• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዳዊት ጠጠር!

March 24, 2017 05:11 am by Editor Leave a Comment

ሰዉ በሀገሩ እንደ ዜጋ እኩል ተወዳድሮ ለመኖር ከአንድ ብሔር መወለድ ወይንም በጥብቅ መዛመድ የቅድሚያ መመዘኛ ሲሆንበት፤ ወዶ ያላመጣዉ፣ ፈቅዶ ያልተዛመደዉ ብሄሩ የተፈጥሮ ዉበቱ ሳይሆን እርግማን ሲሆንበት፤ ተምሮ ማወቅ አዉቆ መጠየቁ፣ ለሀገሩ መቆርቆሩ በቅን ሳይታይለት ቀርቶ መጨረሻዉ እድለኛ ከሆነ ማዕከላዊ አለያም ቅሊንጦ መግባትና ሰዉሰራሽ ሲኦልን ማየት ማሳረግያዉ ሲሆን በለስ ያልቀናዉ ደግሞ በዚች ምድር የመኖርያ ቀኑ በአንባገነኑ ስርዓት ሲወሰንለት፤ አፈር ገፍቶ ለፍቶ ግሮ ጥሮ ሳይማር ያስተማረዉን ማህበረሰብ በዉቀቱ ለማገልገል በአምስት ለአንድ መጠርነፍ ግዴታ ሲሆንበት፤ በተወለደበት ሀገር እንደ ሁለተኛ ዜጋ መታየት፣ በገዛ ሃገሩ ባዕድ መሆንን፣ ተወዳድሮ ማሸነፍ ሳይቻል ሲቀር ስደትን አማራጭ የሌለዉ መፍትሄ አድርጎ ለመዉሰድ ይገደዳል ይሰደዳልም፡፡ እውነተኛ መግቢያ ባታገኝም ነብሱ ለግዜውም ቢሆን ማረፊያ በማግኘቷ በሀገሩ ካደመነበት ጥቁር ጭጋግ በመራቁ ለጊዜዉም ቢሆን ነብሱ እፎይታ ይሰማታል ነገ የሚል ተስፋ በልቡም ያጭራል:: ሆኖም የተፈጥሮ ጉዳይ ነዉና ሰው ከበቀለበት አፈር ተነጥሎ ሌላ ቦታ እስኪያፈራ ግዜ እንደሚወስድበት ሁሉ በስደት የሚኖርበት ባህል አፈር እና አየር አለመመቸት ከሀገር እና ከቤተሰብ ናፍቆት ጋር ተደምሮ ነፍሱን ምቾት ይነሳዋል፤ ሃሳቡና ቀልቡ ሁሌም ወደተወልደበት፣ አፈር ፈጭቶ፣ ጭቃ አቡኩቶ፣ የበሬ ጭራ ጎትቶ፣ ቦርቆ ወዳደገበት ቀየዉ ሽምጥ ይጋልበበታል በትዝታም ይቆዝማል፡፡

የወገን ጨዋታ በአይኑ እየዞረ ከዛሬ ነገ ይሻላል በሚል ተስፋ ከዚያም ሲያልፍ የኔንስ ሕይወት አንዴ ዉሃ በልቶታል ግን ወገኔን ቤተሰቦቼን ለምን ብሎ ሰዉነቱን ረስቶ ከክብሩ ዝቅ ብሎ ክብሩንና ማንነቱን ከማያዉቁለት በግ መሰል ተኩላዎች ጋር የተናጠቃትን ስጋ መሰል ጥሪት ተስፋ ወዳጣባት ሃገሩ መልሶ በሚልከዉ ገንዘብ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በሙስና ሀንጎቨርና በዘረኝነት አዙሪት የሚመራት መንግስት ነኝ ባይ ወንበዴ ዋነኛዉ የዉጭ ምንዛሬ ምንጭ ከመሆኑም ባሻገር ለወያኔ እብት ማስተንፈሻ ብሎም ከሰዉ በታች ሆኖ በላካት ጥሪት ለወንድሙ ሕይወት ቀነ ቀጠሮ መቁረጫ ምላጭ መግዣ መሆኑን ስረዳ ልቤ በሃዘን ይርዳል እረ ለመሆኑ ይህች ሀገር የማን ናት ብሎ ዉስጤ ይጠይቃል

ይህ ባለ ብዙ ጥያቄና ባለብዙ መልስ ባለቤት የሆነዉ ሃገሩን ናፋቂ ስደተኛ ለህዉሃት መራሹ አንባገነን መንግስት የዉጭ ምንዛሬ አቅም የመጀመሪያዉን ዱላ አቀባይ በመሆን መንግስት ከአሜሪካና አዉሮፓ ከሚያገኝዉ አመታዊ የገንዘብ ተፋሰስ ሰዎስትና አራት እጥፍ በዓመት በአማካኝ ከ3.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያደርጋል፡፡ ይህም ከዉጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ከሚገኘዉ ገቢ ሲነፃፀር በ4 እጥፍ የሚበልጥ ሲሆን ወደዉጭ ሸቀጥ በመላክ የሚገኘውን  ገቢ 93 በመቶው ይሆናል ማለት ነዉ፡፡

ታድያ በንደዚህ ሁኔታ የተገኘን የዉጭን ምንዛሬ በመጠቀም ለሀገር እድገት ለልማት እንዲሁም በሀገራችን የሚታየዉን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለምፍታት ከመጣር ይልቅ ወንበዴዉና በወንበዴዉ ዉስጥ የተሰገሰጉ ሆዳችዉ የማይጠረቃ ቆዳቸዉ ከጅብ ጅማት የተሰሩ ነገራቸዉ ሁሉ እንብላዉ እንብላዉ የሆኑ በእብሪት የታበዩ ለማይረባ አይምሮ የተሰጡ የሀገር ሸክም ወንበዴዎች ጥቅማቸዉን ለማስጠበቅ ሌት ተቀን በወገኖቻችን ላይ ያማያባራ የግፍ ጎራዴዎቻቸዉን ከአፎቱ ከመዘዙ አመታት ተቆጠሩ::

ወገን በሰዉ ሀገር የብሶትና የናፍቆት እንባ ወደዉስጥ ያነባል፤ ከዛ ማዶ የአንድ ክልል ሰዎች ዳንኪራ ይረግጣሉ ዉስኪ ይራጫሉ ባንተ ገንዘብ ባንተ ምንዛሬ በተገዛ እርሳስ  ወንድምህ ለትምህርት እንደወጣ በዛዉ ጠባብተኛ፣ ትምክህተኛ፣  ሽብርተኛ፣  አብዮተኛ ተብሎ በወጣበት ይሰረዛል፤ ላይመለስ ይሸኛል:: ትላንት አንተ የላከዉ ገንዘብ የህዉሃት ወዳጆችና አጋፋሪዎች ደረታቸዉን በእብሪት አሳብጦ እንደ ጎልያድ የገዘፉ እንዲመስላቸዉ አድርጉአቸዋል፤ የህዝብ ሮሮ፣ የህዝብ ዋይታ፣ የህዝብ ጩሀት፣ የህዝብ ብሶትን የሚሰሙበት ጆሮ የሚያሰላስሉበት አይምሮ ተደፍኗል፤ ይልቁንስ ከህዝብ ይልቅ በሲንጋፖር፣ በቻይና፣ በታይላንድ እንዲሁም በአሜሪካና በተለያዩ የአዉሮፓ ሃገራት የሚገኙ አለማቀፍ ባንኮች ዉስጥ በድብቅ ያከማቹት የህዝብ ሀብት ያሳስባቸዋል፣ ያስጨንቃቸዋል::

እዉነታዉ ይህ ነዉ እነሱ ሐገራቸዉን በማይተረቃ የነዋይ ፍቅር አሳልፈዉ ሰተዋል! ለነሱ ሕዝብ ማለት የሀገር ሀብት ሳይሆን ለገቢ ምንጭነት የሚያገለግል ግኡዝ አካል የፋብሪካ ጥሬ ዕቃነት የበለጠ ዋጋ እንደሌለዉ ለማሳየት እሩቅ መሄድ ስያስፈልገን ያለፉትን አስራ አንድ ወራት መለስ ብሎ ኦሮሚያን፣ አማራን እንዲሁም ደቡብን ማሰብ በቂ ነዉ! ሃይ ባይም ያሻዋል:: ዛሬ በሀገር ዉስጥ ስላለዉ ትግልና ምላሹ እንዲሁም በላያችን ላይ ስለተደነገገዉ የአስቸቁአይ የግዜ አዋጅ በማተት ጊዜአችሁን አላጠፋም:: ግና ለወንበዴዉ ጉጀሌ አንዱ የአቅም ምንጭ ሰልሆንነዉ በስደት የምንኖር አገር አልባ ባላገሮች ወይም መንግስት አቆላምጦ የሚጠራን ዳያስፖራዎች በጋራ በመሆን ሕዉሃት መራሹ መንግስት ነኝ ባዩ ላይ የዉጪ ምንዝሬ ምንጭ ላይ ከፍ ያለ ጫና በመፍጠር ለዉጥ ማምጣት ስለሚቻልበት እዉነታ ጥቂት ማለትወደድኩ

በዉጪ ያለዉ የሀገሬ ሰዉ ሊገነዘበዉ የሚገባዉ ነገር ቢኖር ኪሱን አራቁቶ የሚልካት ገንዘብ የዳዊት ጠጠር መሆኗን የመረዳት ጉዳይ ነዉ::

ታድያ ምን ይደረግ? የሚለዉ አንገብጋቢ ጥያቄ ይመስለኛል. . . .

የመተባበሩ ጉዳይ ካለ ሁሉም ጋር መልሱ ያለ ይመስለኛል፤ “የሃገርህን ሰርዶ በሀገር በሬ” እንዲሉ አበዉ እራሱን እንደጎልያድ በትቢት የካበዉ ህዉሃት መራሹ አንባገነኑ መንግስት የቆመበት አንደኛዉ የገንዘብ ምሰሶ መሰረት መሆናችንን ለማሳየት ወደ ሀገር ቤት የምንልከዉን የዉጭ ምንዛሬ መሐለቅ በማቀብ በእብሪትና በማናለብኝነት መሰረታዊና እንደሰዉ የመታየት ብሎም ተፈጥሮአዊ መብቶቻቸዉ እንዲጠበቁላቸዉ የጠየቁ ወገኖችችን ላይ ያለ ሕግ አግባብ ሕፃን ሴት አዝዉንት ወጣት ሳይል የሚወስደዉን የአፈና፣ የድብደባ፣ የእሰራትና፣ ግድያ እንዲያቆም ጫና እንፍጠር!! ብሎም በሀገራችን ዉስጥ የአንባገነን ስርዓት ያበቃ ዘንድ ከዛም የሁሉም ለሁሉም የሚሆን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት የበኩላችንን በመወጣት ከአባቶቻችን በአደራ የተቀበልናትን የደም ዉርስ በመጠበቅ ልጆቻችን የሚኮሩበት ሃገራዊ ቅርስ እናኑር:: በሀገራችንም የህዝብን ጥይቄ መሰረት ያደረገዉ የእንቢተኝነት እንቅስቃሴ ተሳታፊ በመሆን የለዉጥ ሂደቱ ላይ አሻራችንን በማኖር ከትዉልድ ተወቃሽነት እንዳን፤ ለመጭዉ ትዉልድም ከዘረኝነት የፀዳችና ልዕልናዋ የተከበረ ዲሞክራሲያዊት ሃገር በጋራ እንመስርት እላለሁ::

ሰላም ለሀገራችን!!

(መብራቱ ከስቶክሆልም – soranet2011@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule