• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከሞቱት ያልሞትነው!”

April 25, 2015 03:33 am by Editor Leave a Comment

” ….. የለቅሶና የብዙ ዋይታ ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤ ልጆችዋ ስለሞቱባት መጽናናት እምቢ አለች።….” /ማቴዎስ 2፡18/

ኮንፊሽየስ ወደ ጫካ በመሄድ ግዜውን ማሳለፍ ይወድ ነበር ይባላል። ከዕለታት እንድ ቀን እንደተለመደው ወደ አንድ፤ ከአካባቢው ‘ርቆ ወደሚገኝ ጫካ አመራ። ከሰዓታት ጉዞ በኋላ ጥቅጥቅ ባል ጫካ ውስጥ እንደደረሰ ለማርፍ ሲሞክር የገጠመው፤ የተለመደው የወፎች ዝማሬና የአበባወችና የዛፎች ውብ ማዕዛ ሳይሆን እጅግ አሳዛኝ ፣ የለቅሶና የሲቃ ድምጽ ነበር። ኮንፊሽየስ የሰማውን ማመን እያቃተው ወደዚያው አመራ፤ ወደ ድምጹ እየተጠጋ ሲሄድ፤ አንዲት ሴት ሳሩን እየነጨች መሬቱን እየቧጨረች የ ”ኤሎሄ” ዋይታ ታስተጋባለች። ራሱን ለመቆጣጠር እየሞከረ ቀስ እያለ ተጠጋት። ሊያጽናናትም ሞከረ። ግን የምትጽናና ሴት ሁና አላገኛትም። ይሁን እንጂ በዚህ ጫካ ውሰጥ ለምን እንደመጣችና የዋይተዋን ምክንያት እ‘ድትነግረው አግባባት። እሷም ከአንድ ልጇ ጋር ወደዚህ ጫካ ለመኖር እንደመጣችና ልጇ ግን በአውሬዎች እንደተበላባት ቋንቋ ሊገልጸው በማይችል ሀዘን ነገረችው። ‘’ አውሬዎች አንድ ልጀን ብሉት።”

ኮንፊሽየስም በመገረም ”ለምን ከተማ ውስጥ አትኖሩም ነበር? እንዴት ጫክ ወስጥ መኖር ትመርጣላችሁ?” በማለት ጠየቀ። ያገኘው መልስ ግን ” ጌታዬ ከተማ ያሉት አውሬዎች ከዚህ ጫካ ውስጥ ካሉት አውሬዎች ይብሳሉ፤ የከተማዎቹ አውሬዎች ባሌንና ታላቁን ልጅን በልተዋል፤ የቀረኝን አንድ ልጀን ለማትረፍ ነበር ወደዚህ ጫካ የመጣውት፤ ይኽው እሱንም አጣውት።” አለችው። እኛም ከወያኔ አውሬዎች የተርፉትን ወገኖቻችን በጫካ አውሬዎች አስበላናቸው፣ አሰየፍናቸው::

ግን እኛ ”ያልሞትነው” በህይወት ያለነው ምን እያደረግን ነው? አሁንም እንዳለፈ ሁሉ “መግለጫ እናወጣለን!….. ሻማ እናበራለን!……. ሰላማዊ ሰልፍ እንወጣና፣ ድርጊቱን እናወግዛለን!……. ወያኔ ወገኖቻችን ይታደግ እንላለን (ሃያ አራት ዓመት ሙሉ) ……ወያኔ ደግሞ ቆመጡን ያቀምሰናል፤ ጥይቱን ያጠጣናል፤ እስርቤት ያጉረናል፤ በባዕድ ሀገር እየሄድን እንድንታረድ፣ ከሳአውዲ እስከ የመን፣ ከደቡብ እፍሪካ እስከ ሊቢያ፣ ከሳህራ እስከ ካለሀሪ በርሃ ፣ ከኤደን እስከ ሜድትራኒያን ባህር ብሎም ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ እስከ አለበት ድረስ ባህር፣ እሳት፣ በርሃና ሰይፍ እንዲበላን ያመቻቸናል።

የገዛ ሀገራችን ለወያኔ አውሬዎች አስረክበናልና፤ መንግስትና ሀገር እስከሌለን ድረስ በየትም ቦታ ብንሄድ የሚጠብቀን በባዕዳን አውሬዎች እጅ መውደቅና መታረድ ነው። ኮንፊሽየስ ጫካ ውስጥ እንዳገኛት እናት።

ከዚህ ላይ ከዚህ በፊት የጦመርኩትን በከፊል በድጋሜ ልጠቀም፤

”ዓለም የም‘ጠፋው፣ ሰይጣናዊ ምግባር በሚፈጽሙ ሳይሆን፤ ምንም ሳያደርጉ ቀጭ ብለው በሚመለከቷቸው ሰዎች ነው።” /አልበርት አነስታየን/

እናም የምድርን የሰቆቃና የሞትን አይነት ሁሉ እያስከፈሉን፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያንን እያጠፉ ያሉት፣ እስላማዊ መንግስት ነኝ ባይ (አይሲኤል) ፣ ወያኔ፣ ሳአውዲ አረቢያ/ አረቦች፣ ምእራቡ ዓለም፣ ደቡብ አፍሪካ ወይም ሌላ ሳይሆን፣ እኛ እራሳችን ቁጭ ብለን የምንመለከተው ወይም ለታይታ የምንታይው፣ ኢትዮጵያዊያኖች ነን። እኛ ነን….. በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ላይ ተቀምጠን፤ ለወገኖቻችን መሆን ያልቻልነው። እኛ ነን….. ለጠባብ መንደርተኞች ሀገራችን አሳልፈን የሰጠን። ትላ’ትናም ይሁን ዛሬ እውነቱ ይኸው ነው። ይኸን እውነታ ተቀብለን፣ በተለይም በዚች ወቅት ለኅልውናችን ስንል የሚጠይቀውን መሰዋእትነት እስከ አልከፈልን ድረስ፣ ስቃይና ሰቆቃ፤ እንደ በግ መታረድ፣ እንደትላ’ቱና እንደዛሬው ሁሉ፣ ነገም ተባብሶ ይደገማል።

ባለፉት ዓመታት ከሀገርቤት ጀምሮ በዓለም ዙሪያ እንደ ቅጠል የረገፉትንና የምድራችንን ስቃይ የከፈሉትን ለግዜውም ቢሆን ወደ ጎን ትተን፤ እስቲ ለደቂቃ የአይሲኤል ሰይፍ የበላቸውን ወግኖቻችን የመጨረሻ ሰዓት እናስበው? ሀዘን፣ …ለቅሶ፣ …. ምን ይበቃል? ዋይታችንን የሚገልጽ ቋንቋ በዚች ምድር ላይ ይኖር ይሆን? ኅሊናችን ምን ይለናል? ” ከሞቱት ላልሞትነው” ለኛ ለቀሪዎቹ ሸክሙ አይከብድም? ”ሰው ከንቱ ነውና……” እንደ ትላንትናዎቹ ወግኖቻችን ነገም እነዚህን እንረሳቸው ይሆን? በየትም ቦታና በማንኛውም ግዜና ሁኔታ ብንሆን ፣ በህይወት ላለን ዜጎች የማናመልጠው ነገር ፤ እነሱ የሰማዕትነትን አክሊል ተቀናጅተው፤ የቤት ስራውን ለኛ ጥለውልን ሄደውል።

ሚያዚያ 2007

ኢ-ሜል: philiposmw@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule