• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከሞቱት ያልሞትነው!”

April 25, 2015 03:33 am by Editor Leave a Comment

” ….. የለቅሶና የብዙ ዋይታ ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤ ልጆችዋ ስለሞቱባት መጽናናት እምቢ አለች።….” /ማቴዎስ 2፡18/

ኮንፊሽየስ ወደ ጫካ በመሄድ ግዜውን ማሳለፍ ይወድ ነበር ይባላል። ከዕለታት እንድ ቀን እንደተለመደው ወደ አንድ፤ ከአካባቢው ‘ርቆ ወደሚገኝ ጫካ አመራ። ከሰዓታት ጉዞ በኋላ ጥቅጥቅ ባል ጫካ ውስጥ እንደደረሰ ለማርፍ ሲሞክር የገጠመው፤ የተለመደው የወፎች ዝማሬና የአበባወችና የዛፎች ውብ ማዕዛ ሳይሆን እጅግ አሳዛኝ ፣ የለቅሶና የሲቃ ድምጽ ነበር። ኮንፊሽየስ የሰማውን ማመን እያቃተው ወደዚያው አመራ፤ ወደ ድምጹ እየተጠጋ ሲሄድ፤ አንዲት ሴት ሳሩን እየነጨች መሬቱን እየቧጨረች የ ”ኤሎሄ” ዋይታ ታስተጋባለች። ራሱን ለመቆጣጠር እየሞከረ ቀስ እያለ ተጠጋት። ሊያጽናናትም ሞከረ። ግን የምትጽናና ሴት ሁና አላገኛትም። ይሁን እንጂ በዚህ ጫካ ውሰጥ ለምን እንደመጣችና የዋይተዋን ምክንያት እ‘ድትነግረው አግባባት። እሷም ከአንድ ልጇ ጋር ወደዚህ ጫካ ለመኖር እንደመጣችና ልጇ ግን በአውሬዎች እንደተበላባት ቋንቋ ሊገልጸው በማይችል ሀዘን ነገረችው። ‘’ አውሬዎች አንድ ልጀን ብሉት።”

ኮንፊሽየስም በመገረም ”ለምን ከተማ ውስጥ አትኖሩም ነበር? እንዴት ጫክ ወስጥ መኖር ትመርጣላችሁ?” በማለት ጠየቀ። ያገኘው መልስ ግን ” ጌታዬ ከተማ ያሉት አውሬዎች ከዚህ ጫካ ውስጥ ካሉት አውሬዎች ይብሳሉ፤ የከተማዎቹ አውሬዎች ባሌንና ታላቁን ልጅን በልተዋል፤ የቀረኝን አንድ ልጀን ለማትረፍ ነበር ወደዚህ ጫካ የመጣውት፤ ይኽው እሱንም አጣውት።” አለችው። እኛም ከወያኔ አውሬዎች የተርፉትን ወገኖቻችን በጫካ አውሬዎች አስበላናቸው፣ አሰየፍናቸው::

ግን እኛ ”ያልሞትነው” በህይወት ያለነው ምን እያደረግን ነው? አሁንም እንዳለፈ ሁሉ “መግለጫ እናወጣለን!….. ሻማ እናበራለን!……. ሰላማዊ ሰልፍ እንወጣና፣ ድርጊቱን እናወግዛለን!……. ወያኔ ወገኖቻችን ይታደግ እንላለን (ሃያ አራት ዓመት ሙሉ) ……ወያኔ ደግሞ ቆመጡን ያቀምሰናል፤ ጥይቱን ያጠጣናል፤ እስርቤት ያጉረናል፤ በባዕድ ሀገር እየሄድን እንድንታረድ፣ ከሳአውዲ እስከ የመን፣ ከደቡብ እፍሪካ እስከ ሊቢያ፣ ከሳህራ እስከ ካለሀሪ በርሃ ፣ ከኤደን እስከ ሜድትራኒያን ባህር ብሎም ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ እስከ አለበት ድረስ ባህር፣ እሳት፣ በርሃና ሰይፍ እንዲበላን ያመቻቸናል።

የገዛ ሀገራችን ለወያኔ አውሬዎች አስረክበናልና፤ መንግስትና ሀገር እስከሌለን ድረስ በየትም ቦታ ብንሄድ የሚጠብቀን በባዕዳን አውሬዎች እጅ መውደቅና መታረድ ነው። ኮንፊሽየስ ጫካ ውስጥ እንዳገኛት እናት።

ከዚህ ላይ ከዚህ በፊት የጦመርኩትን በከፊል በድጋሜ ልጠቀም፤

”ዓለም የም‘ጠፋው፣ ሰይጣናዊ ምግባር በሚፈጽሙ ሳይሆን፤ ምንም ሳያደርጉ ቀጭ ብለው በሚመለከቷቸው ሰዎች ነው።” /አልበርት አነስታየን/

እናም የምድርን የሰቆቃና የሞትን አይነት ሁሉ እያስከፈሉን፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን እያጠፉ ያሉት፣ እስላማዊ መንግስት ነኝ ባይ (አይሲኤል) ፣ ወያኔ፣ ሳአውዲ አረቢያ/ አረቦች፣ ምእራቡ ዓለም፣ ደቡብ አፍሪካ ወይም ሌላ ሳይሆን፣ እኛ እራሳችን ቁጭ ብለን የምንመለከተው ወይም ለታይታ የምንታይው፣ ኢትዮጵያዊያኖች ነን። እኛ ነን….. በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ላይ ተቀምጠን፤ ለወገኖቻችን መሆን ያልቻልነው። እኛ ነን….. ለጠባብ መንደርተኞች ሀገራችን አሳልፈን የሰጠን። ትላ’ትናም ይሁን ዛሬ እውነቱ ይኸው ነው። ይኸን እውነታ ተቀብለን፣ በተለይም በዚች ወቅት ለኅልውናችን ስንል የሚጠይቀውን መሰዋእትነት እስከ አልከፈልን ድረስ፣ ስቃይና ሰቆቃ፤ እንደ በግ መታረድ፣ እንደትላ’ቱና እንደዛሬው ሁሉ፣ ነገም ተባብሶ ይደገማል።

ባለፉት ዓመታት ከሀገርቤት ጀምሮ በዓለም ዙሪያ እንደ ቅጠል የረገፉትንና የምድራችንን ስቃይ የከፈሉትን ለግዜውም ቢሆን ወደ ጎን ትተን፤ እስቲ ለደቂቃ የአይሲኤል ሰይፍ የበላቸውን ወግኖቻችን የመጨረሻ ሰዓት እናስበው? ሀዘን፣ …ለቅሶ፣ …. ምን ይበቃል? ዋይታችንን የሚገልጽ ቋንቋ በዚች ምድር ላይ ይኖር ይሆን? ኅሊናችን ምን ይለናል? ” ከሞቱት ላልሞትነው” ለኛ ለቀሪዎቹ ሸክሙ አይከብድም? ”ሰው ከንቱ ነውና……” እንደ ትላንትናዎቹ ወግኖቻችን ነገም እነዚህን እንረሳቸው ይሆን? በየትም ቦታና በማንኛውም ግዜና ሁኔታ ብንሆን ፣ በህይወት ላለን ዜጎች የማናመልጠው ነገር ፤ እነሱ የሰማዕትነትን አክሊል ተቀናጅተው፤ የቤት ስራውን ለኛ ጥለውልን ሄደውል።

ሚያዚያ 2007

ኢ-ሜል: philiposmw@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule