• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እምቢተኝነት በተግባር!

September 27, 2017 12:02 pm by Editor 1 Comment

“ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”። የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተነተነበት ጽሁፍ ላይ ከተናገረው። ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ።

ዛሬ በተከበረው የመስቀል በዓል ላይ የህወሓትን ማስፈራሪያና ዛቻ ከምንም ባለመቁጠር የውቅሮ፣ ዓዲግራት፣ መቀሌ፣ ጎንደር፣ ደሴና ሌሎች አካባቢዎች ህዝብ “ባለኮከቡን ባንዲራ አይወክለኝም” በማለት ኮከብ አልባውን ሠንቀድ ዓላማ ይዞ በመውጣት እምቢተኝነቱን አድፍረት አሳይቷል።

ሃይለኪሮስ ታፈረ (Hailekiros Tafere) በፌስቡክ ገጹ የዘገበውን አስመልክቶ አምዶን ገብረሥላሴ ይህንን ብሏል፤

“ፖሊስ “ኮከብ የሌለው ባንዴራ ዳሜራ ሸፍናቹሃል” በሚል ሰበብ ዛሬ መስቀል በዓል እያከበረ የነበረው የውቅሮ ከተማ ህዝብ ላይ ድብደባ ፈፅመዋል። የውቅሮ ፖሊስ የመስቀል ዳሜራ በኮከብ የሌለው ባንዴራ ሸፍናቹሃል በማለት በህዝቡ በተለይ በወጣቶችና ህፃናት ላይ ድብደባ ፈፅመዋል። ህወሓት በስመኮከብ ህዝበ ክርስትያን ድብደባ ፈፅማለች።”

በጎንደር፣ በደሴ፣ በመቀሌ፣ በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ሕዝቡ በተመሳሳይ እምቢተኝነቱን ኮከብ አልባውን ሠንደቅ ይዞ በመውጣት አሳይቷል።

በአዲስ አበባ ከበሮውን በባለኮከቡ ጠቅልለው የወጡትን አስመልክቶ እሸቱ ሆማ ቀኖ Eshetu Homa Keno) ይህንን በማለት ተሳልቋል፤

“የሰንደቅ አላማ አዋጁ አንቀፅ 23(9) ደግሞ ሰንደቅ አላማን የህንፃ ወይም የሌሎች ቁሳቁሶች መሸፈኛ ማድረግ የተከለከለ ነው፣ እስከ 3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ወይም እስከአንድ አመት እስር ያስቀጣል ይላል፤ ያው ለማስታወስ ያህል ነው”

ይህንኑ ፎቶ በቅድሚያ በፌስቡክ ገጹ በመለጠፍ ስዩም ተሾመ (Seyoum Teshome) የሚከተለውን አስፍሯል፤

“እዩ እስኪ፣ #የባንድራው_ኮከብ ካሜራው ውስጥ “ገባ-አልገባ” ብለው የተጨነቁ አይመስልም? ታዲያ በእነዚህ ምዕመናን አዕምሮ ውስጥ እየተመላለሰ ያለው #የአምላክ ሥራ ወይስ #የመለስ ሥራ ነው?”

አፍቃሪ ህወሓት የሆነው የፌስቡክ “አርበኛ” ዳንኤል ብርሃኔ በዛሬ በጎንደርና ደሴ ከተሞች በተካሄደው የመስቀል በዓል አከባበር ላይ ኮከብ የሌለበት ባንዲራ ጥቅም ላይ መዋሉን አስመልክቶ በቀጣይ ቀናት አንዳንድ ውዝግቦች ሊነሱ ስለማለቱ ስዩም ይህንን ምላሽ ሰጥቷል።

“ይህ ባለ ኮከቡ ባንዲራ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እንደሆነ የተደነገገው የኢፊድሪ ሕግ-መንግስት ላይ ነው። ነገር ግን፣ ሕገ-መንግስቱን በመጣስ ግንባር ቀደሙ #የኢህአዴግ_መንግስት ራሱ ነው። “ባለቤቱ የናቀው አሞሌን ማንም አይፈልገውም!” እንዲሉ ኢህአዴግ የናቀውን ሕገ-መንግስት #የጎንደርና_ደሴ ህዝብ የሚያከብረው በምን ዕዳው ነው?! ሀገሪቱ እየተመራች ያለው #በፀረ_ሽብር አዋጁ እንጂ በሕገ-መንግስቱ አይደለም። እሱ ደግሞ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላም ላይ ያለው አንባሻ ይሁን ኮኮብ አይደነግግም! ስለዚህ የጎንደርና ደሴ ህዝብ ከፈለገ #የራስተፈራያን ባንዲራ ይዞ መስቀልን ማክበር ይችላል!!!”

ስዩም በጽሁፉ መጨረሻ ላይ ከላይ የጠቀስነውን ሃሳብ ብዚህ መልኩ ደግሞታል፤

“የታፈነ ሕዝብ ያምፃል!” የጎንደር፥ ደሴ፥ ዓዲግራትና ውቅሮ ከተማ ነዋሪዎች የመስቀል በዓል አከባበርን ኮከብ የሌለበትን ባንዲራ መጠቀማቸው ከላይ ከጠቀስኩት ጋር ተመሳሳይ ነው። አመፅና ተቃውሞ አደባባይ ወጥቶ ድንጋይ መወርወር ብቻ አይደለም። የመንግስትን ቅቡልነት ሊያሳጣ የሚችል ማንኛውም ዓይነት ነገር መፈፀም ነው።”

የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁንም በሁሉም አቅጣጫ የህወሓት/ኢህአዴግን አገዛዝ አልቀበልም እያለ በሚያገኘው አጋጣሚ ሁሉ እምቢተኝነቱን እየገለጸ ነው! ትውልድ አምጿል! ሕዝብ እምቢ ብሏል!

ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ ከማኅበራዊ ገጾች ያጠናቀረው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    September 28, 2017 09:04 pm at 9:04 pm

    ኢህኣድግ! ኢህኣድግ!ኢህኣድግ!!
    ምነው ብትጠርግልን ይህን እንኩቶ! እንደ ደርግ??
    በበዓል ቀን በመስቀል!
    ስዕሉ ሌላ ወሬው ለየቅል
    እንግዲህ ምን እንበል??
    የስርዓት ለውጥ ዝም ብሎ
    በተመኘሁ ወይ አባብሎ
    ይመጣ መሰለው ጓዙን ጥሎ??
    ምነው ኢህድግ ይህን ኮተት
    በምርጫ ይሻላል ብለህ ከተትክ?
    አልጫ ኮነው ፍርክርክ!!!!
    ጭብጥ የማይሉ በመድረክ??
    ስድባቸው መረረን ያለልክ!
    ምነ ወጀብ ቢኖርህ
    መጥረግ ነበር!እንዲያ እንድንልህ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule