• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እምቢተኝነት በተግባር!

September 27, 2017 12:02 pm by Editor 1 Comment

“ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”። የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተነተነበት ጽሁፍ ላይ ከተናገረው። ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ።

ዛሬ በተከበረው የመስቀል በዓል ላይ የህወሓትን ማስፈራሪያና ዛቻ ከምንም ባለመቁጠር የውቅሮ፣ ዓዲግራት፣ መቀሌ፣ ጎንደር፣ ደሴና ሌሎች አካባቢዎች ህዝብ “ባለኮከቡን ባንዲራ አይወክለኝም” በማለት ኮከብ አልባውን ሠንቀድ ዓላማ ይዞ በመውጣት እምቢተኝነቱን አድፍረት አሳይቷል።

ሃይለኪሮስ ታፈረ (Hailekiros Tafere) በፌስቡክ ገጹ የዘገበውን አስመልክቶ አምዶን ገብረሥላሴ ይህንን ብሏል፤

“ፖሊስ “ኮከብ የሌለው ባንዴራ ዳሜራ ሸፍናቹሃል” በሚል ሰበብ ዛሬ መስቀል በዓል እያከበረ የነበረው የውቅሮ ከተማ ህዝብ ላይ ድብደባ ፈፅመዋል። የውቅሮ ፖሊስ የመስቀል ዳሜራ በኮከብ የሌለው ባንዴራ ሸፍናቹሃል በማለት በህዝቡ በተለይ በወጣቶችና ህፃናት ላይ ድብደባ ፈፅመዋል። ህወሓት በስመኮከብ ህዝበ ክርስትያን ድብደባ ፈፅማለች።”

በጎንደር፣ በደሴ፣ በመቀሌ፣ በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ሕዝቡ በተመሳሳይ እምቢተኝነቱን ኮከብ አልባውን ሠንደቅ ይዞ በመውጣት አሳይቷል።

በአዲስ አበባ ከበሮውን በባለኮከቡ ጠቅልለው የወጡትን አስመልክቶ እሸቱ ሆማ ቀኖ Eshetu Homa Keno) ይህንን በማለት ተሳልቋል፤

“የሰንደቅ አላማ አዋጁ አንቀፅ 23(9) ደግሞ ሰንደቅ አላማን የህንፃ ወይም የሌሎች ቁሳቁሶች መሸፈኛ ማድረግ የተከለከለ ነው፣ እስከ 3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ወይም እስከአንድ አመት እስር ያስቀጣል ይላል፤ ያው ለማስታወስ ያህል ነው”

ይህንኑ ፎቶ በቅድሚያ በፌስቡክ ገጹ በመለጠፍ ስዩም ተሾመ (Seyoum Teshome) የሚከተለውን አስፍሯል፤

“እዩ እስኪ፣ #የባንድራው_ኮከብ ካሜራው ውስጥ “ገባ-አልገባ” ብለው የተጨነቁ አይመስልም? ታዲያ በእነዚህ ምዕመናን አዕምሮ ውስጥ እየተመላለሰ ያለው #የአምላክ ሥራ ወይስ #የመለስ ሥራ ነው?”

አፍቃሪ ህወሓት የሆነው የፌስቡክ “አርበኛ” ዳንኤል ብርሃኔ በዛሬ በጎንደርና ደሴ ከተሞች በተካሄደው የመስቀል በዓል አከባበር ላይ ኮከብ የሌለበት ባንዲራ ጥቅም ላይ መዋሉን አስመልክቶ በቀጣይ ቀናት አንዳንድ ውዝግቦች ሊነሱ ስለማለቱ ስዩም ይህንን ምላሽ ሰጥቷል።

“ይህ ባለ ኮከቡ ባንዲራ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እንደሆነ የተደነገገው የኢፊድሪ ሕግ-መንግስት ላይ ነው። ነገር ግን፣ ሕገ-መንግስቱን በመጣስ ግንባር ቀደሙ #የኢህአዴግ_መንግስት ራሱ ነው። “ባለቤቱ የናቀው አሞሌን ማንም አይፈልገውም!” እንዲሉ ኢህአዴግ የናቀውን ሕገ-መንግስት #የጎንደርና_ደሴ ህዝብ የሚያከብረው በምን ዕዳው ነው?! ሀገሪቱ እየተመራች ያለው #በፀረ_ሽብር አዋጁ እንጂ በሕገ-መንግስቱ አይደለም። እሱ ደግሞ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላም ላይ ያለው አንባሻ ይሁን ኮኮብ አይደነግግም! ስለዚህ የጎንደርና ደሴ ህዝብ ከፈለገ #የራስተፈራያን ባንዲራ ይዞ መስቀልን ማክበር ይችላል!!!”

ስዩም በጽሁፉ መጨረሻ ላይ ከላይ የጠቀስነውን ሃሳብ ብዚህ መልኩ ደግሞታል፤

“የታፈነ ሕዝብ ያምፃል!” የጎንደር፥ ደሴ፥ ዓዲግራትና ውቅሮ ከተማ ነዋሪዎች የመስቀል በዓል አከባበርን ኮከብ የሌለበትን ባንዲራ መጠቀማቸው ከላይ ከጠቀስኩት ጋር ተመሳሳይ ነው። አመፅና ተቃውሞ አደባባይ ወጥቶ ድንጋይ መወርወር ብቻ አይደለም። የመንግስትን ቅቡልነት ሊያሳጣ የሚችል ማንኛውም ዓይነት ነገር መፈፀም ነው።”

የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁንም በሁሉም አቅጣጫ የህወሓት/ኢህአዴግን አገዛዝ አልቀበልም እያለ በሚያገኘው አጋጣሚ ሁሉ እምቢተኝነቱን እየገለጸ ነው! ትውልድ አምጿል! ሕዝብ እምቢ ብሏል!

ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ ከማኅበራዊ ገጾች ያጠናቀረው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    September 28, 2017 09:04 pm at 9:04 pm

    ኢህኣድግ! ኢህኣድግ!ኢህኣድግ!!
    ምነው ብትጠርግልን ይህን እንኩቶ! እንደ ደርግ??
    በበዓል ቀን በመስቀል!
    ስዕሉ ሌላ ወሬው ለየቅል
    እንግዲህ ምን እንበል??
    የስርዓት ለውጥ ዝም ብሎ
    በተመኘሁ ወይ አባብሎ
    ይመጣ መሰለው ጓዙን ጥሎ??
    ምነው ኢህድግ ይህን ኮተት
    በምርጫ ይሻላል ብለህ ከተትክ?
    አልጫ ኮነው ፍርክርክ!!!!
    ጭብጥ የማይሉ በመድረክ??
    ስድባቸው መረረን ያለልክ!
    ምነ ወጀብ ቢኖርህ
    መጥረግ ነበር!እንዲያ እንድንልህ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule