቸውን ደፍተው በዝምታ የሚሠሩ ብዙ አሉ፡፡ እንደሸንኮራ ተመጥጠው የተጣሉም›› ይላሉ፡፡

በሌላ በኩል የክብር ዶክትሬት ዕውቅና ለማግኘት ዘገዩ ወይም ሳያገኙ ቀሩ ሳይሆን ዕውቅናው ለማይገባቸው እየተሰጠ መሆኑን በመግለጽ ዕውቅናውስ በምን መስፈርት እየተሰጠ እንደሆነ የሚጠይቁ ብዙዎች ናቸው፡፡

በማኅበራዊ ጥናት መድረክ (ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ) አጥኚ የሆኑት ዶ/ር ዘሪሁን መሀመድ በዩኒቨርሲቲዎቻችን የክብር ዶክትሬት አሰጣጥ ላይ ችግሮች አለ ብለው ያምናሉ፡፡ የመጀመርያው የክብር ዶክትሬቱ ለማን መሰጠት አለበት? የሚለውን በሚመለከት መስፈርቶች ግልፅ አይደሉም የሚል አስተያየት አላቸው፡፡ ‹‹ለሰዎች ዕውቅና መስጠት ይገባል፡፡ ግን የሚታየው የአገልግሎት ዘመን ነው? ስኬት? የታተሙ ሥራዎች ናቸው? ግልፅ የሆነ የመለኪያ መሠረት ያለን አይመስለኝም›› ይላሉ፡፡

በውጭ አገር በተሰማሩበት ሙያ ከስኬት ጫፍ የደረሱና ሥራቸውም በተጨባጭ ለሚታይ ሰዎች ዕውቅናው እንደሚሰጥ በመጥቀስ ዩኒቨርሲቲዎቻችን ግን በሙያቸው ገና ግማሽ መንገድ ለተጓዙ መስጠታቸው ጥያቄ ውስጥ የሚወድቅ መሆኑን ያመለክታሉ፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ዕውቅና መሰጠት ካለበት ዕውቅናው የግድ የክብር ዶክትሬት መሆን አለበት ወይ? የሚል ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ እዚህ ላይም የተለያዩ አገሮችን በኒሻንና በተለያዩ ማዕረጎች ዕውቅና የመስጠት ተሞክሮ በማንሳት ዕውቅና ይገባቸዋል ለሚባሉ ሁሉ የግድ የክብር ዶክትሬት መሆን የለበትም የሚል ጠንካራ አቋማቸውን ያንፀባርቃሉ፡፡ በኒሻንና ለሌሎች ሽልማቶች ዕውቅና የመስጠት ነገር በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሥርዓት፣ ዘግይቶም ቢሆን በደርግም እንደነበር በማስታወስ ‹‹ለውጭ አገር ዜጋም፣ በዚህኛውም በዚያኛውም ዘርፍ ላሉ፣ ለዜጎችም የምንሰጠው የክብር ዶክትሬት ነው›› ይላሉ፡፡

በሌላ በኩል የክብር ዶክትሬት ብርቅዬ እንጂ በብዛት የሚሰጥ መሆን አለበት ወይ? የሚል ጥያቄ የሚያነሱም አሉ፡፡ ‹‹የክብር ዶክትሬትን እንዲሁ መስጠት ክብሩን መንካትና መንሳትም ነው›› የሚል አስተያየታቸውን የሰጡ አሉ፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ቁጥራቸው በርካታ በሆነው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት በመስጠት ፉክክር ውስጥ የገቡ እስኪመስል ሩጫ እየታየ መሆኑን ለሪፖርተር የገለጹም አልታጡም፡፡ አንዳንዶች እውነትም ሥራቸው ብቻ ሳይሆን ቲፎዞ ጭምር ለክብር ዶክትሬት እንዳበቃቸውም አስተያየት ይሰነዝራል፡፡

ሌላው ከክብር ዶክትሬት ጋር በተያያዘ እንደ ችግር የሚነሳው ዲግሪው መጠሪያ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ዶ/ር ዘሪሁንን የመሰሉ ብዙዎች ዲግሪው በፍጹም መጠሪያ መሆን የለበትም የሚል አቋም ሲይዙ ይህን የሚቃወሙም አሉ፡፡ ዕውቅናው የጥረት የልፋት ዋጋ በመሆኑ መጠሪያ መሆን አለበት መጠሪያም ነው የሚሉት ባለፈው ዓመት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ባበረከተላቸው ዝግጀት ላይ ከዚያ ዕለት ጀምሮ ማንም ዶ/ር ብሎ ሊጠራቸው እንደሚገባ ያሳሰቡት አርቲስት ተስፋዬ አበበ ናቸው፡፡ ‹‹ብዙዎች ሲጠሩበት ኖረዋል፡፡ እንደዚሁ እንደ ሎተሪ ሳይሆን የሕይወት ታሪክና ስኬት ታይቶ የተሰጠ ነው›› ብለዋል፡፡

በተቃራኒው የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የተለያዩ የክብር ዶክትሬቶች ማግኘትን ነገር ግን ዶክተር ተብለው ተጠርተው እንደማያውቁ የሚያስታውሱት ዶ/ር ዘሪሁን የክብር ዶክትሬት የተበረከተላቸው ዶ/ር ሲባሉ አቤት ማለት የሚዲያውም ይህን ዲግሪ እንደመጠሪያ መጠቀም አግባብ አይደለም ይላሉ፡፡

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለሆኑት ዶ/ር ፍቅሬ ለሜሳ የክብር ዶክትሬት ዕውቅና ሲሰጥ ዩኒቨርሲቲው ምንን መሠረት አድርጎ እንደሆነ በማስመልከት ጥያቄ አቅርበን ነበር፡፡ ዩኒቨርሲቲው ዕጩዎችን ከመምረጥ፣ የሕይወት ተሞክሮና የሥራ ልምዳቸውን መመርመርን ጨምሮ አጠቃላይ ሒደቱ የሚመራበት መመሪያ መኖሩን ይገልጻሉ፡፡ ሒደቱ ምስጢራዊ ሲሆን ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ዲኖች ይሳተፋሉ፡፡ ‹‹ዋናው መስፈርታችን ኅብረተሰብን በራስ ጥረት በመንቀሳቀስ መጥቀም ነው›› በማለት ምሳሌ መሆን መቻል፣ በሥራ የተመሰገኑ መሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ አገርን ማሳወቅ ከመስፈርቶቹ መካከል ናቸው፡፡ ዕጩዎች በዩኒቨርሲቲው፣ ከዩኒቨርሲቲው ውጪ ባሉ አካላትም ሊጠቆሙ ሲችሉ ዕጩዎችን የሚያቀርበው ፕሬዚዳንቱ ሲሆን በመጨረሻ የክብር ዶክትሬቱን የሚያፀድቀው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡

ዶ/ር ፍቅሬ እንደሚሉት ዕጩዎች ላይ ጥናት የሚደረገው ምስጢራዊ በሆነ መንገድ ሲሆን የዕጩዎች ሥራና ስኬት ተጨባጭነት ይመዘናል፡፡ በሌላ በኩል መመሪያው ለመንግሥት ባለሥልጣናት ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይከለክላል፡፡ ይህ የሆነው ባለሥልጣኑን ለመጥቀም ወይም ዩኒቨርሲቲው ራሱ ጥቅምን ታሳቢ በማድረግ ነው የሚል አመለካከት ይፈጥራል በሚል ሥጋት ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲያቸው በሰጠው የክብር ዶክትሬቶች ጥያቄ ተነስቶ ወይም ቅሬታ ቀርቦ ያውቅ እንደሆነ ለዶ/ር ፍቅሬ ጥያቄ አቀረብን፡፡ ‹‹ብዙ ቅሬታዎች ሊኖሩ ይችላሉ ግን ኦፊሻሊ በእኔ በኩል የመጣ ነገር የለም›› የሚል ነበር መልሳቸው፡፡ ዕውቅናው የሚገባቸው ብዙ እንደሚኖሩ ነገር ግን የግድ ከእነሱ ውስጥ ምርጥ የሚባሉትን መምረጥ የግድ መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አድማሱ ፀጋዬም የክብር ዶክትሬት የመስጠቱ ሒደት ሴኔት ባጸደቀው መመርያ የሚመራ ሲሆን ዕውቅናው በትክክል መመርያው ላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች መሠረት አድርጎ እንደሆነ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

እሳቸው እንዳሉት ማንም የክብር ዶክትሬት ይገባዋል የሚለውን መጠቆም ይችላል፡፡ ይገባናል የሚሉም ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ ዩኒቨርሲቲውም ይመርጣል፡፡ ለምሳሌ በመስፈርቶቹ መሠረት ለአንድ ሰው የክብር ዶክትሬት መስጠት ለዩኒቨርሲቲው ገፅታ ግንባታ አስተዋጽኦ ያበረክታል ወይ? የሚለው እንደ አንድ ነገር ይታያል፡፡ በቅርቡ ለቢል ጌትስና ለቱርኩ ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን የክብር ዶክትሬት የተሰጠው ከዚህ አንፃር ሲሆን ከራሳቸው በቀረበ ጥያቄ መሠረት እንደሆነ ደ/ር አድማሱ ገልጸዋል፡፡

እንደ ብርቅ መታየት ያለበት የክብር ዶክትሬት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየበዛ ነው ከዚህም ባለፈ ሁኔታው በኮታ እስኪመስል የክብር ዶክትሬትን ዋጋ የማጥፋት አካሄድ ነው የሚል አስተያየታቸውን የሰነዘሩ አሉ፡፡ ዶ/ር አድማሱ ግን የቁጥር ነገር እንደ ዩኒቨርሲቲዎች ሊለያይ እንደሚችል፤ ይህን ያህል ይሁን ብሎ መወሰን የዩኒቨርሲቲዎችን አካዴሚክ ነፃነት መጋፋት እንደሚሆንም ያስረዳሉ፡፡

ዩኒቨርሲቲያቸውን በምሳሌነት በመጥቀስ በዚህ ዓመት ይህን ያህል የክብር ዶክትሬት እንሰጣለን የሚል ነገር በአሠራራቸው እንደሌለ፤ በዘንድሮው የምርቃት ሥነ ሥርዓትም ለአንድ ድርጅት ዕውቅና ከመስጠት ባሻገር ዩኒቨርሲቲያቸው የክብር ዶክትሬት ለግለሰብ እንደማይሰጥ አስታውቀዋል፡፡ ጊዜን በሚመለከት ደግሞ እንደ ጥያቄውና እንደ ሴኔቱ ውሳኔ በምርቃት ሥነ ሥርዓት ላይ ብቻም ሳይሆን በማንኛውም ጊዜ (ለቢል ጌትስና ለኤርዶጋን እንደተሰጠው) የክብር ዶክትሬት በዓመቱ ማንኛውም ጊዜ ላይ ሊሰጥ ይችላል ብለዋል፡፡

የክብር ዶክትሬት መጠሪያ ይሆናል ወይ? ሌላው ለዶ/ር አድማሱ ያቀረብነው ጥያቄ ነበር፡፡ ‹‹እኛ ሊጠሩበት ይችላሉ ነው የምንለው፡፡ ነገር ግን ሊጠሩበት ይችላሉ አይችሉም የሚለው ነገር አሁን አሁን መነጋገሪያ እየሆነ በመሆኑ የሌሎችን የውጭ አገር ዩኒቨርሲቲዎች ተሞክሮ በማየት በቅርቡ ውሳኔውን እናሳውቃለን›› የሚል መልስ ሰጥተዋል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule